• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሁለት እስረኞች ወግ!

September 16, 2016 07:51 am by Editor Leave a Comment

አዋቂው፣ ዕውቁ እና ተወዳጁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ትሁቱ እና ሠላማዊው ፖለቲከኛ አንዱዓለም አራጌን በአካል ያየኋቸው በ2003 መጨረሻ በአንድነት ፓርቲ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ነበር። ያኔ በጋራ የምንጦምርበትና ለእስር የዳረገን ዞን ዘጠኝ አልተመሠረተም ነበር። ነገር ግን ጓደኞቼ እና ባልደረቦቼ Soleyana እና Atnaf ሳንተዋወቅ በፊት እዚያ እንደነበሩ ኋላ ስናወራ ሰምቻለሁ። በርካታ ሰዎች በተገኙበት ያ ስብሰባ ላይ ዛሬ ዝዋይ ወኅኒ የተጣለው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ተገኝቶ ነበር። ያቺ ስብሰባ እስክንድር ጥናታዊ ንግግር ያቀረበባት ስብሰባ ነበረች። ጥናታዊ ንግግሩ እና ውይይቱ በጥቅሉ በእነአንዱዓለም አራጌ መዝገብ የተከሰሱት 24 ሰዎች ላይ ማስረጃ ሆኖ መጥቷል።

የእነአንዱዓለም አራጌ መዝገብ ብዙ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች የተከሰሱበት መዝገብ ነው። የአዲስ ነገሮቹን ዐብይ ተክለማርያም እና መስፍን ነጋሽ ጨምሮ፣ ከእስክንድር ሌላ አምስት ጋዜጠኞች በዚህ መዝገብ ተፈርዶባቸዋል።

እስክንድርን እና አንዱዓለምን ከዚያ በኋላ ያገኘኋቸው እና የማናገር ዕድል የገጠመኝ ከታሰሩ በኋላ በቃሊቲ (እኔ ራሴ ከመታሰሬ በፊት) ነው። እስክንድር ነጋ ላይ በወቅቱ ለሕወሓት ወገንተኛ የሆኑ ጦማሪዎች ያልጻፈውን ጻፈ እያሉ ሥሙን ሲያጠፉ እውነቱ ምንድን ነው ልለው ነበር የሔድኩት። በኋላ በጥቂት ቀናት ንግግር ብቻ ነፍሴን በቀናነቱ አለመለማት። እስክንድር በጣም ሲመክረኝ ከነበሩ ነገሮች ውስጥ ነውጥ-አልባ (non violent) የትግል ስልት ላይ ፍፁማዊ እምነት እንዲኖረኝ እና ለምሠራቸው ሥራዎች በሙሉ ኃላፊነቱን ለመውሰድ እንድዘጋጅ ነበር። አድርጌዋለሁ/አደርገዋለሁ ብዬ አምናለሁ። ነውጥ-አልባ ፀረ-ጭቆና ትግሌ ይፋዊ የሆነበት እና ወደፊትም የሚሆንበት ምክንያት ለእርሱ ያለኝ አድናቆት እና ክብር የሚገለጽበት መንገድ ስለሆነ ነው።

አንዱዓለም አራጌንም ከዞን ዘጠኝ ባልደረቦቼ እና ሌሎችም ጋር እንጠይቀው ነበር። ስክን ያለ፣ ሃይማኖቱን አጥባቂ እና በመብቱ የማይደራደር ሰው ከገጠማችሁ – እሱ አንዷለም አራጌ ነው። አንዱዓለምን ልንጠይቀው መጀመሪያ የሔድን ግዜ፣ ስለእኛ ጠየቀንና “አዪዪ፣… ይሄ መንግሥት ያስራችኋል” አለን። ያለውም አልቀረ፣ በዓመት ከምናምኑ ታሰርን። አንዱዓለም ከታሰረ በኋላ ሁለት አስገራሚ መጽሐፎች ጽፏል። ‘ያልተሔደበት መንገድ’ እና ‘የሀገር ፍቅር ዕዳ’ የሚሉ ናቸው። መጽሐፍቱን ማንበቡ የአንዱዓለምን ሠላማዊነት እና ባለራዕይነት ማመን ለማይፈልጉት ሳይቀር ያሳምናል።

አንዱዓለም የሁለት ወንድ ልጆች አባት ነው። በአንደኛው መጽሐፉ መግቢያ ላይ እንዲህ ይላል፣ ‘በ1998 ስታሰር [ያኔ ትዳር አልያዘም ነበር] ሳልወልድ ታሰርኩ እያልኩ ሲቆጨኝ ነበር፤ ተፈትቼ አግብቼ ከወለድኩ በኋላ ደግሞ መልሼ ስታሰር የማላሳድጋቸውን ልጆች ወልጄ እያልኩ እቆጫለሁ’ በማለት ቁጭት የማይቀር መሆኑን እና እያንዳንዱ ባለራዕይ መስዋዕትነት እንደሚከፍል ይነግረናል።

ጋዜጠኛ እስክንድርም የአንድ ልጅ አባት ነው። ጓዳው የማይጎድልበት እስክንድር ብልጭልጭ ነገር ሳያሸንፈው ያለውን ሁሉ እውነትን ለጉልቤዎች በመናገር (speaking truth to power) አሳልፎ የሰጠ ሰው ነው። እስር ቤት የተወለደው የታላቁ እስክንድር አንድያ ልጁ ናፍቆት እስክንድር እና ጋዜጠኛ ባለቤቱ ሰርካለም ፋሲል አሁን ሁለቱም ለስደት ተዳርገዋል።

ለአዲስ ዓመት ከግፍ እስር የተፈታው ‘የሙስሊሞች ጉዳይ’ ጋዜጣ አዘጋጁ ጋዜጠኛ ዩሱፍ ጌታቸው ስለ እስክንድር ነጋ አውርቶ አይጠግብም። ቃሊቲ አብረው በታሰሩበት ወቅት የተመለከተውን ሲነግረኝ፣ “እንደሱ ሥነ ስርዓት ያለው ሰው የለም። ሁሉን በዕቅድ ይመራል። እስር ቤት ውስጥ ስፖርት የሚሠራበት፣ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያነብበት እና እያንዳንዱን ነገር የሚያደርግበት የማይዛነፍ ሰዓት አለው። ከፅዳት ሠራተኞቹ ጋር በሳምንት ሁለቴ ቤት ያፀዳል። ከሰዎች ጋር አብሮ የበላበትን ሰሀን የሚያጥበው እሱ ብቻ ነው…” ~ ሽብርተኛ ተብሎ የ18 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበት እስክንድር ነጋ።

እስክንድር ሌላ ቢዝነስ እየሠራ ወይም ተሰድዶ ‘የተደላደለ’ ኑሮ መኖር ሲችል፣ ስለእውነቱ እና እምነቱ የእኔ እና የእናንተን ዕዳ ደርቦ እየከፈለ ነው። አንዱዓለም ከዐሥር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የተከሰተ ድርቅን አስመልክቶ ለተጎዱ ወገኖች መንግሥት በአስቸኳይ እንዲደርስላቸው ሲል ብቻውን ሠላማዊ ሰልፍ የወጣ ዜጋ ነው። በቲፎዞ መኖር አለመኖር፣ ጥቅም ቀርቶ ያላቸውን በማጣት እና ባለማጣት የማይሸበሩት እኒህ ፍፁም ሠላማዊ የትግል አውራዎች የማይገባቸውን ፍርድ ተሸክመው በወኅኒ፣ በአስቀያሚ አያያዝ ተጥለው ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው መንግሥት እነዚህ መሰሎቹን ንፁኃን ነፍሶች በማሰር እና በማሰቃየት የማይቀረውን ነውጥ እና መከፋፈል ሲጠራ ኖሯል። ዛሬ (ዘንድሮ) ለዚህ ሕያው ምስክር ነች።

መስከረም 3, 2009 ሁለቱ ንፁኃን ከታሰሩ እነሆ አምስት ዓመታቸው። (ምንጭ: BefeQadu Z. Hailu)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule