• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አድዋ!

February 28, 2015 12:34 am by Editor Leave a Comment

ዋ! አድዋ ፤ ያ ሑዳዴ

መድፍና ፈንጅ ፤ በጎራዴ

ባሕር ተሻግሮ ፤ የሐበሻን ምድር

ቅኝ ሊገዛ ፤ የማን ደፋር!

አንች አድዋ ፤ የበኩር ልጅ

ላንቺ ውልደት ፤ ስንቱ ሲፈጅ

ተጸንሰሽ ፤ ከውጫሌ

ለደም መሬት ፤ ለአሞሌ

እርግዝናሽ ፤ ዘጠኝ ወሩ

ዓመታትን ፤ ማስቆጠሩ

ክፉውን ቀን ፤ ይዞ አሳሩ

ከብቱ እረግፎ ፤ ባገር ምድሩ

ሰው ሁሉ አልቆ ፤ በችጋሩ

በፋሽስት ሸር ፤ በእኩይ ግብሩ

ከብት የሚፈጅ ፤ ደዌ ረጭቶ

በምን ታርሶ ፣ በምን ለምቶ

የገበሬው ፤ ሀብት ጠፍቶ

አከርካሪው ፤ ተመትቶ

የሚቀመስ ፤ እህል ታጥቶ

ረሀቡ ፤ ሕዝቡን በልቶ

ምኑ ተብሎ ፤ ስንቱን ነግሮ

የግፍ ግፉ ፤ ተዘርዝሮ

ዝም ይሻላል ፤ ምን ተቆጥሮ

በክፉው ቀን ፤ ራብ ደክሞ

ያለቀ ሕዝብ ፤ በአዋጅ ተሞ

በዚያ ድቀት ፤ ተጎድቶ

አፈር ልሶ ፤ ግድ ተነሥቶ

አይቀር ነገር ፤ የሀገር ጥሪ

ነፍሱ የሷ ፤ እሱ አኗሪ

ጉልበት ሆኖት ፤ የሀገር ፍቅሩ

አስቆጥቶት ፤ መደፈሩ

ገሰገሰ ፤ ወደ አድዋ

ጠላት ሊግት ፤ የሞት ጽዋ

አድዋ ላይ ፤ ከግንባሩ

ሊሞሻለቅ ፤ ሲተም ጠሩ

እንደ ሙላት ፤ ደራሹ ጎርፍ

ሲያስገመግም ፤ ጠላት ሊቀስፍ

ከተፍ ሲል ፤ ፊት ለፊቱ

ጥሊያን ራደ ፤ ልብ አጥቶ

ባለ የሌለ ፤ መሣሪያ አጉል

እያስጓራ ፤ ሲከላከል

በመድፍ አረር ፤ በመትረየስ

ግማሽ ሲቀር ፤ ሲሠዋ ነፍስ

ጠጋ ሲባል ፤ ወደ ምሽግ

ሌላ አሳር ፤ ምን ይደረግ?

በስል ችንካር ፤ በውጋቱ

በጠርሙስ ጦር ፤ በስለቱ

ምሽግ ማዶ ፤ በተከለው

አርበኛውን ፤ እንዲያስቀረው

ጠርሙስ አልፎ ፤ የፈንጅ ንጣፍ

ፋኖ የሚፈጅ ፤ በነፍስ ወከፍ

ያ ባዶ እግር ፤ ቢቀረደድ

ቢሸረከት ፤ ቢጎራረድ

ማን ተሰምቶት ፤ ለማን ታውቆ?

በፈንጅውም  ፤ ረግፎ አልቆ

ሊነሣ ይሻል ፤ ሞቶም ወድቆ

በወደቀው ፤ ተረማምዶ

ምሽግ ሰብሮ ፤ ጥሶ ንዶ

በጠላት ላይ ፤ መዓት ወርዶ

ቆርጦ ሲጥል ፤ አንገት ጎርዶ

በፉከራ ፤ ቀልቶ አጭዶ

ሲፈጅ ሲማርክ ፤ ቆልቶ አሳዶ

ብቻ በሀገር ፤ በሕዝብ ፍቅር

በሚፋጀው ፤ እንደ ገሞር፡፡

አንች የረፋድ ፤ የድል ፀሐይ

የወጣሽው ፤ አድዋ ላይ

ከአባትሽ ፤ ከምኒልክ

ድባቅ መትቶ ፤ ካገባው ልክ

ከጣይቱ ፤ ከእናት ኩሩ

ፋኖዎቹ ፤ እያጋፈሩ

አድዋ ላይ ፤ ከአፈሩ

በቅዱሱ ፤ ጊዮርጊስ ለት

ተራድቶሽ ፤ ተርፈሽ ከሞት

ሰዓቱ ሲደርስ ፤ መወለጃሽ

በጭንቅ ምጥ ፤ የተወለድሽ

በሰው አጥንት ፤ በሰው ልጅ ደም

የታረስሽው ፤ የዓለም ሰላም

የሐበሻ ዘውድ ፤ የድል ማማ

በአጥንት ዕዳ ፤ በደም ጉማ

ምታስከፍይ ፤ ቃል ሲሰማ

ያችን ገልቱ ፤ ከንቱ ሮማ፡፡

አድዋ ቅኔ ፤ አድዋ ዜማ

የምትማርክ ፤ ምትስማማ

ለሰው ልጅ ልብ ፤ ያላት ግርማ

የአውሬን ልብ ፤ ምታደማ

በአፍታ ፍልሚያ ፤ ፈጣን ሽኝት

ወዲያው ብልት ፤ እዚያው ጥጥት

በአርበኛ ወግ ፤ በፋኖ ደንብ

ሳይገመት ፤ ሳይታሰብ፡፡

ነጭ በጥቁር ፤ በግፍ ገኖ

በጨካኝ ክንድ ፤ ይዞ አፍኖ

ጥቁሩ ሲኖር ፤ ተኮንኖ

መገልገያ ፤ ዕቃ ሆኖ

አሜን ወዴት ፤ አለሁ ብሎ

አንገት ሰብሮ ፤ ተገልሎ

በምድሪቱ ፤ በመላ ዓለም

በግፍ ሲኖር ፤ አጥቶ ሰላም

ለነጭ ተድላ ፤ ጥሮ ማስኖ

እሱ እንደሚያንስ ፤ ከልቡ አምኖ

ቅስም ሐሞቱ ፤ ነኩቶ ፈሶ

መራር ሐዘን ፤ ልቡ ውስጥ ነግሦ

ሲኖር ዘወትር ፤ ቀንበር አዝሎ

አድዋ ላይ ፤ የድሉ አውሎ

አሽቀንጥሮ ፤ ሸክሙን ጥሎ

ነጩን እባብ ፤ ላይድን ገሎ

አነሣለት ፤ ከስር ነቅሎ

አስበርግጎ ፤ አስደንብሮ

ፈነቃቅሎ ፤ ጥልቅ ሰርስሮ፡፡

እናም ዓለም ፤ ተገደደ

ውዳቂ ሐሳብ ፤ በግድ ካደ

አዲስ ታሪክ ፤ ተሰነደ

የተጠላው ፤ ተወደደ

ሰው መሆኑን ፤ የአዳም ዘር

ከነጭ ቢጫ ፤ ከቀይ ፍጡር

እንደማያንስ ፤ ምን ቢጠቁር

አረጋግጦ ፤ ቆመ በክብር

እድሜ ለዚያች ፤ የድል ፀሐይ

ለበራችው ፤ አድዋ ላይ

የባርነት ፤ ሰንሰለቱን

በጣጠሰ ፤ እግር ብረቱን

ተቀዳጀ ፤ ነጻነቱን

ቀበረለት ፤ ባርነቱን

የሀገሩ ፤ የመብቱ

ራሱ ሆነ ፤ ባለቤቱ

ዕድሜ ለዚያች ፤ የድል ፀሐይ

ለበራችው ፤ አድዋ ላይ

የምዕት ዓመታት ፤ ጣር ጨለማ

ተወገደ ፤ ድል ተሰማ

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ያች ፀሐይ ፤ የድል ጮራ

ደማቅ ጸዳል ፤ የገድል አውራ

የከበረች ፤ ስጦታ ናት

ምንም ነገር ፤ የማይተካት

ከሐበሻ ሕዝብ ፤ ለጥቁር ዘር

ለተገፋው ፤ ለበላ አሳር፡፡

የካቲት 19 2007ዓ.ም.

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule