• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስለ ችጋር

December 1, 2015 11:46 am by Editor Leave a Comment

• ችጋር ምንድን ነው? ሰፊ ቦታንና ብዙ ሕዝብን የሚሸፍን፣ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ፣ ምንም የሚላስ የሚቀመስ ጠፍቶ እንስሳት (ሰውንም ጨምሮ) ዕለት በዕለት የራሳቸውን አካል እስኪያልቅ ድረስ “እየበሉ” በመጨረሻም የሚሞቱበት ሁኔታ ነው፤ ረሀብ አካል ሲዳከም አካልን ለመገንባት የሚደረግ ጥሪ ነው፡፡

• ችጋር የሚያጠቃው ማንን ነው? ትልቁና ዋናው የችጋር እንቆቅልሽ የዚህ ጥያቄ መልስ ነው፤ አብዛኛውን ጊዜ ችጋር የሚያጠቃው ከገበያ ጋር የማይገናኙትን ምግብ አምራቾችን ገበሬዎችን፣ በተለይም እያመረቱ ከእጅ ወዳፍ ብቻ የሚኖሩትን ነው፤ እነዚህ ገበሬዎች የገጠሩ ሕዝብ፣ ማለትም የአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ የመጨረሻ ደሀዎች ናቸው፤ ኑሮአቸው ሁልጊዜም በችጋር አፋፍ ላይ ነው፡፡

• ችጋር ከተፈጥሮ ጋር ያለው ግንኙነት እንዴት ነው? ከላይ እንደተባለው በችጋር ላይ የሚወድቁት ገበሬዎች ከገበያ ጋር እምብዛም ግንኙነት የሌላቸው ናቸው፤ ይህም እምብዛም ጥሬ ገንዘብ የላቸውም ማለት ነው፤ ስለዚህ በገበያ ላይ እህል ቢኖርም የመግዛት አቅም የላቸውም፤ ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ግንኙነት የጠበቀ ነው፤ ምርታቸው መቶ በመቶ በተፈጥሮ ችሮታ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ስለዚህም ተፈጥሮ በትንሹ እንኳን ፊቱን ካዞረ ምርቱ ያንሳል ወይም ጭራሹኑ ይጠፋል፡፡

• ተፈጥሮ ፊቱን የሚያዞረው እንዴት ነው? ብዙ መንገዶች አሉ፤የእርሻ ምርት በተፈጥሮ ሀብቶች ላይ የተመሠረተ ነው፤ መሬት (አፈር)፣ ውሀ፣ የዓየር ጠባይና ጉልበት፣ ተፈጥሮ በነዚህ ላይ ፊቱን ማዞሩ የሚገለጥባቸው ዋና ዋናዎቹ፡-

• ዝናብ ወይ ይበዛል ወይ ያንሳል፤
• የዝናቡ ወቅት ይቀድማል፤ ወይም ይዘገያል፤
• ምርቱን ውርጭ ይመታዋል፤
• ምርቱን ተምች ይመታዋል፤
• ምርቱን በሽታ ይበላዋል፤
• ምርቱን ከባድ ጎርፍ ወይም ከባድ በረዶ ያጠቃዋል፤
• ሌላም፣ ሌላም፣


• ተፈጥሮ በአንድ ምክንያት ፊቱን ሲያዞር ለወትሮው በችጋር አፋፍ ላይ የነበሩት ደሀ ገበሬዎቸው ወደችጋሩ ገደል መግባት ይጀምራሉ፤

• ችጋር ሕዝብን በጅምላ የሚጨፈጭፍበት ጊዜ ከስድስት እስከስምንት ወራት ይፈጃል፤ የተፈጥሮ ችግር መኖሩ ከታወቀ ጀምሮ ከስድስት አስከስምንት ወሮች ሰዎች አካላቸውን “እየበሉ” ይቆያሉ፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ ተከሰተ የተባለው ድርቅ ሰዎችን በችጋር መረፍረፍ የሚጀምረው በሚያዝያና በመጋቢት ነው፤ ገበሬዎቹ ከአሁን ጀምሮ እስከ መጋቢት ምንም ሰፊና ትልቅ ዘላቂ እርዳታ ካላገኙ በመጋቢትና በሚያዝያ ሰው እንደቅጠል የሚረግፍበት ጊዜ ይሆናል፤

• ልብ በሉ የመጀመሪያው የተፈጥሮ አደጋ ሲከሰት ወይ የተዘራው ጠፍቶአል፤ ወይ ቀንሶአል፤ ወይ ተበላሽቶል፤ ስለዚህም ገና በክረምት ወራት አዝመራ እንደማይኖር ይታወቃል፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አስከመጋቢትና ሚያዝያ ቢያንስ ስምንት ወራት አሉ፤ በዚህ ጊዜ ሰዎች ወደችጋሩ ገደል እንዳይገቡ የሚያግደው፡-

ሀ) እያንዳንዱ ሰው ወይም ቤተሰብ ለክፉ ቀን ለመጠባበቂያ የሚሆን እህል በጎተራ ለምን አያስቀምጥም?
ለ) ለክፉ ቀን ጥሬ ገንዘብ በባንከ ለማን አያስቀምጥም?
ሐ) አገዛዙ የእርሻ ምርት የሚቀንስ ወይም የሚጠፋ መሆኑ ከታወቀ ጀምሮ ተጠቂ ለሚሆነው ሕዝብ በቂ ምግብ ለምን አያዘጋጅም? ሕዝቡ ራሱ ለችጋር አደጋ እንዳይጋለጥ በየወረዳው “የእህል ባንክ” ለምን አያቋቁምም?
መ) ከእጅ ወደአፍ የማያልፍ ምርት የሚያመርቱ (ሁሌም ለችጋር የሚጋለጡት) ገበሬዎች ለምን ግብርና ሌሎችም መዋጮዎች እንዲከፍሉ ይገደዳሉ? እንዲያውም በአንጻሩ አገዛዙ እነዚህ ለአደጋ የተጋለጡ ገበሬዎች ማኅበራዊና መዋዕለ ንዋያዊ አቅማቸው አቅማቸው እንዲዳብርና እንዲበረታ የማያደርገው ለምንድን ነው? ደሀነታቸውንና ደካማነታቸውን የሚፈልገው ለምንድን ነው?
ሌሎች፣ ሌሎች ጥያቄዎችም …


• የመጨረሻውና ዋናው ነጥብ ማናቸውም ዓይነት የተፈጥሮ አደጋ ከችጋር ጋር በቀጥታ የተያያዘ አለመሆኑ ነው፤ ከአደጋው በፊት ለማኅበረሰቡ የኑሮና የአስተዳደር ግንኙነት የተገነባው ሕጋዊ የነጻነትና የልማት ሥርዓት መኖር ወይም አለመኖር በአንድ በኩል፣ አደጋውን ተከትሎ እያንዳንዱ ግለሰብ በተናጠል፣ ማኅበረሰቡ በአጠቃላይ ያደረጉትን ወይም ሊያደርጉት የሚገባውን አብረን ስንመለከተው በተፈጥሮ አደጋውና በችጋር መሀከል ያለው ረጅም የጊዜ ርቀት ችጋርን የአገዛዝ ውላጅ ያደርገዋል፤

• ስለዚህም ለልማትም ሆነ የተፈጥሮ አደጋን ለመቋቋም ግለሰቡ በሕጋዊ ሥርዓት ስር በሙሉ ነጻነት የማይኖር ከሆነ ከችጋር የሚወጣበት መንገድ አያገኝም፤

• ሁላችንም በየቀኑ የሚያጋጥመን ረሀብና ለብዙ ወራት ቆይቶ ሥጋን ጨርሶና አጥንትን ፍቆ ለሞት የሚዳርገው ችጋር አንድ አይደሉም፤

• ድርቅ የሚባለው የተፈጥሮ አደጋና በሰው ልጆች ቸልተኛነት የሚከሰተው ችጋር አንድ አይደሉም፤ ሁለቱን አንድ ለማድረግ የሚሞከረው ኃላፊነትን ለመሸሽ ነው፡፡

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)
ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ኅዳር 2008
Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule