• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስለ ችጋር

December 1, 2015 11:46 am by Editor Leave a Comment

• ችጋር ምንድን ነው? ሰፊ ቦታንና ብዙ ሕዝብን የሚሸፍን፣ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ፣ ምንም የሚላስ የሚቀመስ ጠፍቶ እንስሳት (ሰውንም ጨምሮ) ዕለት በዕለት የራሳቸውን አካል እስኪያልቅ ድረስ “እየበሉ” በመጨረሻም የሚሞቱበት ሁኔታ ነው፤ ረሀብ አካል ሲዳከም አካልን ለመገንባት የሚደረግ ጥሪ ነው፡፡

• ችጋር የሚያጠቃው ማንን ነው? ትልቁና ዋናው የችጋር እንቆቅልሽ የዚህ ጥያቄ መልስ ነው፤ አብዛኛውን ጊዜ ችጋር የሚያጠቃው ከገበያ ጋር የማይገናኙትን ምግብ አምራቾችን ገበሬዎችን፣ በተለይም እያመረቱ ከእጅ ወዳፍ ብቻ የሚኖሩትን ነው፤ እነዚህ ገበሬዎች የገጠሩ ሕዝብ፣ ማለትም የአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ የመጨረሻ ደሀዎች ናቸው፤ ኑሮአቸው ሁልጊዜም በችጋር አፋፍ ላይ ነው፡፡

• ችጋር ከተፈጥሮ ጋር ያለው ግንኙነት እንዴት ነው? ከላይ እንደተባለው በችጋር ላይ የሚወድቁት ገበሬዎች ከገበያ ጋር እምብዛም ግንኙነት የሌላቸው ናቸው፤ ይህም እምብዛም ጥሬ ገንዘብ የላቸውም ማለት ነው፤ ስለዚህ በገበያ ላይ እህል ቢኖርም የመግዛት አቅም የላቸውም፤ ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ግንኙነት የጠበቀ ነው፤ ምርታቸው መቶ በመቶ በተፈጥሮ ችሮታ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ስለዚህም ተፈጥሮ በትንሹ እንኳን ፊቱን ካዞረ ምርቱ ያንሳል ወይም ጭራሹኑ ይጠፋል፡፡

• ተፈጥሮ ፊቱን የሚያዞረው እንዴት ነው? ብዙ መንገዶች አሉ፤የእርሻ ምርት በተፈጥሮ ሀብቶች ላይ የተመሠረተ ነው፤ መሬት (አፈር)፣ ውሀ፣ የዓየር ጠባይና ጉልበት፣ ተፈጥሮ በነዚህ ላይ ፊቱን ማዞሩ የሚገለጥባቸው ዋና ዋናዎቹ፡-

• ዝናብ ወይ ይበዛል ወይ ያንሳል፤
• የዝናቡ ወቅት ይቀድማል፤ ወይም ይዘገያል፤
• ምርቱን ውርጭ ይመታዋል፤
• ምርቱን ተምች ይመታዋል፤
• ምርቱን በሽታ ይበላዋል፤
• ምርቱን ከባድ ጎርፍ ወይም ከባድ በረዶ ያጠቃዋል፤
• ሌላም፣ ሌላም፣


• ተፈጥሮ በአንድ ምክንያት ፊቱን ሲያዞር ለወትሮው በችጋር አፋፍ ላይ የነበሩት ደሀ ገበሬዎቸው ወደችጋሩ ገደል መግባት ይጀምራሉ፤

• ችጋር ሕዝብን በጅምላ የሚጨፈጭፍበት ጊዜ ከስድስት እስከስምንት ወራት ይፈጃል፤ የተፈጥሮ ችግር መኖሩ ከታወቀ ጀምሮ ከስድስት አስከስምንት ወሮች ሰዎች አካላቸውን “እየበሉ” ይቆያሉ፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ ተከሰተ የተባለው ድርቅ ሰዎችን በችጋር መረፍረፍ የሚጀምረው በሚያዝያና በመጋቢት ነው፤ ገበሬዎቹ ከአሁን ጀምሮ እስከ መጋቢት ምንም ሰፊና ትልቅ ዘላቂ እርዳታ ካላገኙ በመጋቢትና በሚያዝያ ሰው እንደቅጠል የሚረግፍበት ጊዜ ይሆናል፤

• ልብ በሉ የመጀመሪያው የተፈጥሮ አደጋ ሲከሰት ወይ የተዘራው ጠፍቶአል፤ ወይ ቀንሶአል፤ ወይ ተበላሽቶል፤ ስለዚህም ገና በክረምት ወራት አዝመራ እንደማይኖር ይታወቃል፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አስከመጋቢትና ሚያዝያ ቢያንስ ስምንት ወራት አሉ፤ በዚህ ጊዜ ሰዎች ወደችጋሩ ገደል እንዳይገቡ የሚያግደው፡-

ሀ) እያንዳንዱ ሰው ወይም ቤተሰብ ለክፉ ቀን ለመጠባበቂያ የሚሆን እህል በጎተራ ለምን አያስቀምጥም?
ለ) ለክፉ ቀን ጥሬ ገንዘብ በባንከ ለማን አያስቀምጥም?
ሐ) አገዛዙ የእርሻ ምርት የሚቀንስ ወይም የሚጠፋ መሆኑ ከታወቀ ጀምሮ ተጠቂ ለሚሆነው ሕዝብ በቂ ምግብ ለምን አያዘጋጅም? ሕዝቡ ራሱ ለችጋር አደጋ እንዳይጋለጥ በየወረዳው “የእህል ባንክ” ለምን አያቋቁምም?
መ) ከእጅ ወደአፍ የማያልፍ ምርት የሚያመርቱ (ሁሌም ለችጋር የሚጋለጡት) ገበሬዎች ለምን ግብርና ሌሎችም መዋጮዎች እንዲከፍሉ ይገደዳሉ? እንዲያውም በአንጻሩ አገዛዙ እነዚህ ለአደጋ የተጋለጡ ገበሬዎች ማኅበራዊና መዋዕለ ንዋያዊ አቅማቸው አቅማቸው እንዲዳብርና እንዲበረታ የማያደርገው ለምንድን ነው? ደሀነታቸውንና ደካማነታቸውን የሚፈልገው ለምንድን ነው?
ሌሎች፣ ሌሎች ጥያቄዎችም …


• የመጨረሻውና ዋናው ነጥብ ማናቸውም ዓይነት የተፈጥሮ አደጋ ከችጋር ጋር በቀጥታ የተያያዘ አለመሆኑ ነው፤ ከአደጋው በፊት ለማኅበረሰቡ የኑሮና የአስተዳደር ግንኙነት የተገነባው ሕጋዊ የነጻነትና የልማት ሥርዓት መኖር ወይም አለመኖር በአንድ በኩል፣ አደጋውን ተከትሎ እያንዳንዱ ግለሰብ በተናጠል፣ ማኅበረሰቡ በአጠቃላይ ያደረጉትን ወይም ሊያደርጉት የሚገባውን አብረን ስንመለከተው በተፈጥሮ አደጋውና በችጋር መሀከል ያለው ረጅም የጊዜ ርቀት ችጋርን የአገዛዝ ውላጅ ያደርገዋል፤

• ስለዚህም ለልማትም ሆነ የተፈጥሮ አደጋን ለመቋቋም ግለሰቡ በሕጋዊ ሥርዓት ስር በሙሉ ነጻነት የማይኖር ከሆነ ከችጋር የሚወጣበት መንገድ አያገኝም፤

• ሁላችንም በየቀኑ የሚያጋጥመን ረሀብና ለብዙ ወራት ቆይቶ ሥጋን ጨርሶና አጥንትን ፍቆ ለሞት የሚዳርገው ችጋር አንድ አይደሉም፤

• ድርቅ የሚባለው የተፈጥሮ አደጋና በሰው ልጆች ቸልተኛነት የሚከሰተው ችጋር አንድ አይደሉም፤ ሁለቱን አንድ ለማድረግ የሚሞከረው ኃላፊነትን ለመሸሽ ነው፡፡

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)
ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ኅዳር 2008
Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule