• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

5 ሚሊዮን “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ተጀመረ

September 13, 2021 10:09 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለዓለም የማስረዳትና የአሸባሪውን ህወሃት የጥፋት ድርጊት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማሳየትን አላማ ያደረገው “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል።

ዘመቻው ይፋ ሲደረግ ሚኒስትሮች፣ የተለያዩ ታዋቂ ግለሰቦችና በርካታ ወጣቶች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

“የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ከዛሬ ጀምሮ አስከ መስከረም 15 ቀን 2014 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል።

“በኢትዮጵያ ላይ በተሳሳተ መልኩ የሚነዛው አሉባልታ ከእውነት የራቀ መሆኑን ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ለማሳየት በዘመቻው ይሰራል” ተብሏል።

በዚሁ ንቅናቄ ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እንዲደርስ ይሰራል ተብሏል።

በዚህ ዘመቻ ከ5 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ኀይል በአማራና በአፋር ክልል የፈጸመውን ግፍ የሚያሳይ መልዕክት ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት የሚላክ መሆኑን የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ከአማራ ሚዲያ አዳሙ ሽባባው ዘግቧል።

የአሸባሪውን ሴራ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና ለፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ለማሳወቅ የተዘጋጀው መልዕክት ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት የሚላክ መሆኑን የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አብርሃም አለኽኝ አስታውቀዋል።

አብርሃም አለኽኝ

አሸባሪውና ወራሪው ትህነግ የሀገርና ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎችን በመጣስ በገባበት ቦታ ሁሉ ምንም ዓይነት የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸውን ንጹሐን ዜጎች እየጨፈጨፈ ነው ብለዋል።

ጭፍጨፋውን ለማሳወቅ ደግሞ እንደ ሀገር 5 ሚሊዮን እንደ ክልል ደግሞ 500 ሺህ ወጣቶች የሚፈርሙበት ደብዳቤ ዛሬ የመፈረም ሥራ ተጀምሯል ነው ያሉት።

እንደ ኀላፊው ገለጻ “በአማራ ሕዝብ ላይ ሒሳብ አወራርዳለሁ” ብሎ አውጆ የተነሳው የሽብርተኛው የትህነግ ወራሪ ቡድን በአማራ ሕዝብ ላይ ከፍተኛ ዘረፋ፣ ግድያ፣ ማፈናቀልምና አስገድዶ መድፈር ተግባራትን ፈጽሟል፤ ዜጎች የሚገለገሉበትን የትምህርት፣ የጤና እና የሃይማኖት ተቋማትንም ዘርፏል፤ ከፍተኛ ውድመትም አድርሷል ብለዋል። አሸባሪ ቡድኑ በአፋር ሕዝብ ላይ ተመሳሳይ ግፍ መፈጸሙን ጠቅሰዋል።

ወደ ነጩ ቤተመንግሥት የሚላከው ደብዳቤም የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን የሠራውን ግፍ ማስረጃ የያዘ መሆኑን አቶ አብርሃም አስታውቀዋል።

ቡድኑ የሠራውን ግፍ እና ወንጀል የበለጸጉ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እና ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በተሳሳተ መንገድ እየተረዱት ነው ብለዋል።

ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት የሚላከው ደብዳቤ ዓለም አቀፍ ብዙኃን መገናኛ ተቋማት ከተጎጂዎች ጎን እንዲቆሙ ጥሪ የሚቀርብበት፣ ወራሪው የፈጸማቸው ግፎች የሚጋለጡበት እንደሆነ ነው አቶ አብርሃም የገለጹት። “ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገራት በሽብርተኛው ትህነግ መወረራችንን ሊያውቁ ይገባል” ያሉት አቶ አብርሃም አሸባሪው ትህነግ በወረራቸው የክልሉ አካባቢዎች ሁሉ የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት ጥሷል፤ የተሳሳተ መረጃ በመያዝ የጠላት የክህደት ፖለቲካ አራማጆች እየኾኑ ነው ብለዋል።

የግፉዓንን መልዕክት በያዘው ደብዳቤ ላይ ምሁራን፣ ወጣቶችን እና ሁሉም የክልሉ ነዋሪዎች በመፈረም ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት እንዲላክ መረባረብ እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ አብርሃም እንዳሉት በኢትዮጵያ እየተካሄደ የሚገኘው ጦርነት ራሳችንን ለመከላከል የሚደረግ ነው፤ ጦርነቱ በአጭር ጊዜ ይጠናቀቃል፤ እናሽነፋለንም ብለዋል።

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ጋሻው ተቀባ እንዳስታወቀው ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት የሚላከው ደብዳቤ የፊርማ ሥነ ሥርዓት እስከ መስከረም 10 ይካሄዳል። መስከረም 15 ደግሞ ወደ አሜሪካ ይላካል ብሏል።

በሂደቱም በወረዳ ደረጃ እስከ 1 ሺህ 500፣ በዞን ደረጃ እስከ 2 ሺህ፣ በትልልቅ ከተሞች ደግሞ ከ50 ሺህ እስከ 100 ሺህ ሰዎች ይሳተፋሉ ነው ያለው። በዚህም ሽብርተኛው የትህነግ ወራሪ ቡድን የፈጸመውን ግፍ እና ወንጀል ያልተረዳው የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲገነዘብ የሚደረግበት ነው ብሏል። ይህም ዜጎች በትዊተር የሚያደርጉትን ዘመቻ የሚያጠናክር እንደሆነም ኀላፊው ገልጿል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Ethiopia, ethiopian terrorists, joe biden, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule