• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስለ ችጋር

December 1, 2015 11:46 am by Editor Leave a Comment

• ችጋር ምንድን ነው? ሰፊ ቦታንና ብዙ ሕዝብን የሚሸፍን፣ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ፣ ምንም የሚላስ የሚቀመስ ጠፍቶ እንስሳት (ሰውንም ጨምሮ) ዕለት በዕለት የራሳቸውን አካል እስኪያልቅ ድረስ “እየበሉ” በመጨረሻም የሚሞቱበት ሁኔታ ነው፤ ረሀብ አካል ሲዳከም አካልን ለመገንባት የሚደረግ ጥሪ ነው፡፡

• ችጋር የሚያጠቃው ማንን ነው? ትልቁና ዋናው የችጋር እንቆቅልሽ የዚህ ጥያቄ መልስ ነው፤ አብዛኛውን ጊዜ ችጋር የሚያጠቃው ከገበያ ጋር የማይገናኙትን ምግብ አምራቾችን ገበሬዎችን፣ በተለይም እያመረቱ ከእጅ ወዳፍ ብቻ የሚኖሩትን ነው፤ እነዚህ ገበሬዎች የገጠሩ ሕዝብ፣ ማለትም የአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ የመጨረሻ ደሀዎች ናቸው፤ ኑሮአቸው ሁልጊዜም በችጋር አፋፍ ላይ ነው፡፡

• ችጋር ከተፈጥሮ ጋር ያለው ግንኙነት እንዴት ነው? ከላይ እንደተባለው በችጋር ላይ የሚወድቁት ገበሬዎች ከገበያ ጋር እምብዛም ግንኙነት የሌላቸው ናቸው፤ ይህም እምብዛም ጥሬ ገንዘብ የላቸውም ማለት ነው፤ ስለዚህ በገበያ ላይ እህል ቢኖርም የመግዛት አቅም የላቸውም፤ ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ግንኙነት የጠበቀ ነው፤ ምርታቸው መቶ በመቶ በተፈጥሮ ችሮታ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ስለዚህም ተፈጥሮ በትንሹ እንኳን ፊቱን ካዞረ ምርቱ ያንሳል ወይም ጭራሹኑ ይጠፋል፡፡

• ተፈጥሮ ፊቱን የሚያዞረው እንዴት ነው? ብዙ መንገዶች አሉ፤የእርሻ ምርት በተፈጥሮ ሀብቶች ላይ የተመሠረተ ነው፤ መሬት (አፈር)፣ ውሀ፣ የዓየር ጠባይና ጉልበት፣ ተፈጥሮ በነዚህ ላይ ፊቱን ማዞሩ የሚገለጥባቸው ዋና ዋናዎቹ፡-

• ዝናብ ወይ ይበዛል ወይ ያንሳል፤
• የዝናቡ ወቅት ይቀድማል፤ ወይም ይዘገያል፤
• ምርቱን ውርጭ ይመታዋል፤
• ምርቱን ተምች ይመታዋል፤
• ምርቱን በሽታ ይበላዋል፤
• ምርቱን ከባድ ጎርፍ ወይም ከባድ በረዶ ያጠቃዋል፤
• ሌላም፣ ሌላም፣


• ተፈጥሮ በአንድ ምክንያት ፊቱን ሲያዞር ለወትሮው በችጋር አፋፍ ላይ የነበሩት ደሀ ገበሬዎቸው ወደችጋሩ ገደል መግባት ይጀምራሉ፤

• ችጋር ሕዝብን በጅምላ የሚጨፈጭፍበት ጊዜ ከስድስት እስከስምንት ወራት ይፈጃል፤ የተፈጥሮ ችግር መኖሩ ከታወቀ ጀምሮ ከስድስት አስከስምንት ወሮች ሰዎች አካላቸውን “እየበሉ” ይቆያሉ፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ ተከሰተ የተባለው ድርቅ ሰዎችን በችጋር መረፍረፍ የሚጀምረው በሚያዝያና በመጋቢት ነው፤ ገበሬዎቹ ከአሁን ጀምሮ እስከ መጋቢት ምንም ሰፊና ትልቅ ዘላቂ እርዳታ ካላገኙ በመጋቢትና በሚያዝያ ሰው እንደቅጠል የሚረግፍበት ጊዜ ይሆናል፤

• ልብ በሉ የመጀመሪያው የተፈጥሮ አደጋ ሲከሰት ወይ የተዘራው ጠፍቶአል፤ ወይ ቀንሶአል፤ ወይ ተበላሽቶል፤ ስለዚህም ገና በክረምት ወራት አዝመራ እንደማይኖር ይታወቃል፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አስከመጋቢትና ሚያዝያ ቢያንስ ስምንት ወራት አሉ፤ በዚህ ጊዜ ሰዎች ወደችጋሩ ገደል እንዳይገቡ የሚያግደው፡-

ሀ) እያንዳንዱ ሰው ወይም ቤተሰብ ለክፉ ቀን ለመጠባበቂያ የሚሆን እህል በጎተራ ለምን አያስቀምጥም?
ለ) ለክፉ ቀን ጥሬ ገንዘብ በባንከ ለማን አያስቀምጥም?
ሐ) አገዛዙ የእርሻ ምርት የሚቀንስ ወይም የሚጠፋ መሆኑ ከታወቀ ጀምሮ ተጠቂ ለሚሆነው ሕዝብ በቂ ምግብ ለምን አያዘጋጅም? ሕዝቡ ራሱ ለችጋር አደጋ እንዳይጋለጥ በየወረዳው “የእህል ባንክ” ለምን አያቋቁምም?
መ) ከእጅ ወደአፍ የማያልፍ ምርት የሚያመርቱ (ሁሌም ለችጋር የሚጋለጡት) ገበሬዎች ለምን ግብርና ሌሎችም መዋጮዎች እንዲከፍሉ ይገደዳሉ? እንዲያውም በአንጻሩ አገዛዙ እነዚህ ለአደጋ የተጋለጡ ገበሬዎች ማኅበራዊና መዋዕለ ንዋያዊ አቅማቸው አቅማቸው እንዲዳብርና እንዲበረታ የማያደርገው ለምንድን ነው? ደሀነታቸውንና ደካማነታቸውን የሚፈልገው ለምንድን ነው?
ሌሎች፣ ሌሎች ጥያቄዎችም …


• የመጨረሻውና ዋናው ነጥብ ማናቸውም ዓይነት የተፈጥሮ አደጋ ከችጋር ጋር በቀጥታ የተያያዘ አለመሆኑ ነው፤ ከአደጋው በፊት ለማኅበረሰቡ የኑሮና የአስተዳደር ግንኙነት የተገነባው ሕጋዊ የነጻነትና የልማት ሥርዓት መኖር ወይም አለመኖር በአንድ በኩል፣ አደጋውን ተከትሎ እያንዳንዱ ግለሰብ በተናጠል፣ ማኅበረሰቡ በአጠቃላይ ያደረጉትን ወይም ሊያደርጉት የሚገባውን አብረን ስንመለከተው በተፈጥሮ አደጋውና በችጋር መሀከል ያለው ረጅም የጊዜ ርቀት ችጋርን የአገዛዝ ውላጅ ያደርገዋል፤

• ስለዚህም ለልማትም ሆነ የተፈጥሮ አደጋን ለመቋቋም ግለሰቡ በሕጋዊ ሥርዓት ስር በሙሉ ነጻነት የማይኖር ከሆነ ከችጋር የሚወጣበት መንገድ አያገኝም፤

• ሁላችንም በየቀኑ የሚያጋጥመን ረሀብና ለብዙ ወራት ቆይቶ ሥጋን ጨርሶና አጥንትን ፍቆ ለሞት የሚዳርገው ችጋር አንድ አይደሉም፤

• ድርቅ የሚባለው የተፈጥሮ አደጋና በሰው ልጆች ቸልተኛነት የሚከሰተው ችጋር አንድ አይደሉም፤ ሁለቱን አንድ ለማድረግ የሚሞከረው ኃላፊነትን ለመሸሽ ነው፡፡

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)
ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ኅዳር 2008
Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule