• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አልሸባብ አይሲስን ሊቀላቀል ነው

April 27, 2015 07:40 am by Editor Leave a Comment

በሶማሊያ የሽብር ተግባራትን በመፈጸም የሚታወቀው አልሸባብ ደመኛና አረመኔውን አይሲስን ሊቀላለቀል መሆኑ ተሰማ፡፡ አገራችንን በተጨማሪ የሽብር ስጋት ውስጥ እነደሚጥላት ተገምቷል፡፡

የሶማሊያን ስፊ ግዛት የሚቆጣጠረው አልሸባብ የማእከላዊ ስልጣኑን ካጣ ወዲህ በደረሰበት ወታደራዊ ኪሳራ የአለም አቀፍ አሸባሪው አልቃይዳ ክንፍ በመሆን እያካሄደ ባለው የደፈጣ ውጊያ ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት ርቋት በንጹሃን ደም የታጠበች መንግስት አልባ ጦር ሜዳ ከሆነች ከሁለት ዓስርት አመታት በላይ አስቆጥራለች።

ሟቹ አቶ መለስ የቆሰቆሱት የሶማሊያ ችግር እስካሁን አልበረደም፤ የኢትዮጵያን ጦር ጨምሮ ከተለያዩ አፍሪካ ሃገራት የተውጣጡ ወታደሮች የሶማሊያን ሰላምና ጸጥታ ለማስከበር እያደረጉ ያለው ጥረት መና ቀርቶ የእሳቱ ወላፈን ድንበር ተሻግሮ ለዜጎቻቸው ጦስ እስከ መሆን ርቆ የሄደበት አጋጣሚ የሰላም አስከባሪ ሃገራቱን ዜጎች በሰላም ወጥቶ የመግባት ደኅንነት ስጋት ውስጥ ጥሎታል።

ሶማሊያ ውስጥ ወታደሮቻቸውን ካሰለፉ ሃገራት መሃከል በዩጋንዳ እና ኬንያ ዜጎች ላይ ይህ እስላማዊ ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን “አልሸባብ” ድንበር ተሻግሮ በንጹሃን ላይ የፈፀመው ዘግናኝ ድርጊት ሳይጠቀስ የማይታለፍ ነው።

አልቃይዳን በይፋ ከተቀላቀለ ወዲህ ከአለም ህዝብ የተገለለው አልሸባብ አለም አቀፋዊ ትኩረትን ለመሳብ በአሜሪካ ላይ ጥቃት ለመፈጸም እቅድ እንዳለው በተደጋጋሚ በሚያወጣቸው የዛቻ መግለጫዎቹ ቡደኑ ሃያል ነን ለሚሉ ሃገራት ሳይቀር ራስ ምታት ሆኗባቸዋል።

በኢህአዴግ ድጋፍ ወፌ ቆመ እያለ የሚገኘውን ሞቃዲሾ ላይ የተገደበ በአምሳሉ የፈጠረውን ስርዓት ባለስልጣናት አልሸባብ ሲሻው በሽብር ጥቃት በመግደል አሊያም እርስ በርሳቸው እንዲናቆሩ ጀሌዎቹን አሾልኮ በማስገባት ከሚፈጽመው ደባ ባሻገር ጊዜ እየጠበቀ ከርቀት በሚያስወነጭፋቸው የከባድ ጦር መሳሪያ አረር የቤተመንግስቱን ሰላም መቅኖ በማሳጣት ሶማሊያ ውስጥ  አለ የሚባለውን መንግስት ህግና ስርዓት ትርጉም አልባ አድርጎታል።

የሶማሊያ አለመረጋጋት አገርሽቶ ለጎረቤት ሃገራት ጦስ እየሆነ በመጣበት በአሁኑ ጊዜ አልሸባብ የሽብር ስትራቴጂውን በመቀየር በቅርቡ ኬንያ ላይ በአንድ ዩኒቨርስቲ ማዕከል በክርስትና እምነት ተከታይ ተማሪዎች ላይ የፈፀመውን አረመኔያዊ ድርጊት በሌሎች ላይ አጠናክሮ ለመቀጠል አለምአቀፍ አሸባሪ ቡድን ከሆነው አይሲስ ጋር በመዋሃድ እንደ ሊቢያ ቢጤዎቹ የሰው ልጅን አንገት በካራ ለማረድ የነደፈው እቀድ በአልሸባብ የአመራር አባላት መካከል ንትርክን ፈጥሮ መሰንበቱ ይነገራል። አልሸባብ ከቡድኑ ጋር ለመዋህድ ያቀረበው ጥያቄ ወታደራዊ የሎጀስቲክ አሊያም የሰው ሃይል ድጋፍ ከዚህ ከአረመኔ አይሲስ ለማግኘት እያደረገ ያለው ጥረት የአልሸባብን ወታደራዊ አቅም እየተመናመነ መምጣት በግልጽ የሚያሳይ ጣረሞት ነው በማት አንዳንዶች ይገልጹታል፡፡ በአንጻሩ ሌሎች አልሸባብ አለምአቀፋዊ አቅሙን እያጎለበት የመጣውን አረመኔ አይሲስ ተዋጊዎች ሶማሌያ በማስገባት ኢትዮጵያን በማተራመስ ለመበቀል የታቀደ ስትራቴጂ ሊሆን እንደሚችል ስጋታቸውን ይገልጻሉ።

በሃይማኖት ሽፋን ምዕራብ አፍሪካ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ቦኮ ሃራም በአካባቢው ሃገራት መንግስታት ወታደሮች በቅንጅት የከፈቱበትን ጦርነት መቋቋም ሲሳነው የቦኮ ሃራም መሪ “ሼካው” ኢራቅ እና ሶሪያ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው የዚህ ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው አይሲስ አሸባሪ ቡድን አካል መሆኑን መግለጹ ይታወሳል። አልሸባብ ሰሞኑን እያሰማ ያለው ጩኸት ቡድኑን ለሁለት መክፈሉን ቢሰማም ይህ አጋጣሚ በአባላቱ መሃከል የተፈጠረው ልዩነት ሰፍቶ ለአልሸባብ ከሶማሊያ ምደር መጥፊያው ምክንያት ካልሆነ የ አይሲስ ዱካ ሶማሊያ ውስጥ ከታየ ኢራቅ፣ ሶሪያንና ሊቢያን እያተራመስ የሚገኘው ሰይጣናዊ ሃይል ለሃገራችን ሰላምና መረጋጋት በእንቀርት ላይ ጆሮ ደግፍ ከመሆን ሊያግደው የሚችል ምድራዊ ኃይል እንደሌለ በበርካቶች ዘንድ የሚታመን ሐቅ እየሆነ መጥቷል።

ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች!

(Ethiopian Hagere Jed Bewadi ለጎልጉል የላኩት)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule