• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአክሰስ ሪል ስቴት ደንበኞች አቶ ኤርሚያስን በጋራ ለመፋረድ ተስማሙ

September 5, 2013 06:04 am by Editor Leave a Comment

በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ከ2,500 በላይ ደንበኞች የአክሰስ ሪል ስቴት መሥራች፣ ሥራ አስኪያጅና የቦርድ ሊቀመንበር የነበሩትን አቶ ኤርሚያስ አመልጋን፣ በጋራና በአንድ አቋም ሆነው ለመፋረድ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ባደረጉት ስብሰባ ተስማሙ፡፡

ቤት ገንብተው ሊያስረክቧቸው ባደረጉት ስምምነት ሩብ፣ ግማሽና ሙሉ ክፍያ መፈጸማቸውን የሚናገሩት ደንበኞች፣ አቶ ኤርሚያስን በጋራ ለመፋረድ የተስማሙት፣ ገንዘባቸውን ለማስመለስ በተናጠል ወደ ፍርድ ቤት መሄዳቸውንና የሪል ስቴቱ ንብረት ነው በሚል ንብረት ለማሳገድ ወይም የኪሳራ ውሳኔ ለማስወሰን መንቀሳቀሳቸውን በመተው፣ አቋማቸውን አንድ በማድረግና በመስማማት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የተወሰኑት በተወካዮቻቸው፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ራሳቸው በስብሰባው ላይ በመገኘት በቅርቡ ከተሰየመው ቦርድና ቤት ገዢዎችን በመወከል የተቋቋመው ዓብይ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርት ካዳመጡ በኋላ፣ አቶ ኤርሚያስ የሠሩት ሥራ ውስብስብና በእነሱ መቼም ቢሆን ሊፈታ እንደማይችል በመተማመን መንግሥት ጣልቃ እንዲገባላቸው በጋራ ለመጠየቅ ተስማምተዋል፡፡

በጠቅላላ ስብሰባው ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ጨምሮ አሥር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች እንዲገኙላቸው ጠርተው እንደነበር የገለጹት ኮሚቴዎቹ፣ በስብሰባው ላይ የተገኙላቸው የፍትሕ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካዮች ብቻ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ተወካዮቹም የተበደሉትን ወገኖች ስሜት በመመልከት በጉዳዩ መንግሥት ጣልቃ እንደሚገባበት ቃል እንደገቡላቸው አክለዋል፡፡

አቶ ኤርሚያስ እዚህ ባሉ ወኪላቸው አማካይነት እንደገለጹላቸው፣ በደረቅ ቼክ ምክንያት ተመሥርተውባቸው ከነበሩት አራት ክሶች ሦስቱን አዘግተዋል፡፡ የሚቀራቸው አንድ ክስ ነው፡፡ ይኼንንም ለማዘጋት አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚፈጽሙና የሠሩት ሥራ ወንጀል መሆኑን ማመናቸውን፣ ቤት ገዢዎቹ ተባብረዋቸውና የመንግሥት አካላትን ጠይቀውላቸው ምሕረት ካደረጉላቸው፣ ወደ አገር ቤት ተመልሰው የችግሩ መፍትሔ አፈላላጊ ሊሆኑ እንደሚችሉ መናገራቸውን ኮሚቴው ገልጿል፡፡

የአክሰስ ደንበኞች እንደሚሉት በአሁኑ ጊዜ ዓለም አንድ መንደር በመሆኗ፣ እንኳን ግለሰብ ማንም ቢሆን በአንድ አገር ውስጥ ወንጀል ፈጽሞ በሌላኛው አገር የሚደበቅበት ጊዜ አይደለም፡፡ በመሆኑም አቶ ኤርሚያስ ይኼንን ተገንዝበው በመመለስ የመፍትሔው አካል መሆን አለባቸው ይላሉ፡፡ የማይመጡ ከሆነ መንግሥት ወይም የፌዴራል ፖሊስ በኢንተርፖል አማካይነት እንደሚያስመጣቸው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

እያንዳንዱ ቤት ገዥ በተለያየ አገር ተሰዶ ያጠራቀመውን ጥሪት ለልጆቹ በማሰብና በአገሩ ተመልሶ ለመኖር ካለው ጉጉት የተነሳ ክፍያ በመፈጸሙ፣ ችግሩ መከሰቱን ሲሰማ ሁሉም በየፊናው ወደ ፍርድ ቤት ማምራቱን ኮሚቴዎቹ ገልጸዋል፡፡ አቶ ኤርሚያስ የፈጸሙት ድርጊት ውስብስብ ማለትም አንድን ንብረት በአራትና በአምስት ቦታ አያይዘውት ስለሄዱ፣ ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሳይሆን ለሁሉም ተጐጂ ዜጐች መፍትሔ ሊያስገኝ የሚችለው መንግሥት ጣልቃ በመግባት አስተዳደራዊ መፍትሔ ሲሰጥ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም ሁሉም ተጐጂዎች በየግላቸው ወደ ፍርድ ቤት በመሄድ የኪሳራ ውሳኔ ለማስወሰን መሯሯጣቸውን ትተው፣ በአንድ አቋም መንግሥትን እየተማፀኑ መሆናቸውንም ኮሚቴው አስታውቋል፡፡

መንግሥትና የኢትዮጵያ ሕዝብ በደላቸውን እንዲሰማላቸው ሰላማዊ ሠልፍ እንደሚያደርጉም ተናግረዋል፡፡ እስካሁን ድረስ ያለው የመንግሥት ምላሽም አስደሳችና ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule