• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚ/ር ዓቢይ

June 6, 2018 12:35 am by Editor Leave a Comment

ክቡር ሆይ

ግንቦት 28 ቀን 2010 አም የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሜቴ በቁልፍ የአኮኖሚ ተግባር የተሰማሩና እስካሁን በመንግስት ቁጥጥር ስር ያሉ አገልግሎት ሰጪና አምራች ድርጅቶች በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለግል ባለሀብቶች እንዲሸጡ መወሰኑን ተረድቻለሁ፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የባቡር አገልግሎት ለሽያጭ እንዲቀርቡ መወሰኑ ከፍተኛ ሀዘንና ድንጋጤ ፈጥሮብኛል፡፡

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣

ከሁለት ወራት በፊት የኢህአዴግ ሊቀመንበርና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ከተመረጡ በኋላ በሚያራምዱት የአንድነት፣ የፍቅር፣ የልማት፣ የዴሞክራሲና የህግ የበላይነት ኢትዮጵያዊ ራእይ በአገራችን በኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ታይቶ የማያውቅ የሰላም፣ የፍቅርና የተስፋ መንፈስ ቀስቅሰዋል፡፡ አንዳንዶቻችን ኢህአዴግ እንደ ድርጅትና እንደ መንግስት ባለፉት 27 አመታት በህዝብና በአገር ላይ የፈጸመው በደል ሳያግደን ከጎንዎ ተሰልፈናል፡፡ የሁን እንጂ፣ ይህ አሁን የተገለጠው የኢህአዴግ ውሳኔ የአገርንና የህዝብን ዘላቂ ጥቅም ከፍተኛ ጉዳት ላይ የሚጥል መሆኑን በአክብሮት ልገልጥልዎ እወዳለሁ፡፡

የህዝብ ንብረት የሆኑ አገልግሎት ሰጭና አምራች ድርጅቶችን ወደ ግል ንብረትነት ለማዛወር የተወሰነው የአገሪቱን ፈጣንና ተከታታይ እድገት ለማገዝ መሆኑ ተገልጧል፡፡ ይህ ምክንያት ለስኳር አምራች ድርጅቶችና ለኢትዮ ቴሌኮም ይሰራ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድን እና ባቡርን በሚመለከት ግን የሚያስከትለው ጥቅምን ሳይሆን ከፍተኛ ጉዳትን ነው፡፡

በ1938 አም የተቋቋመው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአገልግሎቱ ብቃትና ጥራት በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሌለው፣ በአለም ዙሪያ ታዋቂነትን ያተረፈ ድርጅት፡፡ በአለም ዙሪያ ያሉ ትላልቅ የግልና የመንግስት አየር መንገዶች እየከሰሩ በሚዘጉበት ወቅት በአትራፊነት የዘለቀ ብሄራዊ ቅርስ ነው፡፡ በሙሉ ቀርቶ በከፈልም ቢሆን ለግል ባለንብረቶች የሚሸጥበት አንዳች አሳማኝ ምክንያት የለም፡፡ አላማው ይበልጥ እድገት ማስቻል ከሆነ የግል ባለሀብቶች ሌላ ተፎካካሪ አየር መንገድ አቋቁመው ገበያውን እንዲቀላቀሉ መምከር እንጂ ይህንን የመሰለ ሁለት ትውልድ መስዋእት ከፍሎ ያበለጸገውን አትራፊ ስመ-ጥር ተቋም ለግል ባለሀብቶች መሸጥ ታሪካዊ ስህተት ይሆናል፡፡

ባቡርን በሚመለከት የበርካታ አውሮፓ አገሮች ልምድ የሚያሳየው ባቡር ሙሉ ለሙሉ ወይም ከ80 በመቶ በላይ የአክስዮን ድርሻው በህዝብ ንብረትነት የተያዘ ነው፡፡ ከነዚህ መሀል ሆላንድ፣ ስዊድን፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ቤልጂግ የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡

በአንጻሩ በ1985 አም በስልጣን ላይ የነበረው የእንግሊዝ ወግ አጥባቂ መንግስት፣ በፖለቲካ ምክንያት፣ የህዝብ ንብረት የነበረውን የእንግሊዝ ባቡር ለግል ባለንብረቶች ከሸጠው በኋላ እስካሁን ራሱን መቻል አቅቶት በኪሳራ ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በየአመቱ ከእንግሊዝ መንግስት በቢልዮን ዶላር የሚቆጠር ድጎማ ለግል ባለንብረቶቹ ይሰጣል፡፡ የባቡር አገልግሎት ጥራት ከአውሮፓ አገሮች ጋር ሲወዳደር የእንግሊዝ ከተጠቀሱት አገሮች ሁሉ ዝቅተኛ ነው፡፡ ባቡር ለመሳፈር የእንግሊዝ ህዝብ የሚከፍለው ዋጋ ግን ከአውሮፓ አገሮች ጋር ሲወዳደር እስከ 40 በመቶ ከፍ ያለ ነው፡፡ በነዚህና ሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች ተቃዋሚው የእንግሊዝ ሰራተኞች ፓርቲ ባቡርን መልሼ እወርስና የህዝብ ንብረት አደርጋለሁ ሲል ለህዝብ ቃል ገብቷል፡፡

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣

ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅምና ለዘላቂው ህዝባዊ ጥቅም ሲባል፣ ጫናው ከየትም ይምጣ ከየት፣ እነዚህን የመሳሰሉ ብሄራዊ ተቋሞች ለሽያጭ ሊቀርቡ አይገባም፡፡

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

አበራ የማነ አብ፣ ብሩሴል፣ ቤልጅግ ግንቦት 29፣ 2010

aberayemaneab@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule