• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአክሰስ ሪል ስቴት ደንበኞች አቶ ኤርሚያስን በጋራ ለመፋረድ ተስማሙ

September 5, 2013 06:04 am by Editor Leave a Comment

በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ከ2,500 በላይ ደንበኞች የአክሰስ ሪል ስቴት መሥራች፣ ሥራ አስኪያጅና የቦርድ ሊቀመንበር የነበሩትን አቶ ኤርሚያስ አመልጋን፣ በጋራና በአንድ አቋም ሆነው ለመፋረድ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ባደረጉት ስብሰባ ተስማሙ፡፡

ቤት ገንብተው ሊያስረክቧቸው ባደረጉት ስምምነት ሩብ፣ ግማሽና ሙሉ ክፍያ መፈጸማቸውን የሚናገሩት ደንበኞች፣ አቶ ኤርሚያስን በጋራ ለመፋረድ የተስማሙት፣ ገንዘባቸውን ለማስመለስ በተናጠል ወደ ፍርድ ቤት መሄዳቸውንና የሪል ስቴቱ ንብረት ነው በሚል ንብረት ለማሳገድ ወይም የኪሳራ ውሳኔ ለማስወሰን መንቀሳቀሳቸውን በመተው፣ አቋማቸውን አንድ በማድረግና በመስማማት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የተወሰኑት በተወካዮቻቸው፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ራሳቸው በስብሰባው ላይ በመገኘት በቅርቡ ከተሰየመው ቦርድና ቤት ገዢዎችን በመወከል የተቋቋመው ዓብይ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርት ካዳመጡ በኋላ፣ አቶ ኤርሚያስ የሠሩት ሥራ ውስብስብና በእነሱ መቼም ቢሆን ሊፈታ እንደማይችል በመተማመን መንግሥት ጣልቃ እንዲገባላቸው በጋራ ለመጠየቅ ተስማምተዋል፡፡

በጠቅላላ ስብሰባው ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ጨምሮ አሥር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች እንዲገኙላቸው ጠርተው እንደነበር የገለጹት ኮሚቴዎቹ፣ በስብሰባው ላይ የተገኙላቸው የፍትሕ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካዮች ብቻ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ተወካዮቹም የተበደሉትን ወገኖች ስሜት በመመልከት በጉዳዩ መንግሥት ጣልቃ እንደሚገባበት ቃል እንደገቡላቸው አክለዋል፡፡

አቶ ኤርሚያስ እዚህ ባሉ ወኪላቸው አማካይነት እንደገለጹላቸው፣ በደረቅ ቼክ ምክንያት ተመሥርተውባቸው ከነበሩት አራት ክሶች ሦስቱን አዘግተዋል፡፡ የሚቀራቸው አንድ ክስ ነው፡፡ ይኼንንም ለማዘጋት አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚፈጽሙና የሠሩት ሥራ ወንጀል መሆኑን ማመናቸውን፣ ቤት ገዢዎቹ ተባብረዋቸውና የመንግሥት አካላትን ጠይቀውላቸው ምሕረት ካደረጉላቸው፣ ወደ አገር ቤት ተመልሰው የችግሩ መፍትሔ አፈላላጊ ሊሆኑ እንደሚችሉ መናገራቸውን ኮሚቴው ገልጿል፡፡

የአክሰስ ደንበኞች እንደሚሉት በአሁኑ ጊዜ ዓለም አንድ መንደር በመሆኗ፣ እንኳን ግለሰብ ማንም ቢሆን በአንድ አገር ውስጥ ወንጀል ፈጽሞ በሌላኛው አገር የሚደበቅበት ጊዜ አይደለም፡፡ በመሆኑም አቶ ኤርሚያስ ይኼንን ተገንዝበው በመመለስ የመፍትሔው አካል መሆን አለባቸው ይላሉ፡፡ የማይመጡ ከሆነ መንግሥት ወይም የፌዴራል ፖሊስ በኢንተርፖል አማካይነት እንደሚያስመጣቸው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

እያንዳንዱ ቤት ገዥ በተለያየ አገር ተሰዶ ያጠራቀመውን ጥሪት ለልጆቹ በማሰብና በአገሩ ተመልሶ ለመኖር ካለው ጉጉት የተነሳ ክፍያ በመፈጸሙ፣ ችግሩ መከሰቱን ሲሰማ ሁሉም በየፊናው ወደ ፍርድ ቤት ማምራቱን ኮሚቴዎቹ ገልጸዋል፡፡ አቶ ኤርሚያስ የፈጸሙት ድርጊት ውስብስብ ማለትም አንድን ንብረት በአራትና በአምስት ቦታ አያይዘውት ስለሄዱ፣ ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሳይሆን ለሁሉም ተጐጂ ዜጐች መፍትሔ ሊያስገኝ የሚችለው መንግሥት ጣልቃ በመግባት አስተዳደራዊ መፍትሔ ሲሰጥ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም ሁሉም ተጐጂዎች በየግላቸው ወደ ፍርድ ቤት በመሄድ የኪሳራ ውሳኔ ለማስወሰን መሯሯጣቸውን ትተው፣ በአንድ አቋም መንግሥትን እየተማፀኑ መሆናቸውንም ኮሚቴው አስታውቋል፡፡

መንግሥትና የኢትዮጵያ ሕዝብ በደላቸውን እንዲሰማላቸው ሰላማዊ ሠልፍ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል፡፡ እስካሁን ድረስ ያለው የመንግሥት ምላሽም አስደሳችና ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule