• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አልበሽር ከተቃዋሚዎች ጋር ለመሥራት እፈልጋለሁ አሉ

February 6, 2014 09:50 am by Editor Leave a Comment

የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር ባለፈው ሰኞ በቀጥታ የአገሪቱ ቴሌቪዥን የተሰራጨ ንግግር አድርገዋል፡፡ የአልበሽር ንግግር በሶስት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን ለመጀመርያ ጊዜ  የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮችን ያካተተ ነበር። በቻይና መንግስት ትብብር በተሰራው የብሉ ናይል የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከተሳተፉት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች መካከል አልበሽር ወደ ስልጣን የመጡበትን የ1989ኙን መፈንቅለ- መንግስት በማቀነባበር ወሳኝ ሚና የተጫወቱትና በ2000 ዓ.ም ከገዢው ፓርቲ የ“ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲ” ተገንጥለው “ኦፖዚሽን ፖፑላር ኮንግረስ” ፓርቲን ያቋቋሙት ሀሰን አልቱራቢ፣ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ የአልበሽር አማካሪ የነበሩትና ታህሳስ ላይ የ“ለውጥ ፓርቲ”ን የመሰረቱት ጋዚ ሳላሀዲን አትባኒ እና የ“ኡማ ፓርቲ” መሪ  ሳዲቅ አልመሃዲ ይገኙበታል፡፡

አልበሽር በንግግራቸው ላይ ሶስት የለውጥ ፕሮግራሞች ያሏቸውን ነጥቦች ይፋ አድርገዋል።

  • የመጀመሪያው ፕሮግራም ከተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር በሚደረግ ተከታታይ ውይይት አሁን በስራ ላይ ባለው የአገሪቱ ህገመንግስት እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በመምከር፣ ህገመንግስቱ የገዥው ፓርቲ ሰነድ ብቻ ሆኖ እንዳይቀር፣ ሁሉንም ሀይሎች ያሳተፈ ህገመንግስት ማርቀቅን ያካትታል።
  • ሁለተኛው ፕሮግራማቸው በአገሪቱ ውስጥ ፀጥታ እና መረጋጋትን  በማምጣት፤ሱዳንን ከአማፂያን ሽኩቻ ነፃ ማድረግ እንደሆነ የገለፁት አልበሽር፤ለዚህ ደግሞ የአቡጃ፣ የዶሃ፣ የስርት እና ሁሉን አቀፉን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
  • ሶስተኛው ፕሮግራም የአገሪቱ ኢኮኖሚ እንዳይንኮታኮት እርምጃ መውሰድን የሚመለከት ሲሆን ለዚህም የኢኮኖሚ ማሻሻያ እንደሚደረግ አልበሽር ገልፀዋል፡፡
ሀሰን አልቱራቢ
ሀሰን አልቱራቢ

“ደቡብ ሱዳን ነፃነቷን ካወጀች በኋላ ነዳጅ መደጎማችንን እንድናቆም  በኢኮኖሚ ባለሙያዎች ስንመከር ተግባራዊ አለማድረጋችን ስህተት ነበር፡፡ በአለም ላይ የነዳጅ ዋጋ እያሻቀበ ቢመጣም  ህዝባችን ላይ ጫና እንዲፈጠር ስላልፈለግን ተግባራዊ ሳናደርገው ቀርተናል፡፡ አዲሱ የኢኮኖሚ ፓኬጅ ድሆችን አይጎዳም፤ምክንያቱም ድሆች መኪና የላቸውም፡፡ እነሱን በዘካት ቻምበር እና በደሞዝ ጭማሪ እንዳይጎዱ ማድረግ ይቻላል” ብለዋል፡፡

ሁሉም ሱዳናውያን የተሃድሶው ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ ያቀረቡት አልበሽር፤ሰላም ቅድሚያ የሚሰጠው አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል – ያለ ሰላም ፖለቲካዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ እድገት እንደሌለ በመጥቀስ፡፡ አልበሽር ይሄን ይበሉ እንጂ የተኩስ አቁም ስምምነትን በተመለከተ ትንፍሽ ያሉት ነገር የለም ተብሏል፡፡ “በሱዳን ውጤት የሌለው የፖለቲካ ሽኩቻ ማብቃት አለበት” በማለት ብቻ  ነው ጉዳዩን አድበስብሰው ያለፉት፡፡

የአልበሽር የሰሞኑ ንግግር ከቀደምት ንግግሮች የሚለየው ተቃዋሚዎችን በማካተቱ ሲሆን ይሄም በ25 ዓመት የስልጣን ዘመናቸው የመጀመሪያው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ከአስራ አራት አመት መለያያትና ተደጋጋሚ እስር በኋላ በአልበሽር ንግግር የታደሙት ሀሰን አልቱራቢ፣“ከንግግሩ የምንጠብቀውን አላገኘንም፤ስለፖለቲካ  እንቅስቃሴም ሆነ ስለሚዲያ ነፃነት ምንም አልተባለም” ሲሉ ቅሬታቸውን ሰንዝረዋል፡፡ የኡማ ፓርቲ መሪ  ሳዲቅ አልመሀዲ ግን በችኮላ አስተያየት ለመስጠት የፈለጉ አይመስሉም፡፡ “በፕሬዚዳንቱ ንግግር ላይ አስተያየት ከመስጠቴ በፊት ጉዳዩን በደንብ ማጤን ይገባኛል” ነው ያሉት፡፡ የአገሪቱን ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥምረት የሚመሩት ፋሩቅ አቡ አሊ፣ ከአልበሽር ንግግር ቀደም ብለው ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ በሰጡት መግለጫ፤“ፕሬዚዳንቱ በፖሊሲያቸው ምክንያት ለተጎዱ ወገኖች በተለይ በመስከረሙ ግጭት የሞቱትን ሰዎች አስመልክቶ ይቅርታ ሲጠይቁ መስማት እፈልጋለሁ” ብለዋል። አልበሽር ግን የተባለውን  ይቅርታ ባለፈው ሰኞ ንግግራቸው ላይ  አልጠየቁም፡፡

እንዲያም ሆኖ ግን የአልበሽር ድንገተኛ የለውጥና የህዳሴ ንግግር እንዲሁም የ“እንወያይ” ጥሪ ብዙዎችን አስገርሟል – ድንገተኛና ያልተጠበቀ በመሆኑ፡፡ አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ደግሞ ከፍርሃት የመነጨ ነው ይላሉ – የአልበሽርን የለውጥና የህዳሴ ንግግር፡፡

ሳዲቅ አልመሀዲ
ሳዲቅ አልመሀዲ

በደቡብ ሱዳን ያለው የፖለቲካ አለመረጋጋት በተለይም ከነዳጅ አቅርበት ጋር ተያይዞ በሰሜን ሱዳን ላይ አሉታዊ ጫናውን እንዳያሳርፍ በመፍራት የወሰዱት እርምጃ ነው የሚሉት ተንታኞች፤በሌላ በኩል የሚፈነዳበት ወቅት የማይታወቀው ነገር ግን አይቀሬው ህዝባዊ አመፅ ከመምጣቱ በፊት እድላቸውን ለመሞከር ሲሉ ያደረጉት ነው ብለዋል፡፡ ለዚህም በተለያዩ የአረብ አገሮች የተካሄዱና አሁንም ያልበረዱ ህዝባዊ አመፆችን በማስረጃነት ይጠቅሳሉ -ተንታኞቹ፡፡

አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ የአልበሽር አዲስ የለውጥ ጥሪ  ከአለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ጋር ያለባቸውን እሰጥ አገባ በአገር ውስጥ  ነፍጥ ከታጠቁ  ወገኖች ጋር በመደራደር ከራሳቸው ከሱዳናውያን የሚመጣውን ግፊት ለመቀነስ ያለመ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ አስተያየት ሰጪዎቹ እንዲህ ይበሉ እንጂ አልበሽር ቢያንስ በሰኞው ንግግራቸው መሳሪያ ከታጠቁ  ኃይሎች ጋር ስለሚደረገው ውይይት ምንም የሰጡት ፍንጭ የለም፡፡

የአልበሽር ንግግር ከመደረጉ በፊት የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት የተለያዩ መረጃዎችነ ለሚዲያዎች መስጠታቸውም ሌላው ትኩረት የሳበ ጉዳይ ነው፡፡ አንድ የመንግስት ባለስልጣን  ቀድመው በሰጡት አስተያየት፤ አልበሽር በንግግራቸው ሁሉን አቀፍ የሆነ የለውጥ እቅድ እንደሚያቀርቡና የሱዳንን ቀውስ ለመፍታት ሁሉንም ወገኖች ያካተተ መፍትሄ እንደሚፈለግ ሲገልፁ፤ ሌላ ባለስልጣን ለሮይተርስ  በሰጡት መግለጫ፤ አልበሽር ሁሉም ተቃዋሚ ኃይሎች የአገሪቱን ህገመንግስት እንደገና አርቅቀው መንግስትን እንዲቀላቀሉ ጥሪ ያቀርባሉ ብለው ነበር። ከአልበሽር ንግግር በኋላ የተደበላለቁ እስተያየቶች መደመጣቸውን ተከትሎ የገዢ  ፓርቲው ምክትል ሊቀመንበርና  የፓርቲ ጉዳዮች ሀላፊ ኢብራሂም ጋንዱር በሰጡት መግለጫ “በሽር ለህዝቡ ንግግራቸውን ለማቅረብ ያቀዱት ከፓርቲዎች ጋር ከተወያዩ በኋላ ነበር፤ነገር ግን ብዙ ጥርጣሬዎች እና መላምቶች ቀድመው በመናፈሳቸው ለህዝቡ ንግግር ለማድረግ ተገደዋል” ብለዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ላይ ከተሳተፉ በኋላ የንግግራቸውን ቀጣይ ክፍል እንደሚያቀርቡና ሁለተኛው ክፍል ብዙ ጉዳዮችን ዘርዘር ባለ መልኩ እንደሚያካትት ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

“የሱዳን ህዳሴ” የሚለው ሰነድም በገዢው ፓርቲ በኩል የቀረበ በመሆኑ የመንግስት ሰነድ አድርጎ መውሰድ እንደማይቻል የገለፁት ኢብራሂም፤ፓርቲያችን ለሱዳን ችግሮች የመፍትሄ አቅጣጫዎች እያቀረበ ሳይሆን ሌሎች የፖለቲካ ሀይሎችም የራሳቸውን ሀሳብ እንዲያመጡ እድል እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡

በሰኞው የአልበሽር ንግግር “ብዙዎች ተስፋ ቆርጠዋል” የሚለውን አስተያየት ኢብራሂም አይቀበሉትም፡፡  “አስተያየቱ ትክክል አይደለም፤ምክንያቱም ከአልበሽር ንግግር በኋላ የተሰራ ፈጣን ቅኝት ህዝቡ  በፕሬዚደንቱ ንግግር መርካቱን ነው የሚያሳየው” ብለዋል፡፡

በአለምአቀፍ ተቋሟት ይፋ የሚደረጉ የጥናት ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት፤ሱዳን በሙስና፣ በልማት  እና በፕሬስ ነፃነት ረገድ  ከመጨረሻዎቹ የዓለም አገራት ተርታ ትመደባለች፡፡ ፕሬዚዳንት አልበሽርም  አስራ አንድ አመቱን ካስቆጠረው የዳርፉር ጦርነት ጋር በተያያዘ በሰዎች ግድያና በዘር ማጥፋት ወንጀል በአለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት የሚፈለጉ መሪ ናቸው፡፡ ባለፈው መስከረም ወር  ከነዳጅ ዋጋ ጋር ተያይዞ በሱዳን በተፈጠረ አለመረጋጋት፣ ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች በፀጥታ ሀይሎች መገደላቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ቢገልፅም፤የአልበሽር መንግስት ቁጥሩ እጅግ የተጋነነ ነው ሲል አጣጥሎታል፡፡ (አዲስ አድማስ)

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule