• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚ/ር ዓቢይ

June 6, 2018 12:35 am by Editor Leave a Comment

ክቡር ሆይ

ግንቦት 28 ቀን 2010 አም የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሜቴ በቁልፍ የአኮኖሚ ተግባር የተሰማሩና እስካሁን በመንግስት ቁጥጥር ስር ያሉ አገልግሎት ሰጪና አምራች ድርጅቶች በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለግል ባለሀብቶች እንዲሸጡ መወሰኑን ተረድቻለሁ፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የባቡር አገልግሎት ለሽያጭ እንዲቀርቡ መወሰኑ ከፍተኛ ሀዘንና ድንጋጤ ፈጥሮብኛል፡፡

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣

ከሁለት ወራት በፊት የኢህአዴግ ሊቀመንበርና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ከተመረጡ በኋላ በሚያራምዱት የአንድነት፣ የፍቅር፣ የልማት፣ የዴሞክራሲና የህግ የበላይነት ኢትዮጵያዊ ራእይ በአገራችን በኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ታይቶ የማያውቅ የሰላም፣ የፍቅርና የተስፋ መንፈስ ቀስቅሰዋል፡፡ አንዳንዶቻችን ኢህአዴግ እንደ ድርጅትና እንደ መንግስት ባለፉት 27 አመታት በህዝብና በአገር ላይ የፈጸመው በደል ሳያግደን ከጎንዎ ተሰልፈናል፡፡ የሁን እንጂ፣ ይህ አሁን የተገለጠው የኢህአዴግ ውሳኔ የአገርንና የህዝብን ዘላቂ ጥቅም ከፍተኛ ጉዳት ላይ የሚጥል መሆኑን በአክብሮት ልገልጥልዎ እወዳለሁ፡፡

የህዝብ ንብረት የሆኑ አገልግሎት ሰጭና አምራች ድርጅቶችን ወደ ግል ንብረትነት ለማዛወር የተወሰነው የአገሪቱን ፈጣንና ተከታታይ እድገት ለማገዝ መሆኑ ተገልጧል፡፡ ይህ ምክንያት ለስኳር አምራች ድርጅቶችና ለኢትዮ ቴሌኮም ይሰራ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድን እና ባቡርን በሚመለከት ግን የሚያስከትለው ጥቅምን ሳይሆን ከፍተኛ ጉዳትን ነው፡፡

በ1938 አም የተቋቋመው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአገልግሎቱ ብቃትና ጥራት በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሌለው፣ በአለም ዙሪያ ታዋቂነትን ያተረፈ ድርጅት፡፡ በአለም ዙሪያ ያሉ ትላልቅ የግልና የመንግስት አየር መንገዶች እየከሰሩ በሚዘጉበት ወቅት በአትራፊነት የዘለቀ ብሄራዊ ቅርስ ነው፡፡ በሙሉ ቀርቶ በከፈልም ቢሆን ለግል ባለንብረቶች የሚሸጥበት አንዳች አሳማኝ ምክንያት የለም፡፡ አላማው ይበልጥ እድገት ማስቻል ከሆነ የግል ባለሀብቶች ሌላ ተፎካካሪ አየር መንገድ አቋቁመው ገበያውን እንዲቀላቀሉ መምከር እንጂ ይህንን የመሰለ ሁለት ትውልድ መስዋእት ከፍሎ ያበለጸገውን አትራፊ ስመ-ጥር ተቋም ለግል ባለሀብቶች መሸጥ ታሪካዊ ስህተት ይሆናል፡፡

ባቡርን በሚመለከት የበርካታ አውሮፓ አገሮች ልምድ የሚያሳየው ባቡር ሙሉ ለሙሉ ወይም ከ80 በመቶ በላይ የአክስዮን ድርሻው በህዝብ ንብረትነት የተያዘ ነው፡፡ ከነዚህ መሀል ሆላንድ፣ ስዊድን፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ቤልጂግ የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡

በአንጻሩ በ1985 አም በስልጣን ላይ የነበረው የእንግሊዝ ወግ አጥባቂ መንግስት፣ በፖለቲካ ምክንያት፣ የህዝብ ንብረት የነበረውን የእንግሊዝ ባቡር ለግል ባለንብረቶች ከሸጠው በኋላ እስካሁን ራሱን መቻል አቅቶት በኪሳራ ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በየአመቱ ከእንግሊዝ መንግስት በቢልዮን ዶላር የሚቆጠር ድጎማ ለግል ባለንብረቶቹ ይሰጣል፡፡ የባቡር አገልግሎት ጥራት ከአውሮፓ አገሮች ጋር ሲወዳደር የእንግሊዝ ከተጠቀሱት አገሮች ሁሉ ዝቅተኛ ነው፡፡ ባቡር ለመሳፈር የእንግሊዝ ህዝብ የሚከፍለው ዋጋ ግን ከአውሮፓ አገሮች ጋር ሲወዳደር እስከ 40 በመቶ ከፍ ያለ ነው፡፡ በነዚህና ሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች ተቃዋሚው የእንግሊዝ ሰራተኞች ፓርቲ ባቡርን መልሼ እወርስና የህዝብ ንብረት አደርጋለሁ ሲል ለህዝብ ቃል ገብቷል፡፡

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣

ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅምና ለዘላቂው ህዝባዊ ጥቅም ሲባል፣ ጫናው ከየትም ይምጣ ከየት፣ እነዚህን የመሳሰሉ ብሄራዊ ተቋሞች ለሽያጭ ሊቀርቡ አይገባም፡፡

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

አበራ የማነ አብ፣ ብሩሴል፣ ቤልጅግ ግንቦት 29፣ 2010

aberayemaneab@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule