• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚ/ር ዓቢይ

June 6, 2018 12:35 am by Editor Leave a Comment

ክቡር ሆይ

ግንቦት 28 ቀን 2010 አም የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሜቴ በቁልፍ የአኮኖሚ ተግባር የተሰማሩና እስካሁን በመንግስት ቁጥጥር ስር ያሉ አገልግሎት ሰጪና አምራች ድርጅቶች በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለግል ባለሀብቶች እንዲሸጡ መወሰኑን ተረድቻለሁ፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የባቡር አገልግሎት ለሽያጭ እንዲቀርቡ መወሰኑ ከፍተኛ ሀዘንና ድንጋጤ ፈጥሮብኛል፡፡

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣

ከሁለት ወራት በፊት የኢህአዴግ ሊቀመንበርና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ከተመረጡ በኋላ በሚያራምዱት የአንድነት፣ የፍቅር፣ የልማት፣ የዴሞክራሲና የህግ የበላይነት ኢትዮጵያዊ ራእይ በአገራችን በኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ታይቶ የማያውቅ የሰላም፣ የፍቅርና የተስፋ መንፈስ ቀስቅሰዋል፡፡ አንዳንዶቻችን ኢህአዴግ እንደ ድርጅትና እንደ መንግስት ባለፉት 27 አመታት በህዝብና በአገር ላይ የፈጸመው በደል ሳያግደን ከጎንዎ ተሰልፈናል፡፡ የሁን እንጂ፣ ይህ አሁን የተገለጠው የኢህአዴግ ውሳኔ የአገርንና የህዝብን ዘላቂ ጥቅም ከፍተኛ ጉዳት ላይ የሚጥል መሆኑን በአክብሮት ልገልጥልዎ እወዳለሁ፡፡

የህዝብ ንብረት የሆኑ አገልግሎት ሰጭና አምራች ድርጅቶችን ወደ ግል ንብረትነት ለማዛወር የተወሰነው የአገሪቱን ፈጣንና ተከታታይ እድገት ለማገዝ መሆኑ ተገልጧል፡፡ ይህ ምክንያት ለስኳር አምራች ድርጅቶችና ለኢትዮ ቴሌኮም ይሰራ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድን እና ባቡርን በሚመለከት ግን የሚያስከትለው ጥቅምን ሳይሆን ከፍተኛ ጉዳትን ነው፡፡

በ1938 አም የተቋቋመው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአገልግሎቱ ብቃትና ጥራት በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሌለው፣ በአለም ዙሪያ ታዋቂነትን ያተረፈ ድርጅት፡፡ በአለም ዙሪያ ያሉ ትላልቅ የግልና የመንግስት አየር መንገዶች እየከሰሩ በሚዘጉበት ወቅት በአትራፊነት የዘለቀ ብሄራዊ ቅርስ ነው፡፡ በሙሉ ቀርቶ በከፈልም ቢሆን ለግል ባለንብረቶች የሚሸጥበት አንዳች አሳማኝ ምክንያት የለም፡፡ አላማው ይበልጥ እድገት ማስቻል ከሆነ የግል ባለሀብቶች ሌላ ተፎካካሪ አየር መንገድ አቋቁመው ገበያውን እንዲቀላቀሉ መምከር እንጂ ይህንን የመሰለ ሁለት ትውልድ መስዋእት ከፍሎ ያበለጸገውን አትራፊ ስመ-ጥር ተቋም ለግል ባለሀብቶች መሸጥ ታሪካዊ ስህተት ይሆናል፡፡

ባቡርን በሚመለከት የበርካታ አውሮፓ አገሮች ልምድ የሚያሳየው ባቡር ሙሉ ለሙሉ ወይም ከ80 በመቶ በላይ የአክስዮን ድርሻው በህዝብ ንብረትነት የተያዘ ነው፡፡ ከነዚህ መሀል ሆላንድ፣ ስዊድን፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ቤልጂግ የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡

በአንጻሩ በ1985 አም በስልጣን ላይ የነበረው የእንግሊዝ ወግ አጥባቂ መንግስት፣ በፖለቲካ ምክንያት፣ የህዝብ ንብረት የነበረውን የእንግሊዝ ባቡር ለግል ባለንብረቶች ከሸጠው በኋላ እስካሁን ራሱን መቻል አቅቶት በኪሳራ ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በየአመቱ ከእንግሊዝ መንግስት በቢልዮን ዶላር የሚቆጠር ድጎማ ለግል ባለንብረቶቹ ይሰጣል፡፡ የባቡር አገልግሎት ጥራት ከአውሮፓ አገሮች ጋር ሲወዳደር የእንግሊዝ ከተጠቀሱት አገሮች ሁሉ ዝቅተኛ ነው፡፡ ባቡር ለመሳፈር የእንግሊዝ ህዝብ የሚከፍለው ዋጋ ግን ከአውሮፓ አገሮች ጋር ሲወዳደር እስከ 40 በመቶ ከፍ ያለ ነው፡፡ በነዚህና ሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች ተቃዋሚው የእንግሊዝ ሰራተኞች ፓርቲ ባቡርን መልሼ እወርስና የህዝብ ንብረት አደርጋለሁ ሲል ለህዝብ ቃል ገብቷል፡፡

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣

ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅምና ለዘላቂው ህዝባዊ ጥቅም ሲባል፣ ጫናው ከየትም ይምጣ ከየት፣ እነዚህን የመሳሰሉ ብሄራዊ ተቋሞች ለሽያጭ ሊቀርቡ አይገባም፡፡

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

አበራ የማነ አብ፣ ብሩሴል፣ ቤልጅግ ግንቦት 29፣ 2010

aberayemaneab@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule