• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአክሰስ ሪል ስቴት ደንበኞች አቶ ኤርሚያስን በጋራ ለመፋረድ ተስማሙ

September 5, 2013 06:04 am by Editor Leave a Comment

በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ከ2,500 በላይ ደንበኞች የአክሰስ ሪል ስቴት መሥራች፣ ሥራ አስኪያጅና የቦርድ ሊቀመንበር የነበሩትን አቶ ኤርሚያስ አመልጋን፣ በጋራና በአንድ አቋም ሆነው ለመፋረድ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ባደረጉት ስብሰባ ተስማሙ፡፡

ቤት ገንብተው ሊያስረክቧቸው ባደረጉት ስምምነት ሩብ፣ ግማሽና ሙሉ ክፍያ መፈጸማቸውን የሚናገሩት ደንበኞች፣ አቶ ኤርሚያስን በጋራ ለመፋረድ የተስማሙት፣ ገንዘባቸውን ለማስመለስ በተናጠል ወደ ፍርድ ቤት መሄዳቸውንና የሪል ስቴቱ ንብረት ነው በሚል ንብረት ለማሳገድ ወይም የኪሳራ ውሳኔ ለማስወሰን መንቀሳቀሳቸውን በመተው፣ አቋማቸውን አንድ በማድረግና በመስማማት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የተወሰኑት በተወካዮቻቸው፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ራሳቸው በስብሰባው ላይ በመገኘት በቅርቡ ከተሰየመው ቦርድና ቤት ገዢዎችን በመወከል የተቋቋመው ዓብይ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርት ካዳመጡ በኋላ፣ አቶ ኤርሚያስ የሠሩት ሥራ ውስብስብና በእነሱ መቼም ቢሆን ሊፈታ እንደማይችል በመተማመን መንግሥት ጣልቃ እንዲገባላቸው በጋራ ለመጠየቅ ተስማምተዋል፡፡

በጠቅላላ ስብሰባው ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ጨምሮ አሥር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች እንዲገኙላቸው ጠርተው እንደነበር የገለጹት ኮሚቴዎቹ፣ በስብሰባው ላይ የተገኙላቸው የፍትሕ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካዮች ብቻ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ተወካዮቹም የተበደሉትን ወገኖች ስሜት በመመልከት በጉዳዩ መንግሥት ጣልቃ እንደሚገባበት ቃል እንደገቡላቸው አክለዋል፡፡

አቶ ኤርሚያስ እዚህ ባሉ ወኪላቸው አማካይነት እንደገለጹላቸው፣ በደረቅ ቼክ ምክንያት ተመሥርተውባቸው ከነበሩት አራት ክሶች ሦስቱን አዘግተዋል፡፡ የሚቀራቸው አንድ ክስ ነው፡፡ ይኼንንም ለማዘጋት አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚፈጽሙና የሠሩት ሥራ ወንጀል መሆኑን ማመናቸውን፣ ቤት ገዢዎቹ ተባብረዋቸውና የመንግሥት አካላትን ጠይቀውላቸው ምሕረት ካደረጉላቸው፣ ወደ አገር ቤት ተመልሰው የችግሩ መፍትሔ አፈላላጊ ሊሆኑ እንደሚችሉ መናገራቸውን ኮሚቴው ገልጿል፡፡

የአክሰስ ደንበኞች እንደሚሉት በአሁኑ ጊዜ ዓለም አንድ መንደር በመሆኗ፣ እንኳን ግለሰብ ማንም ቢሆን በአንድ አገር ውስጥ ወንጀል ፈጽሞ በሌላኛው አገር የሚደበቅበት ጊዜ አይደለም፡፡ በመሆኑም አቶ ኤርሚያስ ይኼንን ተገንዝበው በመመለስ የመፍትሔው አካል መሆን አለባቸው ይላሉ፡፡ የማይመጡ ከሆነ መንግሥት ወይም የፌዴራል ፖሊስ በኢንተርፖል አማካይነት እንደሚያስመጣቸው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

እያንዳንዱ ቤት ገዥ በተለያየ አገር ተሰዶ ያጠራቀመውን ጥሪት ለልጆቹ በማሰብና በአገሩ ተመልሶ ለመኖር ካለው ጉጉት የተነሳ ክፍያ በመፈጸሙ፣ ችግሩ መከሰቱን ሲሰማ ሁሉም በየፊናው ወደ ፍርድ ቤት ማምራቱን ኮሚቴዎቹ ገልጸዋል፡፡ አቶ ኤርሚያስ የፈጸሙት ድርጊት ውስብስብ ማለትም አንድን ንብረት በአራትና በአምስት ቦታ አያይዘውት ስለሄዱ፣ ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሳይሆን ለሁሉም ተጐጂ ዜጐች መፍትሔ ሊያስገኝ የሚችለው መንግሥት ጣልቃ በመግባት አስተዳደራዊ መፍትሔ ሲሰጥ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም ሁሉም ተጐጂዎች በየግላቸው ወደ ፍርድ ቤት በመሄድ የኪሳራ ውሳኔ ለማስወሰን መሯሯጣቸውን ትተው፣ በአንድ አቋም መንግሥትን እየተማፀኑ መሆናቸውንም ኮሚቴው አስታውቋል፡፡

መንግሥትና የኢትዮጵያ ሕዝብ በደላቸውን እንዲሰማላቸው ሰላማዊ ሠልፍ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል፡፡ እስካሁን ድረስ ያለው የመንግሥት ምላሽም አስደሳችና ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule