• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሁለት እስረኞች ወግ!

September 16, 2016 07:51 am by Editor Leave a Comment

አዋቂው፣ ዕውቁ እና ተወዳጁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ትሁቱ እና ሠላማዊው ፖለቲከኛ አንዱዓለም አራጌን በአካል ያየኋቸው በ2003 መጨረሻ በአንድነት ፓርቲ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ነበር። ያኔ በጋራ የምንጦምርበትና ለእስር የዳረገን ዞን ዘጠኝ አልተመሠረተም ነበር። ነገር ግን ጓደኞቼ እና ባልደረቦቼ Soleyana እና Atnaf ሳንተዋወቅ በፊት እዚያ እንደነበሩ ኋላ ስናወራ ሰምቻለሁ። በርካታ ሰዎች በተገኙበት ያ ስብሰባ ላይ ዛሬ ዝዋይ ወኅኒ የተጣለው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ተገኝቶ ነበር። ያቺ ስብሰባ እስክንድር ጥናታዊ ንግግር ያቀረበባት ስብሰባ ነበረች። ጥናታዊ ንግግሩ እና ውይይቱ በጥቅሉ በእነአንዱዓለም አራጌ መዝገብ የተከሰሱት 24 ሰዎች ላይ ማስረጃ ሆኖ መጥቷል።

የእነአንዱዓለም አራጌ መዝገብ ብዙ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች የተከሰሱበት መዝገብ ነው። የአዲስ ነገሮቹን ዐብይ ተክለማርያም እና መስፍን ነጋሽ ጨምሮ፣ ከእስክንድር ሌላ አምስት ጋዜጠኞች በዚህ መዝገብ ተፈርዶባቸዋል።

እስክንድርን እና አንዱዓለምን ከዚያ በኋላ ያገኘኋቸው እና የማናገር ዕድል የገጠመኝ ከታሰሩ በኋላ በቃሊቲ (እኔ ራሴ ከመታሰሬ በፊት) ነው። እስክንድር ነጋ ላይ በወቅቱ ለሕወሓት ወገንተኛ የሆኑ ጦማሪዎች ያልጻፈውን ጻፈ እያሉ ሥሙን ሲያጠፉ እውነቱ ምንድን ነው ልለው ነበር የሔድኩት። በኋላ በጥቂት ቀናት ንግግር ብቻ ነፍሴን በቀናነቱ አለመለማት። እስክንድር በጣም ሲመክረኝ ከነበሩ ነገሮች ውስጥ ነውጥ-አልባ (non violent) የትግል ስልት ላይ ፍፁማዊ እምነት እንዲኖረኝ እና ለምሠራቸው ሥራዎች በሙሉ ኃላፊነቱን ለመውሰድ እንድዘጋጅ ነበር። አድርጌዋለሁ/አደርገዋለሁ ብዬ አምናለሁ። ነውጥ-አልባ ፀረ-ጭቆና ትግሌ ይፋዊ የሆነበት እና ወደፊትም የሚሆንበት ምክንያት ለእርሱ ያለኝ አድናቆት እና ክብር የሚገለጽበት መንገድ ስለሆነ ነው።

አንዱዓለም አራጌንም ከዞን ዘጠኝ ባልደረቦቼ እና ሌሎችም ጋር እንጠይቀው ነበር። ስክን ያለ፣ ሃይማኖቱን አጥባቂ እና በመብቱ የማይደራደር ሰው ከገጠማችሁ – እሱ አንዷለም አራጌ ነው። አንዱዓለምን ልንጠይቀው መጀመሪያ የሔድን ግዜ፣ ስለእኛ ጠየቀንና “አዪዪ፣… ይሄ መንግሥት ያስራችኋል” አለን። ያለውም አልቀረ፣ በዓመት ከምናምኑ ታሰርን። አንዱዓለም ከታሰረ በኋላ ሁለት አስገራሚ መጽሐፎች ጽፏል። ‘ያልተሔደበት መንገድ’ እና ‘የሀገር ፍቅር ዕዳ’ የሚሉ ናቸው። መጽሐፍቱን ማንበቡ የአንዱዓለምን ሠላማዊነት እና ባለራዕይነት ማመን ለማይፈልጉት ሳይቀር ያሳምናል።

አንዱዓለም የሁለት ወንድ ልጆች አባት ነው። በአንደኛው መጽሐፉ መግቢያ ላይ እንዲህ ይላል፣ ‘በ1998 ስታሰር [ያኔ ትዳር አልያዘም ነበር] ሳልወልድ ታሰርኩ እያልኩ ሲቆጨኝ ነበር፤ ተፈትቼ አግብቼ ከወለድኩ በኋላ ደግሞ መልሼ ስታሰር የማላሳድጋቸውን ልጆች ወልጄ እያልኩ እቆጫለሁ’ በማለት ቁጭት የማይቀር መሆኑን እና እያንዳንዱ ባለራዕይ መስዋዕትነት እንደሚከፍል ይነግረናል።

ጋዜጠኛ እስክንድርም የአንድ ልጅ አባት ነው። ጓዳው የማይጎድልበት እስክንድር ብልጭልጭ ነገር ሳያሸንፈው ያለውን ሁሉ እውነትን ለጉልቤዎች በመናገር (speaking truth to power) አሳልፎ የሰጠ ሰው ነው። እስር ቤት የተወለደው የታላቁ እስክንድር አንድያ ልጁ ናፍቆት እስክንድር እና ጋዜጠኛ ባለቤቱ ሰርካለም ፋሲል አሁን ሁለቱም ለስደት ተዳርገዋል።

ለአዲስ ዓመት ከግፍ እስር የተፈታው ‘የሙስሊሞች ጉዳይ’ ጋዜጣ አዘጋጁ ጋዜጠኛ ዩሱፍ ጌታቸው ስለ እስክንድር ነጋ አውርቶ አይጠግብም። ቃሊቲ አብረው በታሰሩበት ወቅት የተመለከተውን ሲነግረኝ፣ “እንደሱ ሥነ ስርዓት ያለው ሰው የለም። ሁሉን በዕቅድ ይመራል። እስር ቤት ውስጥ ስፖርት የሚሠራበት፣ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያነብበት እና እያንዳንዱን ነገር የሚያደርግበት የማይዛነፍ ሰዓት አለው። ከፅዳት ሠራተኞቹ ጋር በሳምንት ሁለቴ ቤት ያፀዳል። ከሰዎች ጋር አብሮ የበላበትን ሰሀን የሚያጥበው እሱ ብቻ ነው…” ~ ሽብርተኛ ተብሎ የ18 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበት እስክንድር ነጋ።

እስክንድር ሌላ ቢዝነስ እየሠራ ወይም ተሰድዶ ‘የተደላደለ’ ኑሮ መኖር ሲችል፣ ስለእውነቱ እና እምነቱ የእኔ እና የእናንተን ዕዳ ደርቦ እየከፈለ ነው። አንዱዓለም ከዐሥር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የተከሰተ ድርቅን አስመልክቶ ለተጎዱ ወገኖች መንግሥት በአስቸኳይ እንዲደርስላቸው ሲል ብቻውን ሠላማዊ ሰልፍ የወጣ ዜጋ ነው። በቲፎዞ መኖር አለመኖር፣ ጥቅም ቀርቶ ያላቸውን በማጣት እና ባለማጣት የማይሸበሩት እኒህ ፍፁም ሠላማዊ የትግል አውራዎች የማይገባቸውን ፍርድ ተሸክመው በወኅኒ፣ በአስቀያሚ አያያዝ ተጥለው ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው መንግሥት እነዚህ መሰሎቹን ንፁኃን ነፍሶች በማሰር እና በማሰቃየት የማይቀረውን ነውጥ እና መከፋፈል ሲጠራ ኖሯል። ዛሬ (ዘንድሮ) ለዚህ ሕያው ምስክር ነች።

መስከረም 3, 2009 ሁለቱ ንፁኃን ከታሰሩ እነሆ አምስት ዓመታቸው። (ምንጭ: BefeQadu Z. Hailu)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule