• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የ“ህዳሴው” ግድብ ተጽዕኖ ሌላ አቅጣጫ መያዙ አሳሳቢ ሆኗል

April 25, 2014 09:49 pm by Editor Leave a Comment

ሃያ አምስት በመቶ እንደተጠናቀቀ የሚነገርለት የ“ህዳሴው” ግድብ በኢትዮያና በግብጽ መካከል ከፈጠረው የፖለቲካ ቁርቋሶ በተጨማሪ ወደ ሃይማኖት መንደርም እየዘለቀ ነው፡፡ ዛሬ (አርብ) ግብጽን ለመጎብኘት ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበሩት አቡነ ማቲያስ ከግብጽ በኩል እንዳይመጡ በተላለፈላቸው መልዕክት መሠረት ጉብኝታቸውን ላልተወሰነ ጊዜ አስተላልፈውታል፡፡

በግብጽና በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የተለያዩ የዜና ዘጋቢዎች እንዳሉት ከሆነ መልዕክቱ ያስተላለፉት የግብጹ ፓትሪያርክ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ ናቸው፡፡ ፓትሪያርኩ ለአቡነ ማቲያስ ባስተላለፉት መልዕክት በበርካታ ቢሊዮን ዶላር የሚገነባው የአባይ ግድብ የፈጠረው ሁኔታ እንዳለ ሆኖ ይህንን ጉብኝት ማካሄድ የግብጽን ቤ/ክ “የሚያሳፍር” ይሆናል በሚል ነው ምክራቸውን ለአቡነ ማቲያስ የለገሱት፡፡

ስማቸውን ሳይጠቅሱ መረጃውን ለግብጽ የሚዲያ አካላት የተናገሩት ባለሥልጣን እንደሚሉት ከሆነ ሁለቱ ቤ/ክናት ለረጅም ጊዜ የቆየ ግንኙነት ቢኖራቸውም ግድቡን በተመለከተ ይፋዊ ያልሆነ ሽምግልና የማካሄዳቸው ሁኔታ የማያዛልቅ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ሁለቱ ከፍተኛ የቤ/ክ መሪዎች በሚገናኙበት ወቅት ይህ ጉዳይ ሳይነሳ እንደማይታለፍ የታወቀ ነው፡፡

አቡነ ታዋድሮስ “አሳፋሪ” ያሉትን ጉዳይ በዝርዝር አልገለጹትም ሆኖም የግድቡ መሠራት ግብጽን ክፉኛ ያሳሰባት ጉዳይ ከሆነ ሰንብቷል፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ በተለያዩ ጉዳዮች ውስጥ ጣልቃ ስትገባ ከመቆየት አልፋ ኢህአዴግን ለሚቃወሙ የመሣሪያና የመሳሰሉ ዕገዛዎችን ለማድረግ ስትንቀሳቀስ መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡

በሃይማኖቱ ዓለም ከፍተኛ ትስስር ያላቸው የግብጽና የኢትዮጵያ ቤ/ክናት ከ“ህዳሴው” ግድብ ጋር በተያያዘ እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳቸው የውጥረቱን አሳሳቢነት የሚገልጽ ነው የሚሉ ክፍሎች ግብጽ መረጋጋት ስታገኝ የሚሆነውን ለመተንበይ ያስቸግራል ይላሉ፡፡ የሃይማኖት ተቋማት ለዕርቅና ሰላም መሥራት በሚገባቸው ጊዜ ከፖለቲካው በላይ መሆን አለመቻላቸው ሹመታቸውም ከዚያው የመነጨ ለመሆኑ ማስረጃ ነው፡፡ አገልግሎታቸውም ከፖለቲካው ሥልጣን በላይ መሆን ያልቻለ መሆኑን በግልጽ ያሳያል በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ያነጋገራቸው ባለሙያ እንደሚሉት የግድቡ ሥራና በሁለቱ አገሮች መካከል የተፈጠረው ሁኔታ ሁሉንም ሊያሳስብ የሚገባ ነው ይላሉ፡፡ በተለይ ኢህአዴግ የግድቡን ሥራ ለፖለቲካ መጠቀሚያነት ማዋሉ “አስከፊ ነው” ብለዋል፡፡ “አባይን የመገደቡ ጉዳይ አሁን የታሰበ ወይም የተጀመረ አይደለም፤ በንጉሡ ጊዜም ሆነ በደርግ ጊዜ የነበረ ነው፡፡ እኔ የፖለቲካ ተንታኝም ሆነ የታሪክ ምሁር አይደለሁም ነገር ግን በግድቡ ሥራ ላይ ባለኝ ሙያ በከፍተኛ ደረጃ እሳተፋለሁ፡፡ ህወሃት እና ኢህአዴግ ለራሳቸው ርካሽ ፖለቲካ መጠቀሚያነት ሲያውሉትና ሕዝቡን ከንቱ በሆነ አገራዊ ስሜት አስገብተው የራሳቸውን ፖለቲካ ለማራመድ የሚያደርጉትን ሁሉ በየቀኑ በሥራችን ላይ የምናየው አስከፊ ልምምድ ነው፡፡ እኔ የትግራይ ተወላጅ በመሆኔ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያዊነቴ አባይ ለዚህ መዋሉ ያስደስተኛል ነገር ግን ኅብረተሰቡ ሲጠይቅ “የግብጽ ደጋፊ ነህ፤ ጸረ-ልማት ነህ ወዘተ” ማለቱ የትም አያደርስም፡፡ በዚህ ላይ ከአገሪቷ ኢኮኖሚ አኳያ የግድቡ ወጪም ሆነ፣ የባለቤትነቱ ጉዳይ እንዲሁም ሌላ በርካታ ጉዳዮች ሊጠየቁ የሚገባቸው ጥያቄዎች ናቸው” ብለዋል፡፡

ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ዕቅድ ተይዞለት የነበረው የአቡነ ማትያስ የግብጽ ጉብኝት ላሁኑ ተላልፎ የነበረ ሲሆን የአቡነ ታዋድሮስ የመስከረም ወር የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውም በተመሳሳይ ምክንያት መሰረዙ ይታወሳል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule