• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በ5 ዓመቱ ሕፃን ላይ የግብረ-ሰዶም ጥቃት የፈፀመው በ20 ዓመት እሥራት ተቀጣ

December 25, 2014 01:07 am by Editor 1 Comment

አስራ ሦስት ዓመት ባልሞላው ሕፃን ላይ የግብረ ሰዶም ጥቃት ፈፅሟል ሲል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሠረተበት የ23 ዓመቱ ወጣት ሳሙኤል መርዕድ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ20 ዓመት እሥራት እንዲቀጣ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት ከትናንት በስቲያ ታህሳስ 13 ቀን 2007 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔ አስተላለፈበት።

ዐቃቤ ሕግ ለፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት በየካቲት 06 ቀን 2006 ዓ.ም ባቀረበው ክስ ላይ እንደዘረዘረው፤ የ23 ዓመቱ ወጣት ከእርሱ ጋር አንድ አይነት ፆታ ባለውና ዕድሜው ከ13 ዓመት በታች በሆነው ታዳጊ ልጅ ላይ የግብረ-ሰዶም ጥቃት ለማድረስ አስቦ ተንቀሳቅሷል ይላል። በዚህም መሠረት በጥቅምት 24 ቀን 2006 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 8፡00 ሲሆን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 01/02/03 ክልል ልዩ ቦታው ጌሾ ተራ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ እድሜው አምስት ዓመት በሆነው የግል ተበዳዩን ህጻን ኳስ ከሚጫወትበት ሜዳ ላይ ጠርቶ፤ ጭር ወዳለና ሰው ወደማይዘዋወርበት ቦታ በመውሰድ ሱሪውን አውልቆ የግብረ-ሰዶም ጥቃት ፈፅሞበታል ሲል ያትታል።

በዚህም ሳያበቃ ተከሳሽ የ5 ዓመቱን የግል ተበዳይ ህዳር 1 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ሲሆን ከላይ በተጠቀሰው ቦታ ተመሳሳዩን የግብረ-ሰዶም ጥቃት በህፃኑ ላይ ሊፈፅምበት ሲሰናዳ ሰው ደርሶ ያስጣለው በመሆኑ በፈፀመው ለአካለ መጠን ባልደረሱ ልጆች ላይ የሚፈፀም የግብረ-ሰዶም ጥቃት ወንጀል ክስ ተመስርቶበታል ይላል።

የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎትም፣ የዐቃቤ ሕግን ክስ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች መርምሮ ሲያበቃ፤ ተከሳሹ የተመሰረተበትን ክስ በሚገባ ሊከላከል ባለመቻሉ ታህሳስ 8 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛነቱ ተረጋግጧል።

በዚህም መሠረት የግራቀኙን የቅጣት አስተያየት ያዳመጠው ችሎቱ፤ ተከሳሽ ምንም ዓይነት የቅጣት ማቅለያ አለማቅረቡን እና ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ ድርጊቱ በተደጋጋሚ ጊዜ የተፈፀመ ስለመሆኑ በመጥቀሱ የቅጣት ማክበጃ በማቅረቡ፤ የወንጀሉን መካከለኛ ደረጃነት በአንድ እርከን ከፍ አድርጎታል። በመሆኑም ተከሳሹ ዕድሜው 13 ዓመት ባልሞላው እና የአምስት ዓመት ዕድሜ ባለው ህጻን ልጅ ላይ በፈፀመው የግብረ-ሰዶም ጥቃት ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ20 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ሲል ችሎቱ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል። (ምንጭ: ሰንደቅ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Sebsibe wolde says

    December 27, 2014 08:01 am at 8:01 am

    min malet new ethiopia wodetnew tadiya le akima adam lederesut tefekdoal maletnw.??? Min malet new min maletnw abazachihut ahunw tekawumo yaderegewun maymesil kitat tikauna ke 13 amet betachnw tilalachihu tadiya keziya belay tefekdoal maletnw woy ” ethiopia hagare monginesh telala yemotalish kerto yegedelesh bala”

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule