• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሁለት እስረኞች ወግ!

September 16, 2016 07:51 am by Editor Leave a Comment

አዋቂው፣ ዕውቁ እና ተወዳጁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ትሁቱ እና ሠላማዊው ፖለቲከኛ አንዱዓለም አራጌን በአካል ያየኋቸው በ2003 መጨረሻ በአንድነት ፓርቲ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ነበር። ያኔ በጋራ የምንጦምርበትና ለእስር የዳረገን ዞን ዘጠኝ አልተመሠረተም ነበር። ነገር ግን ጓደኞቼ እና ባልደረቦቼ Soleyana እና Atnaf ሳንተዋወቅ በፊት እዚያ እንደነበሩ ኋላ ስናወራ ሰምቻለሁ። በርካታ ሰዎች በተገኙበት ያ ስብሰባ ላይ ዛሬ ዝዋይ ወኅኒ የተጣለው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ተገኝቶ ነበር። ያቺ ስብሰባ እስክንድር ጥናታዊ ንግግር ያቀረበባት ስብሰባ ነበረች። ጥናታዊ ንግግሩ እና ውይይቱ በጥቅሉ በእነአንዱዓለም አራጌ መዝገብ የተከሰሱት 24 ሰዎች ላይ ማስረጃ ሆኖ መጥቷል።

የእነአንዱዓለም አራጌ መዝገብ ብዙ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች የተከሰሱበት መዝገብ ነው። የአዲስ ነገሮቹን ዐብይ ተክለማርያም እና መስፍን ነጋሽ ጨምሮ፣ ከእስክንድር ሌላ አምስት ጋዜጠኞች በዚህ መዝገብ ተፈርዶባቸዋል።

እስክንድርን እና አንዱዓለምን ከዚያ በኋላ ያገኘኋቸው እና የማናገር ዕድል የገጠመኝ ከታሰሩ በኋላ በቃሊቲ (እኔ ራሴ ከመታሰሬ በፊት) ነው። እስክንድር ነጋ ላይ በወቅቱ ለሕወሓት ወገንተኛ የሆኑ ጦማሪዎች ያልጻፈውን ጻፈ እያሉ ሥሙን ሲያጠፉ እውነቱ ምንድን ነው ልለው ነበር የሔድኩት። በኋላ በጥቂት ቀናት ንግግር ብቻ ነፍሴን በቀናነቱ አለመለማት። እስክንድር በጣም ሲመክረኝ ከነበሩ ነገሮች ውስጥ ነውጥ-አልባ (non violent) የትግል ስልት ላይ ፍፁማዊ እምነት እንዲኖረኝ እና ለምሠራቸው ሥራዎች በሙሉ ኃላፊነቱን ለመውሰድ እንድዘጋጅ ነበር። አድርጌዋለሁ/አደርገዋለሁ ብዬ አምናለሁ። ነውጥ-አልባ ፀረ-ጭቆና ትግሌ ይፋዊ የሆነበት እና ወደፊትም የሚሆንበት ምክንያት ለእርሱ ያለኝ አድናቆት እና ክብር የሚገለጽበት መንገድ ስለሆነ ነው።

አንዱዓለም አራጌንም ከዞን ዘጠኝ ባልደረቦቼ እና ሌሎችም ጋር እንጠይቀው ነበር። ስክን ያለ፣ ሃይማኖቱን አጥባቂ እና በመብቱ የማይደራደር ሰው ከገጠማችሁ – እሱ አንዷለም አራጌ ነው። አንዱዓለምን ልንጠይቀው መጀመሪያ የሔድን ግዜ፣ ስለእኛ ጠየቀንና “አዪዪ፣… ይሄ መንግሥት ያስራችኋል” አለን። ያለውም አልቀረ፣ በዓመት ከምናምኑ ታሰርን። አንዱዓለም ከታሰረ በኋላ ሁለት አስገራሚ መጽሐፎች ጽፏል። ‘ያልተሔደበት መንገድ’ እና ‘የሀገር ፍቅር ዕዳ’ የሚሉ ናቸው። መጽሐፍቱን ማንበቡ የአንዱዓለምን ሠላማዊነት እና ባለራዕይነት ማመን ለማይፈልጉት ሳይቀር ያሳምናል።

አንዱዓለም የሁለት ወንድ ልጆች አባት ነው። በአንደኛው መጽሐፉ መግቢያ ላይ እንዲህ ይላል፣ ‘በ1998 ስታሰር [ያኔ ትዳር አልያዘም ነበር] ሳልወልድ ታሰርኩ እያልኩ ሲቆጨኝ ነበር፤ ተፈትቼ አግብቼ ከወለድኩ በኋላ ደግሞ መልሼ ስታሰር የማላሳድጋቸውን ልጆች ወልጄ እያልኩ እቆጫለሁ’ በማለት ቁጭት የማይቀር መሆኑን እና እያንዳንዱ ባለራዕይ መስዋዕትነት እንደሚከፍል ይነግረናል።

ጋዜጠኛ እስክንድርም የአንድ ልጅ አባት ነው። ጓዳው የማይጎድልበት እስክንድር ብልጭልጭ ነገር ሳያሸንፈው ያለውን ሁሉ እውነትን ለጉልቤዎች በመናገር (speaking truth to power) አሳልፎ የሰጠ ሰው ነው። እስር ቤት የተወለደው የታላቁ እስክንድር አንድያ ልጁ ናፍቆት እስክንድር እና ጋዜጠኛ ባለቤቱ ሰርካለም ፋሲል አሁን ሁለቱም ለስደት ተዳርገዋል።

ለአዲስ ዓመት ከግፍ እስር የተፈታው ‘የሙስሊሞች ጉዳይ’ ጋዜጣ አዘጋጁ ጋዜጠኛ ዩሱፍ ጌታቸው ስለ እስክንድር ነጋ አውርቶ አይጠግብም። ቃሊቲ አብረው በታሰሩበት ወቅት የተመለከተውን ሲነግረኝ፣ “እንደሱ ሥነ ስርዓት ያለው ሰው የለም። ሁሉን በዕቅድ ይመራል። እስር ቤት ውስጥ ስፖርት የሚሠራበት፣ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያነብበት እና እያንዳንዱን ነገር የሚያደርግበት የማይዛነፍ ሰዓት አለው። ከፅዳት ሠራተኞቹ ጋር በሳምንት ሁለቴ ቤት ያፀዳል። ከሰዎች ጋር አብሮ የበላበትን ሰሀን የሚያጥበው እሱ ብቻ ነው…” ~ ሽብርተኛ ተብሎ የ18 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበት እስክንድር ነጋ።

እስክንድር ሌላ ቢዝነስ እየሠራ ወይም ተሰድዶ ‘የተደላደለ’ ኑሮ መኖር ሲችል፣ ስለእውነቱ እና እምነቱ የእኔ እና የእናንተን ዕዳ ደርቦ እየከፈለ ነው። አንዱዓለም ከዐሥር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የተከሰተ ድርቅን አስመልክቶ ለተጎዱ ወገኖች መንግሥት በአስቸኳይ እንዲደርስላቸው ሲል ብቻውን ሠላማዊ ሰልፍ የወጣ ዜጋ ነው። በቲፎዞ መኖር አለመኖር፣ ጥቅም ቀርቶ ያላቸውን በማጣት እና ባለማጣት የማይሸበሩት እኒህ ፍፁም ሠላማዊ የትግል አውራዎች የማይገባቸውን ፍርድ ተሸክመው በወኅኒ፣ በአስቀያሚ አያያዝ ተጥለው ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው መንግሥት እነዚህ መሰሎቹን ንፁኃን ነፍሶች በማሰር እና በማሰቃየት የማይቀረውን ነውጥ እና መከፋፈል ሲጠራ ኖሯል። ዛሬ (ዘንድሮ) ለዚህ ሕያው ምስክር ነች።

መስከረም 3, 2009 ሁለቱ ንፁኃን ከታሰሩ እነሆ አምስት ዓመታቸው። (ምንጭ: BefeQadu Z. Hailu)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule