• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

5 ሚሊዮን “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ተጀመረ

September 13, 2021 10:09 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለዓለም የማስረዳትና የአሸባሪውን ህወሃት የጥፋት ድርጊት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማሳየትን አላማ ያደረገው “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል።

ዘመቻው ይፋ ሲደረግ ሚኒስትሮች፣ የተለያዩ ታዋቂ ግለሰቦችና በርካታ ወጣቶች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

“የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ከዛሬ ጀምሮ አስከ መስከረም 15 ቀን 2014 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል።

“በኢትዮጵያ ላይ በተሳሳተ መልኩ የሚነዛው አሉባልታ ከእውነት የራቀ መሆኑን ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ለማሳየት በዘመቻው ይሰራል” ተብሏል።

በዚሁ ንቅናቄ ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እንዲደርስ ይሰራል ተብሏል።

በዚህ ዘመቻ ከ5 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ኀይል በአማራና በአፋር ክልል የፈጸመውን ግፍ የሚያሳይ መልዕክት ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት የሚላክ መሆኑን የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ከአማራ ሚዲያ አዳሙ ሽባባው ዘግቧል።

የአሸባሪውን ሴራ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና ለፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ለማሳወቅ የተዘጋጀው መልዕክት ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት የሚላክ መሆኑን የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አብርሃም አለኽኝ አስታውቀዋል።

አብርሃም አለኽኝ

አሸባሪውና ወራሪው ትህነግ የሀገርና ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎችን በመጣስ በገባበት ቦታ ሁሉ ምንም ዓይነት የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸውን ንጹሐን ዜጎች እየጨፈጨፈ ነው ብለዋል።

ጭፍጨፋውን ለማሳወቅ ደግሞ እንደ ሀገር 5 ሚሊዮን እንደ ክልል ደግሞ 500 ሺህ ወጣቶች የሚፈርሙበት ደብዳቤ ዛሬ የመፈረም ሥራ ተጀምሯል ነው ያሉት።

እንደ ኀላፊው ገለጻ “በአማራ ሕዝብ ላይ ሒሳብ አወራርዳለሁ” ብሎ አውጆ የተነሳው የሽብርተኛው የትህነግ ወራሪ ቡድን በአማራ ሕዝብ ላይ ከፍተኛ ዘረፋ፣ ግድያ፣ ማፈናቀልምና አስገድዶ መድፈር ተግባራትን ፈጽሟል፤ ዜጎች የሚገለገሉበትን የትምህርት፣ የጤና እና የሃይማኖት ተቋማትንም ዘርፏል፤ ከፍተኛ ውድመትም አድርሷል ብለዋል። አሸባሪ ቡድኑ በአፋር ሕዝብ ላይ ተመሳሳይ ግፍ መፈጸሙን ጠቅሰዋል።

ወደ ነጩ ቤተመንግሥት የሚላከው ደብዳቤም የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን የሠራውን ግፍ ማስረጃ የያዘ መሆኑን አቶ አብርሃም አስታውቀዋል።

ቡድኑ የሠራውን ግፍ እና ወንጀል የበለጸጉ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እና ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በተሳሳተ መንገድ እየተረዱት ነው ብለዋል።

ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት የሚላከው ደብዳቤ ዓለም አቀፍ ብዙኃን መገናኛ ተቋማት ከተጎጂዎች ጎን እንዲቆሙ ጥሪ የሚቀርብበት፣ ወራሪው የፈጸማቸው ግፎች የሚጋለጡበት እንደሆነ ነው አቶ አብርሃም የገለጹት። “ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገራት በሽብርተኛው ትህነግ መወረራችንን ሊያውቁ ይገባል” ያሉት አቶ አብርሃም አሸባሪው ትህነግ በወረራቸው የክልሉ አካባቢዎች ሁሉ የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት ጥሷል፤ የተሳሳተ መረጃ በመያዝ የጠላት የክህደት ፖለቲካ አራማጆች እየኾኑ ነው ብለዋል።

የግፉዓንን መልዕክት በያዘው ደብዳቤ ላይ ምሁራን፣ ወጣቶችን እና ሁሉም የክልሉ ነዋሪዎች በመፈረም ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት እንዲላክ መረባረብ እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ አብርሃም እንዳሉት በኢትዮጵያ እየተካሄደ የሚገኘው ጦርነት ራሳችንን ለመከላከል የሚደረግ ነው፤ ጦርነቱ በአጭር ጊዜ ይጠናቀቃል፤ እናሽነፋለንም ብለዋል።

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ጋሻው ተቀባ እንዳስታወቀው ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት የሚላከው ደብዳቤ የፊርማ ሥነ ሥርዓት እስከ መስከረም 10 ይካሄዳል። መስከረም 15 ደግሞ ወደ አሜሪካ ይላካል ብሏል።

በሂደቱም በወረዳ ደረጃ እስከ 1 ሺህ 500፣ በዞን ደረጃ እስከ 2 ሺህ፣ በትልልቅ ከተሞች ደግሞ ከ50 ሺህ እስከ 100 ሺህ ሰዎች ይሳተፋሉ ነው ያለው። በዚህም ሽብርተኛው የትህነግ ወራሪ ቡድን የፈጸመውን ግፍ እና ወንጀል ያልተረዳው የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲገነዘብ የሚደረግበት ነው ብሏል። ይህም ዜጎች በትዊተር የሚያደርጉትን ዘመቻ የሚያጠናክር እንደሆነም ኀላፊው ገልጿል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Ethiopia, ethiopian terrorists, joe biden, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule