• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በ5 ዓመቱ ሕፃን ላይ የግብረ-ሰዶም ጥቃት የፈፀመው በ20 ዓመት እሥራት ተቀጣ

December 25, 2014 01:07 am by Editor 1 Comment

አስራ ሦስት ዓመት ባልሞላው ሕፃን ላይ የግብረ ሰዶም ጥቃት ፈፅሟል ሲል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሠረተበት የ23 ዓመቱ ወጣት ሳሙኤል መርዕድ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ20 ዓመት እሥራት እንዲቀጣ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት ከትናንት በስቲያ ታህሳስ 13 ቀን 2007 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔ አስተላለፈበት።

ዐቃቤ ሕግ ለፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት በየካቲት 06 ቀን 2006 ዓ.ም ባቀረበው ክስ ላይ እንደዘረዘረው፤ የ23 ዓመቱ ወጣት ከእርሱ ጋር አንድ አይነት ፆታ ባለውና ዕድሜው ከ13 ዓመት በታች በሆነው ታዳጊ ልጅ ላይ የግብረ-ሰዶም ጥቃት ለማድረስ አስቦ ተንቀሳቅሷል ይላል። በዚህም መሠረት በጥቅምት 24 ቀን 2006 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 8፡00 ሲሆን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 01/02/03 ክልል ልዩ ቦታው ጌሾ ተራ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ እድሜው አምስት ዓመት በሆነው የግል ተበዳዩን ህጻን ኳስ ከሚጫወትበት ሜዳ ላይ ጠርቶ፤ ጭር ወዳለና ሰው ወደማይዘዋወርበት ቦታ በመውሰድ ሱሪውን አውልቆ የግብረ-ሰዶም ጥቃት ፈፅሞበታል ሲል ያትታል።

በዚህም ሳያበቃ ተከሳሽ የ5 ዓመቱን የግል ተበዳይ ህዳር 1 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ሲሆን ከላይ በተጠቀሰው ቦታ ተመሳሳዩን የግብረ-ሰዶም ጥቃት በህፃኑ ላይ ሊፈፅምበት ሲሰናዳ ሰው ደርሶ ያስጣለው በመሆኑ በፈፀመው ለአካለ መጠን ባልደረሱ ልጆች ላይ የሚፈፀም የግብረ-ሰዶም ጥቃት ወንጀል ክስ ተመስርቶበታል ይላል።

የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎትም፣ የዐቃቤ ሕግን ክስ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች መርምሮ ሲያበቃ፤ ተከሳሹ የተመሰረተበትን ክስ በሚገባ ሊከላከል ባለመቻሉ ታህሳስ 8 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛነቱ ተረጋግጧል።

በዚህም መሠረት የግራቀኙን የቅጣት አስተያየት ያዳመጠው ችሎቱ፤ ተከሳሽ ምንም ዓይነት የቅጣት ማቅለያ አለማቅረቡን እና ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ ድርጊቱ በተደጋጋሚ ጊዜ የተፈፀመ ስለመሆኑ በመጥቀሱ የቅጣት ማክበጃ በማቅረቡ፤ የወንጀሉን መካከለኛ ደረጃነት በአንድ እርከን ከፍ አድርጎታል። በመሆኑም ተከሳሹ ዕድሜው 13 ዓመት ባልሞላው እና የአምስት ዓመት ዕድሜ ባለው ህጻን ልጅ ላይ በፈፀመው የግብረ-ሰዶም ጥቃት ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ20 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ሲል ችሎቱ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል። (ምንጭ: ሰንደቅ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Sebsibe wolde says

    December 27, 2014 08:01 am at 8:01 am

    min malet new ethiopia wodetnew tadiya le akima adam lederesut tefekdoal maletnw.??? Min malet new min maletnw abazachihut ahunw tekawumo yaderegewun maymesil kitat tikauna ke 13 amet betachnw tilalachihu tadiya keziya belay tefekdoal maletnw woy ” ethiopia hagare monginesh telala yemotalish kerto yegedelesh bala”

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule