• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጨነቀው “መንግስት”

November 16, 2017 07:44 pm by Editor Leave a Comment

እኔማ የዚህ መንግስት ባህርይ ከቶውንም ሊገባኝ አልቻለም፡፡ እንደ እኔ እንደኔ “መንግስት” ጃጅቷል ባይ ነኝ፡፡ በመጃጃት የሚታይ ስዕብና በዚህ መንግስት እያየሁ ነው፡፡ የአማራ ክልል መንግስት ጳጉሜ 3 ቀን 2009 ዓ.ም ምን እንደታየው በውል ባላውቅም ከመሬት ተነስቶ የመንግስት ተሸከርካሪ አያያዝ፣ አጠቃቀምና የንብረት አስተዳደር መመሪያ አሻሽያለሁ ብሎ በሌጣ ደብዳቤ ለመንግስት ተቋማት ሰርኩላር አስተላልፎ ነበር፡፡  በክልሉ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ተላላኪነት ለክልሉ ቢሮዎች የተላከው ደብዳቤ ከመስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ወይም የሥራ ኃላፊዎች ለሥራ ጉዳይ ክልሉን ለቀው ወደ አዲስ አበባ ሲሄዱ የሚመሩትን ተቋም ተሸከርካሪ ይዘው እንዳሄዱ የሚያሳስብና በተማከለ መንገድ በከተማው በሚዘጋጁ ተሸከርካሪዎች መጠቀም እንደሚችሉ የሚያሳውቅ ነበር፡፡

በተማከለ መንገድ በሚዘጋጁ ተሸከርካሪዎች መጠቀም የሚችሉ ብሎ ደብዳቤው ያሳወቃቸው የሥራ ኃላፊዎች የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር፣ ም/ርዕሰ መስተዳድርና በዚህ ደረጃ ያሉ ኃላፊዎች፣ የክልሉ ም/ቤት አፈ ጉባዔና ምክትል አፈ ጉባዔ፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት፣ የካቢኔ አባላት የሆኑት የቢሮ ኃላፊዎች፣ ዋና ኦዲተር፣ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ ያሉ ኃላፊዎች የዞን ዋና አስተዳዳሪዎችና የሜትሮፖሊታን ከተማ ከንቲባዎች ናቸው፡፡

የተጠቀሱት ኃላፊዎች አዲስ አበባ ለሚደረጉ ማንኛውም ስብሰባዎች ወይም ሌሎች ሥራዎች ወደ አዲስ አበባ በአይሮፕላን የሚሄዱ ከሆነ ከአይሮፕላን ማረፊያ የሚቀበላቸውና በቆይታቸው ወቅት በማዕከል አገልግሎት ለመስጠት የተዘጋጁ ተሸከርካሪዎችን  ወይም በቀን 1200 ብር ያልበለጠ የመኪና ኪራይ በሕጋዊ ደረሰኝ መጠቀም እንደሚችሉ ያተተው ቀላጤው ለከተማ አገልግሎት ተጨማሪ ተሸከርካሪ ማንቀሳቀስ እንደሌለባቸው አስረድቷል፡፡

የተሽከርካሪ ስምሪትና የማስተዳደሩን ተግባር ለክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ሥልጣን የሰጠው ይኸው መመሪያ በክልሉ የካብኔ አባላት የሆኑ ቢሮዎች ምክትል ቢሮ ኃላፊዎችና በምክትል ቢሮ ደረጃ የተሾሙ ሹማምንቶች ወደ አዲስ አበባ በአይሮፕላን የሚሄዱ ከሆነ በማዕከል በተዘጋጁ ተሸከርካሪዎች መጠቀም የማይችሉ ከሆነ በቀን ከብር 600 ያልበለጠ የመኪና ኪራይ በመጠቀም በህጋዊ ደረሰኝ ማወራረድ እንደሚችሉ ያትታል፡፡

በመመሪያው የተቀመጡትን ድንጋጌዎች ተላልፎ የተገኘ የሥራ ኃላፊ ከተፈቀደለት የገንዘብ መጠን በላይ ያለውን ወጪ በግሉ እንደሚሸፍንና በመመሪያው ከተፈቀደው ውጪ ሂሳብ ያወራረደ የመ/ቤቱ የግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደርም ተጠያቂ እንደሚሆን ያሳውቃል፡፡

ይህ ደብዳቤ በየተቋሙ ከደረሰ በኋላ መመሪያው የሚመለከታቸው የከፍተኛ አመራር ሹፌሮች ቅስማቸው በመሰበሩና መንግስት ጉሮሮአቸው ላይ በመቆሙ አለቆቻቸውን ከኤር ፖርት ለመቀበልና ለመሸኘት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ ከአንድ ተሳፋሪ ከባህር ዳር አዲስ አበባ 450 ብር የሚያገኙት የትራንስፖርት ገቢ ሲያጡ ቅሬታ አይሉት ሐዘን ኡኡታቸውን ባገኙት አጋጣሚ ማሰማት ጀመሩ፡፡

በቅሬታ መልክ የሚያስተጋቡት የተሻሻለው መመሪያ የአሽከርካሪዎች የሥራ ሁኔታ ያላገነዘበና ለይስሙላ የወጣ መመሪያ እንደሆነና ከመንግስት የሥራ ሰዓት ውጭ ከኃላፊዎች ጋር እስከ ምሽት እያመሸን፣ ቤተሰቦቻቸውን እያመላለስንና የቤት ወጪያቸውን እየገዛና ለምናደርስበት የትርፍ ሰዓት አገልግሎት አበል ሊታሰብልን ይገባል ብለዋል፡፡

የወጣው መመሪያ እርስ በርሱ እንደሚቃረን በክልሉ በየተቋማቱ ያሉ የግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ባለሙያዎች ቢናገሩም የክልሉ መንግስት ካፈርኩ አይመልሰኝ በሚል ህሳቤ መመሪያው ለመተግበር ሲነሳ በመመሪያው የተጠቀሱ ክልሉ ካብኔዎች በአገሪቱ መዲና አዲስ አበባ ከተማ በማዕከል ደረጃ በሚዘጋጀው የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የተወከሉት የወያኔው ኤፈርት ድርጅት በሚያቀርባቸው ተሸከርካሪ መሆኑን የክልሉ መንግስት ሲያውቅ መመሪያውን ማሻሻል ገባ፡፡

ሰሞኑን በየተቋማቱ የተሠራጨው የማሻሻያ ደብዳቤ የክልሉን መንግስት መጨነቅ የሚያበስር ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ከክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ በቁጥር አብክመ/ ገኢት/ክበ-01/450 በቀን 20/02/2010 ዓ.ም የተሠራጨው ደብዳቤ … በማዕከል ይዘጋጃሉ የተባሉት ተሸከርካሪዎች በግዥና በሌሎች ምክንያቶች ስለዘገዩ አመቻችተን በሌላ ደብዳቤ እስከምናሳውቃችሁ ድረስ ከዚህ በፊት በነበረው የተሽከርካሪ አጠቃቀም መመሪያ መሠረት እንዲፈጸም እናሳውቃለን ይላል፡፡

እኔን የገረመኝ ተሻሻለ የተባለው መመሪያ ሦስት ወራት ሳይሞላው ውድቅ መደረጉ ሳይሆን በማዕከል ይዘጋጃል የተባለው የትራንስፖርት አገልግሎት በወጉ ሳይቀርብ መመሪያ ለማሻሻል የገባው የአማራ ክልል ካብኔ ተግባር ነው፡፡

የክልሉ ካብኔ ውሳኔ አንድ አባባል አስታወሰኝ፡፡ አንዱ ባልንጀራውን የመጥረቢያ እጀታ በምን ተቆረጠ ብሎ ይጠይቀዋል፡፡ ተጠያቂው ባልንጀራም  በመጥረቢያ ስል መለሰ፡፡ ጠያቂውም መልሶ መጥረቢያ ከመፈጠሩ በፊት ኧረ ቀደም ቀደም ብሎ ቢጠይቀው ምላሽ አጣለት ይባላል፡፡ የክልሉ መንግስትስ ከነገረ ቀደም የመንግስት ተሸከርካሪ አያያዝ፣ አጠቃቀምና የንብረት አስተዳደር መመሪያ ማሻሻል ያስፈለገው ለምን ይሆን? የኔ ጥያቄ ነው፡፡ ምላሹ መንግስት ቢጨንቀው ነው፡፡ (ከኢንተርኔት የተገኘው ፎቶ የብአዴን ቢሮ ነው)

ጲላጦስ ከጣና ዳር (ummp4.20@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule