
(የካቲት 66 ሕዝባዊ አብዮት 43ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ)
ኢትዮጵያ ሀገራችን ታዳጊ ሀገሮችን በተለይ አፍሪካን እንደ ቅርጫ የተቀራመቱት ቅኝ ገዥዎችና ወራሪዎችን ጥቃት መክታ የግዛት አንድነቷንና ሉዓላዊነቷን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ለማንም ባዕዳን ወራሪ ኃይል ሳትደፈርና ሳትገዛ የኖረች የማንነታችንና የክብራችን መግለጫ ናት። ዮሐንስ በመተማ፣ ቴዎድሮስ በመቅደላ፣ ምኒልክ በአድዋ እየተባለ የሚነገርላቸው፣ የሚጻፍላቸው፡ የሚዘፈንላቸው ነገስታቶች በሀገር አንድነትና በኢትዮጵያዊነት ማንነት ወራሪን ያሳፈሩና ዓለምን ያስደነቁ ኢትዮጵያዊነት የክብርና የአንድነት ተምሳሌትነቷን ያስፃፉና ያስተረኩ እስከዛሬም ሆነ ወደፊት ይህ ማንነታቸውን ታሪክ የሚያወሳላቸው ነገስታት ናቸው።
በነዚህ ነገስታቶች የአገዛዝ ዘመን የሀገር አንድነትንና የግዛት ነፃነትን በማስከበር ደረጃ በየጊዜው ስማቸው የሚጠራ ጀግኖችን ሀገራችን አስመዝግባለች። ዶጋሌ ሲነሳ አሉላ አባ ነጋ፡ መድፍ ሲነሳ ፊታውራሪ ገበየሁና ባልቻ አባ ነፍሶ፡ ስቅላት ሲታወስ በላይ ዘለቀ፡ ብልህነት ሲጠቀስ እቴጌ ጣይቱ፣ ሞኝነት ሲዜም ደጃዝማች አያሌው ብሩ፣ እምነት ለነፃነት ሲነሣ አቡነ ጴጥሮስ መሰል ጊዜ ያበቀላቸው ጀግኖች በዝማሬው፣ በተረቱ፣፡ በግጥሙ፣ በተውኔቱ ሲታወሱ ኖረዋል።
ኢትዮጵያ የተበታተነ የዘመነ መሳፍንት አገዛዝ ታሪክ አስመዝግባ በአንድ ማዕከላዊ መንግሥት ሥር ትተዳደር ዘንድ የተደረገው ትግልና የእርስ በርስ ጦርነት እንደማንኛውም ዓለም የታሪኳ አንዱ ገጽታ ቢሆንም ከሦስት ሺህ ዘመን በላይ የሚወስደን ታሪካችን ከበርካታ ሀገራት ቀዳሚ ሥፍራን ያስይዛታል። የዚህ ታሪክ ተረካቢ ነገስታት በሀገር አንድነት ከጥያቄ ባይገቡም ኢትዮጵያን በልማትና ዕድገት ጎዳና በማራመድ ለቀጣይ ትውልድ አርኣያ የምትሆን ኢትዮጵያን አቅጣጫ ማስያዙና መሰረት መጣሉ ላይ ብዙ የሚቀራቸው ነበር። ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷን ለዕድገት፣ የልጆቿን ጀግንነት ለልማትና ብልጽግና ትጠቀምበት ዘንድ ለትውልድ መሠረት የሚጥል አገዛዝ ማግኘት ተስኗታል። ምኒልክ በአድዋ፣ የኢትዮጵያ አርበኞችና፣ ጀግኖች በፋሽስት ወረራ የተቀዳጁትን ድል ለሀገር ዕድገትና ልማት ለማዋል አልታደለችም። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
Wonderful article,I have followed all this,I have been in Addis Abeba starting from the beginning of the revolution,I have eaten dinner with the cousin of my mother who was killed half a year after I left Ethiopia with general Teferi Bente,a decent person.
In 1966(1974Euro) the people rose against the emperor rule. There was no one to direct or lead the people’s movement, and it was a mass riot where each sector of society rejected the old order. Workers, teachers, students, soldiers, priests, etc. all participated in that earth shaking Ethiopian revolution. As naturally as such things develop, those capable of giving leadership emerged out of these movements. THERE WAS NO ONE DESTINED OR ENTITLED FOR LEADERSHIP. LEADERS WERE TO COME OUT OF THE MOVEMENT ITSELF.
This was the Ethiopian reality in those times. And as things progressed, the military leaders came out organized and began giving direction to the movement. Again NO ONE WAS ENTITLED OR BESTOWED BY GOD FOR LEADERSHIP. Hence there was no opportunity lost as Ethiopians used what was available and tried to work things out. That was what happened.
This idea of “lost opportunity” or the idea of “Derg usurped the leading role” or “Student were the leading part”, or such non-senses do not reflect the real process of the Ethiopian revolution.