• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

100% ደፋኝ “ጎበዞች”

June 21, 2015 08:01 pm by Editor Leave a Comment

በ1994ዓም የኢራቁ ፕሬዚዳንት ሳዳም ሁሴን “በምርጫ” 100% ደፍነው ነበር፡፡ ያለፈው ዓመት ደግሞ የሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ-ኧን ያለአንዳች ተቀናቃኝ ባደረጉት “ከፍተኛ ትንቅንቅ” በነበረበት የምርጫ ውድድር ብቻቸውን ተወዳድረው በመጨረሻው ላይ ትንፋሻቸውን ይዘው 100% ለመድፈን በቅተዋል፡፡

ሳዳም 100 ከደፈኑ በኋላ ብዙም አልቆዩም፡፡ በሌላ በኩል የቀድሞው የሰሜን ኮሪያ ታላቁ ባለራዕይ መሪ ኪም ጆንግ ኢል ከልጃቸው ኪም ጆንግ-ኧን በ0.1% በመበለጥ በ2001ዓም 99.9% ያገኙ “ጎበዝ” ነበሩ፡፡

የኩባው ራዑል ካስትሮ በ2000ዓም 99.4% ሲያገኙ የሶሪያው ባሽር አል አሳድ 97.6% ያስቆጠሩ ሌላው “ደፋኝ” ናቸው፡፡ የቱርክሜኒስታኑ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በ1984 እንዲሁም የቼችኒያው የተባበሩት ሩሲያ ፓርቲ በ2003ዓም 99.5% ያስቆጠሩ ሌሎቹ “ጎበዞች” ናቸው፡፡ በ1996ዓም በጆርጂያ ሚኻኤል ሳካሽቪሊ ሌላው 96% ያገኙ ታታሪ “ተመራጭ” ናቸው፡፡

በአምባገነን አገዛዞች ውስጥ የሚደረግ ምርጫ አንድ ተወዳዳሪ ራሱን በማቅረብ የሚወዳደር ከመሆኑ ባሻገር መራጮች የሚሰጣቸው ምርጫ አምባገነኑን መምረጥ ወይም ስቃይና መከራ መቀበል ነው፡፡ አንዳንዶቹ አምባገነኖች “ፉክክር” ተደርጎ ነበር ለማስባል “ታማኝ ተፎካካሪዎችን” ራሳቸው እንደሚፈጥሩና “ምርጫው ፍትሃዊ፣ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሁም የምርጫ መስፈርቶችን ያሟላ” እንዲመስል እንደሚያደርጉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በግላስጎው ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንቲስት የሆኑት ቶማስ ሉንድበርግ ሲናገሩ “ከሁለት ሦስተኛ በላይ ድምጽ አግኝቶ በማንኛውም ምርጫ የሚያል (ፓርቲ) ሲኖር ጥርጣሬ ሊያስነሳ ይገባል” ብለዋል፡፡ ምክንያቱን ሲጠቅሱም በፍትሃዊና ሰላማዊ ምርጫ ይህ ዓይነቱ ውጤት ያልተለመደ ስለሆነ ነው ይላሉ፡፡ የተበታተኑ (ኅብረት ያልፈጠሩ) የተቀናቃኝ ፓርቲዎች በሚኖሩበት ምርጫ የሚገኘው ውጤት 60-80% ሊያልፍ አይችልም ይላሉ፡፡

አምባገነናዊ ሥርዓቶች የሚጋልቡት ባቡር የታሰበበት መድረሻ እንደሚደርስ አምባገነኖቹ እርግጠኞች ናቸው፡፡ ባቡሩ የሚያውቀው ጣቢያ መኖሩን ብቻ ነው፡፡ አልፎ ስለመጣው ሃዲድና መሰል ጉዳዮች የሚያውቀው አንዳች ነገር የለም፡፡ መድረሻ ጣቢያ እንዳለው ያውቃል፤ አሁን ካለበት ጣቢያ እስከመድረሻው ጣቢያዎች እንዳሉ ያውቃል፡፡ የመጨረሻ ጣቢያ ስለመድረሱ ግን ምንም በእርግጠኝነት የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ ሃዲዱ እየሰራ ይሁን፣ ያደርሰው ይሆን፣ መንገድ ላይ አደጋ ይኑር፣ … ምንም እርግጠኛ ሆኖ የሚያውቀው ነገር የለም፡፡

“ስለ ክብር አልባ ታላቅነት፣ ጥበብ አልባ ሃብት፣ ሕግ አልባ ኃይልና ሥልጣን ታሪክ ምን ይላል? መልሱ በባቢሎን፣ በሜዶንና ፋርስ፣ በግሪክ እንዲሁም በሮም ታላላቅ ግዛተ አጼዎች መገርሰስ በተደጋጋሚ ተነግሯል፡፡ እነዚህ አራት ተከታታይ ዓለምን የገዙ ኃያላን ነበሩ፡፡ አሁን በምን ሁኔታና የት ይሆን ያሉት?” ኦርሰን ኤፍ ዊትኒይ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule