• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ልማታዊ ሙስና?

December 10, 2014 06:51 am by Editor 1 Comment

ባለፈው ዓርብ በተከፈተው የመሬት ሊዝ ጨረታ በአንድ ካሬ ሜትር 305 ሺሕ ብር ቀረበ፡፡ ይህ ዋጋ በከተማው ታሪክ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ የሊዝ ጨረታን የወቅቱ አነጋጋሪ ክስተት አድርጓል፡፡

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መርካቶ በርበሬ አካባቢ 449 ካሬ ሜትር ቦታ ለጨረታ ቀርቧል፡፡ በካሬ ሜትር የቀረበው ገንዘብ ሲሰላ ይህ አነስተኛ ቦታ 136.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ሆኗል፡፡ 20 በመቶ ብቻ የተከፈለበት ይህ መሬት ከነወለዱ እስከ 300 ሚሊዮን ብር በ30 ዓመት ሊደርስ እንደሚችል ባለሙያዎቹ ገልጸዋል፡፡ ይህ ክስተት ለአዲስ አበባ ሊዝ ሥሪት ባለሙያዎች እንዲሁም በጨረታው ለታደሙ ባለሀብቶች የቀረበው ዋጋ ብዥታን ፈጥሯል፡፡ በጨረታው ላይ ሁለተኛ ሆኖ የቀረበው ዋጋም ከዚህ ቀደም ቀርቦ የማያውቅ ሲሆን፣ የቀረበውም በካሬ ሜትር 288 ሺሕ ከ90 ሳንቲም ነው፡፡ “በአዲስ አበባ የሊዝ ዋጋ ላይ ቆም ተብሎ ካልታሰበ አደገኛ ውጤት ሊኖረው ይችላል፤” ሲሉ የአዲስ አበባ አስተዳደር የሊዝ ባለሙያ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

መርካቶ በርበሬ ተራ ለሚገኘው ለዚህ 449 ካሬ ሜትር ቦታ በካሬ ሜትር 305 ሺሕ ብር ያቀረበው ዝዋይ ኢንተርናሽናል የተባለ ኩባንያ ነው፡፡ ይህ ኩባንያ ቀደም ሲል ከዚህ ቦታ አጠገብ መሬት በሊዝ ገዝቶ የንግድ ማዕከል ያቋቋመ እንደሆነ ታውቋል፡፡

ለዚሁ ቦታ በካሬ ሜትር 288 ሺሕ ከ90 ሳንቲም ያቀረበው ደግሞ ኤንኤስኤ የተባለ ኩባንያ ነው፡፡ ይህ ኩባንያም ቦታውን ማሸነፍ ባይችልም ያቀረበው ገንዘብ ግን በከተማው ታሪክ ቀርቦ የማያውቅ ነው፡፡ በከተማው ታሪክ ክብረ ወሰን ሆኖ የቆየው ከወራት በፊት በስምንተኛው ዙር ሊዝ ጨረታ ቦሌ አካባቢ ከኤድናሞል ወረድ ብሎ የሚገኝ ቦታ ነበር፡፡ ቦታው 158 ካሬ ሜትር ስፋት ሲኖረው፣ ለዚህ ቦታ በካሬ ሜትር 65 ሺሕ ብር ያቀረበው ኤስኤንአይ ትሬዲንግ ነው፡፡

በ11ኛው ሊዝ ጨረታ በካሬ ሜትር የቀረበው 305 ሺሕ ብር ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቦ ከነበረው 65,000 ብር በ4,692 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ በርካታ የመሬት ሥሪት ባለሙያዎች ይህ ዋጋ ምናልባት ለዓመታት ክብረ ወሰን ሆኖ ይቆያል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸው፣ ነገር ግን በከተማው የሚገኙ አንዳንድ ነጋዴዎች የሚወስዱትን አደጋ መገመት የሚያስቸግር በመሆኑ በቅርቡ አይሻሻልም ማለት አይቻልም ብለዋል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ባለሙያዎች እንደሚሉት ይህ ገንዘብ በማንኛውም መመዘኛ ጤነኛ ኢኮኖሚያዊ አካሄድ አይደለም ካሉ በኋላ፣ ሁኔታው ቆም ተብሎ ሊታሰብበት የሚገባ ነው ይላሉ፡፡

አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ለጨረታ የቀረበው ይህ ቦታ ብቻ ነው፡፡ ቦሌ ክፍለ ከተማ ላይ ደግሞ 57 ቦታዎች ለጨረታ ቀርበዋል፡፡ ሚሊኒየም አዳራሽ ጀርባ የወጡ ሁለት ቦታዎች ከፍተኛ ዋጋ ቀርቦላቸዋል፡፡

በዚህ ቦታ ለወጣ 400 ካሬ ሜትር ቦታ ቤተልሔም ብርሃን የተባሉ ባለሀብት፣ በካሬ ሜትር 55,244 ብር አቅርበዋል፡፡ ወ/ሮ መኪያ የተባሉ ባለሀብት ደግሞ ለ403 ካሬ ሜትር ቦታ በካሬ ሜትር 51,111 ብር አቅርበዋል፡፡

ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ሁለት ቦታዎች ለጨረታ የቀረቡ ሲሆን፣ 12,000 እና 15,000 በካሬ ሜትር ቀርቦላቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቦሌ ክፍለ ከተማ በብዛት ኮንዶሚኒየም ቤቶች እየተገነቡበት ባለው ቀጠና በተለይም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሠራተኞቹ መኖሪያ ቤት እየገነባ ባለበት አካባቢ 52 ቦታዎች ለጨረታ ቀርበዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ቦታዎች እስከ 15,000 ብር የቀረበላቸው ሲሆን፣ ራሕማ ጀማል የተባሉ ባለሀብት በዚህ አካባቢ በካሬ ሜትር 15,221 ብር ሲያቀርቡ ከዚሁ ቦታ አጠገብ ዘገየ ዘመዴ የተባሉ ባለሀብት 2,489 ብር አቅርበዋል፡፡

በዚህ አካባቢ ብዙም ጨረታ ወጥቶ የማያውቅ በመሆኑ የቦታውን ዋጋ ለመስጠት ባለሙያዎች ተቸግረው ነበር፡፡ በሁለቱ ባለሀብቶች መካከልም የቀረበው ዋጋ ልዩነቱ ከዚህ መነሻነት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ በዚሁ አካባቢ በተነፃፃሪ ዝቅተኛ ዋጋ አቅርበው አሸናፊ የሆኑ አሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ውብነሽ ሀብቴ በካሬ ሜትር 3,189 ብር፣ አሰፋ ታምሬ በካሬ 2,689 ብር፣ ብርቄ መለስ 1,805 ብር ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ እንዲሁ የዋጋ መነሳት የታየበት ሲሆን፣ በካሬ ሜትር 18,000 ብር ቀርቧል፡፡

የአዲስ አበባ የመሬት ዋጋ ንረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄድ ላይ ሲሆን፣ ለዚህ ምክንያቱ አስተዳደሩ እንደሆነ ይጠቀሳል፡፡ የከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ኃይሌ በቅርብ ከኢብኮ ጋር ባደረጉት ቆይታ የመሬት ዋጋ እንዲንር መንግሥት እንደማይፈልግና አልሚዎች ያላቸውን ካፒታል መሬት በመግዛት ሳይሆን፣ ለልማቱ በማዋል ማደግ እንደሚኖርባቸው አስታውቀው ነበር፡፡ ነገር ግን የከተማው የመሬት ዋጋ በየጊዜው እየጨመረ በመሄድ ላይ መገኘቱ ለበርካታ ኢኮኖሚያዊ ችግሮ ሊዳርግ እንደሚችል በመግለጽ ባለሙያዎች ማሳሰቢያ እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Abe says

    December 10, 2014 08:20 pm at 8:20 pm

    This shows how the country is in crisis and leading abnormal Economy. Where did all these so called ” Investors” brought the money from while the people of the country is languishing in abject poverty and lacks in even daily food items to survive?What was the source?and were there any justifiable and plausible economic activities going on in the country as such in the past two and half decades that could earn/reward them to offer and spend this much on a piece of land at this time except corruption? Its shame and even immoral for these biders to rush to grab the poors land while many are seen thrown on the streets and looking for food-is that to improve the fate of the many poor or to dance on thier death bed?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule