• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጨነቀው “መንግስት”

November 16, 2017 07:44 pm by Editor Leave a Comment

እኔማ የዚህ መንግስት ባህርይ ከቶውንም ሊገባኝ አልቻለም፡፡ እንደ እኔ እንደኔ “መንግስት” ጃጅቷል ባይ ነኝ፡፡ በመጃጃት የሚታይ ስዕብና በዚህ መንግስት እያየሁ ነው፡፡ የአማራ ክልል መንግስት ጳጉሜ 3 ቀን 2009 ዓ.ም ምን እንደታየው በውል ባላውቅም ከመሬት ተነስቶ የመንግስት ተሸከርካሪ አያያዝ፣ አጠቃቀምና የንብረት አስተዳደር መመሪያ አሻሽያለሁ ብሎ በሌጣ ደብዳቤ ለመንግስት ተቋማት ሰርኩላር አስተላልፎ ነበር፡፡  በክልሉ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ተላላኪነት ለክልሉ ቢሮዎች የተላከው ደብዳቤ ከመስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ወይም የሥራ ኃላፊዎች ለሥራ ጉዳይ ክልሉን ለቀው ወደ አዲስ አበባ ሲሄዱ የሚመሩትን ተቋም ተሸከርካሪ ይዘው እንዳሄዱ የሚያሳስብና በተማከለ መንገድ በከተማው በሚዘጋጁ ተሸከርካሪዎች መጠቀም እንደሚችሉ የሚያሳውቅ ነበር፡፡

በተማከለ መንገድ በሚዘጋጁ ተሸከርካሪዎች መጠቀም የሚችሉ ብሎ ደብዳቤው ያሳወቃቸው የሥራ ኃላፊዎች የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር፣ ም/ርዕሰ መስተዳድርና በዚህ ደረጃ ያሉ ኃላፊዎች፣ የክልሉ ም/ቤት አፈ ጉባዔና ምክትል አፈ ጉባዔ፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት፣ የካቢኔ አባላት የሆኑት የቢሮ ኃላፊዎች፣ ዋና ኦዲተር፣ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ ያሉ ኃላፊዎች የዞን ዋና አስተዳዳሪዎችና የሜትሮፖሊታን ከተማ ከንቲባዎች ናቸው፡፡

የተጠቀሱት ኃላፊዎች አዲስ አበባ ለሚደረጉ ማንኛውም ስብሰባዎች ወይም ሌሎች ሥራዎች ወደ አዲስ አበባ በአይሮፕላን የሚሄዱ ከሆነ ከአይሮፕላን ማረፊያ የሚቀበላቸውና በቆይታቸው ወቅት በማዕከል አገልግሎት ለመስጠት የተዘጋጁ ተሸከርካሪዎችን  ወይም በቀን 1200 ብር ያልበለጠ የመኪና ኪራይ በሕጋዊ ደረሰኝ መጠቀም እንደሚችሉ ያተተው ቀላጤው ለከተማ አገልግሎት ተጨማሪ ተሸከርካሪ ማንቀሳቀስ እንደሌለባቸው አስረድቷል፡፡

የተሽከርካሪ ስምሪትና የማስተዳደሩን ተግባር ለክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ሥልጣን የሰጠው ይኸው መመሪያ በክልሉ የካብኔ አባላት የሆኑ ቢሮዎች ምክትል ቢሮ ኃላፊዎችና በምክትል ቢሮ ደረጃ የተሾሙ ሹማምንቶች ወደ አዲስ አበባ በአይሮፕላን የሚሄዱ ከሆነ በማዕከል በተዘጋጁ ተሸከርካሪዎች መጠቀም የማይችሉ ከሆነ በቀን ከብር 600 ያልበለጠ የመኪና ኪራይ በመጠቀም በህጋዊ ደረሰኝ ማወራረድ እንደሚችሉ ያትታል፡፡

በመመሪያው የተቀመጡትን ድንጋጌዎች ተላልፎ የተገኘ የሥራ ኃላፊ ከተፈቀደለት የገንዘብ መጠን በላይ ያለውን ወጪ በግሉ እንደሚሸፍንና በመመሪያው ከተፈቀደው ውጪ ሂሳብ ያወራረደ የመ/ቤቱ የግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደርም ተጠያቂ እንደሚሆን ያሳውቃል፡፡

ይህ ደብዳቤ በየተቋሙ ከደረሰ በኋላ መመሪያው የሚመለከታቸው የከፍተኛ አመራር ሹፌሮች ቅስማቸው በመሰበሩና መንግስት ጉሮሮአቸው ላይ በመቆሙ አለቆቻቸውን ከኤር ፖርት ለመቀበልና ለመሸኘት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ ከአንድ ተሳፋሪ ከባህር ዳር አዲስ አበባ 450 ብር የሚያገኙት የትራንስፖርት ገቢ ሲያጡ ቅሬታ አይሉት ሐዘን ኡኡታቸውን ባገኙት አጋጣሚ ማሰማት ጀመሩ፡፡

በቅሬታ መልክ የሚያስተጋቡት የተሻሻለው መመሪያ የአሽከርካሪዎች የሥራ ሁኔታ ያላገነዘበና ለይስሙላ የወጣ መመሪያ እንደሆነና ከመንግስት የሥራ ሰዓት ውጭ ከኃላፊዎች ጋር እስከ ምሽት እያመሸን፣ ቤተሰቦቻቸውን እያመላለስንና የቤት ወጪያቸውን እየገዛና ለምናደርስበት የትርፍ ሰዓት አገልግሎት አበል ሊታሰብልን ይገባል ብለዋል፡፡

የወጣው መመሪያ እርስ በርሱ እንደሚቃረን በክልሉ በየተቋማቱ ያሉ የግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ባለሙያዎች ቢናገሩም የክልሉ መንግስት ካፈርኩ አይመልሰኝ በሚል ህሳቤ መመሪያው ለመተግበር ሲነሳ በመመሪያው የተጠቀሱ ክልሉ ካብኔዎች በአገሪቱ መዲና አዲስ አበባ ከተማ በማዕከል ደረጃ በሚዘጋጀው የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የተወከሉት የወያኔው ኤፈርት ድርጅት በሚያቀርባቸው ተሸከርካሪ መሆኑን የክልሉ መንግስት ሲያውቅ መመሪያውን ማሻሻል ገባ፡፡

ሰሞኑን በየተቋማቱ የተሠራጨው የማሻሻያ ደብዳቤ የክልሉን መንግስት መጨነቅ የሚያበስር ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ከክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ በቁጥር አብክመ/ ገኢት/ክበ-01/450 በቀን 20/02/2010 ዓ.ም የተሠራጨው ደብዳቤ … በማዕከል ይዘጋጃሉ የተባሉት ተሸከርካሪዎች በግዥና በሌሎች ምክንያቶች ስለዘገዩ አመቻችተን በሌላ ደብዳቤ እስከምናሳውቃችሁ ድረስ ከዚህ በፊት በነበረው የተሽከርካሪ አጠቃቀም መመሪያ መሠረት እንዲፈጸም እናሳውቃለን ይላል፡፡

እኔን የገረመኝ ተሻሻለ የተባለው መመሪያ ሦስት ወራት ሳይሞላው ውድቅ መደረጉ ሳይሆን በማዕከል ይዘጋጃል የተባለው የትራንስፖርት አገልግሎት በወጉ ሳይቀርብ መመሪያ ለማሻሻል የገባው የአማራ ክልል ካብኔ ተግባር ነው፡፡

የክልሉ ካብኔ ውሳኔ አንድ አባባል አስታወሰኝ፡፡ አንዱ ባልንጀራውን የመጥረቢያ እጀታ በምን ተቆረጠ ብሎ ይጠይቀዋል፡፡ ተጠያቂው ባልንጀራም  በመጥረቢያ ስል መለሰ፡፡ ጠያቂውም መልሶ መጥረቢያ ከመፈጠሩ በፊት ኧረ ቀደም ቀደም ብሎ ቢጠይቀው ምላሽ አጣለት ይባላል፡፡ የክልሉ መንግስትስ ከነገረ ቀደም የመንግስት ተሸከርካሪ አያያዝ፣ አጠቃቀምና የንብረት አስተዳደር መመሪያ ማሻሻል ያስፈለገው ለምን ይሆን? የኔ ጥያቄ ነው፡፡ ምላሹ መንግስት ቢጨንቀው ነው፡፡ (ከኢንተርኔት የተገኘው ፎቶ የብአዴን ቢሮ ነው)

ጲላጦስ ከጣና ዳር (ummp4.20@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule