• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

100% ደፋኝ “ጎበዞች”

June 21, 2015 08:01 pm by Editor Leave a Comment

በ1994ዓም የኢራቁ ፕሬዚዳንት ሳዳም ሁሴን “በምርጫ” 100% ደፍነው ነበር፡፡ ያለፈው ዓመት ደግሞ የሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ-ኧን ያለአንዳች ተቀናቃኝ ባደረጉት “ከፍተኛ ትንቅንቅ” በነበረበት የምርጫ ውድድር ብቻቸውን ተወዳድረው በመጨረሻው ላይ ትንፋሻቸውን ይዘው 100% ለመድፈን በቅተዋል፡፡

ሳዳም 100 ከደፈኑ በኋላ ብዙም አልቆዩም፡፡ በሌላ በኩል የቀድሞው የሰሜን ኮሪያ ታላቁ ባለራዕይ መሪ ኪም ጆንግ ኢል ከልጃቸው ኪም ጆንግ-ኧን በ0.1% በመበለጥ በ2001ዓም 99.9% ያገኙ “ጎበዝ” ነበሩ፡፡

የኩባው ራዑል ካስትሮ በ2000ዓም 99.4% ሲያገኙ የሶሪያው ባሽር አል አሳድ 97.6% ያስቆጠሩ ሌላው “ደፋኝ” ናቸው፡፡ የቱርክሜኒስታኑ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በ1984 እንዲሁም የቼችኒያው የተባበሩት ሩሲያ ፓርቲ በ2003ዓም 99.5% ያስቆጠሩ ሌሎቹ “ጎበዞች” ናቸው፡፡ በ1996ዓም በጆርጂያ ሚኻኤል ሳካሽቪሊ ሌላው 96% ያገኙ ታታሪ “ተመራጭ” ናቸው፡፡

በአምባገነን አገዛዞች ውስጥ የሚደረግ ምርጫ አንድ ተወዳዳሪ ራሱን በማቅረብ የሚወዳደር ከመሆኑ ባሻገር መራጮች የሚሰጣቸው ምርጫ አምባገነኑን መምረጥ ወይም ስቃይና መከራ መቀበል ነው፡፡ አንዳንዶቹ አምባገነኖች “ፉክክር” ተደርጎ ነበር ለማስባል “ታማኝ ተፎካካሪዎችን” ራሳቸው እንደሚፈጥሩና “ምርጫው ፍትሃዊ፣ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሁም የምርጫ መስፈርቶችን ያሟላ” እንዲመስል እንደሚያደርጉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በግላስጎው ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንቲስት የሆኑት ቶማስ ሉንድበርግ ሲናገሩ “ከሁለት ሦስተኛ በላይ ድምጽ አግኝቶ በማንኛውም ምርጫ የሚያል (ፓርቲ) ሲኖር ጥርጣሬ ሊያስነሳ ይገባል” ብለዋል፡፡ ምክንያቱን ሲጠቅሱም በፍትሃዊና ሰላማዊ ምርጫ ይህ ዓይነቱ ውጤት ያልተለመደ ስለሆነ ነው ይላሉ፡፡ የተበታተኑ (ኅብረት ያልፈጠሩ) የተቀናቃኝ ፓርቲዎች በሚኖሩበት ምርጫ የሚገኘው ውጤት 60-80% ሊያልፍ አይችልም ይላሉ፡፡

አምባገነናዊ ሥርዓቶች የሚጋልቡት ባቡር የታሰበበት መድረሻ እንደሚደርስ አምባገነኖቹ እርግጠኞች ናቸው፡፡ ባቡሩ የሚያውቀው ጣቢያ መኖሩን ብቻ ነው፡፡ አልፎ ስለመጣው ሃዲድና መሰል ጉዳዮች የሚያውቀው አንዳች ነገር የለም፡፡ መድረሻ ጣቢያ እንዳለው ያውቃል፤ አሁን ካለበት ጣቢያ እስከመድረሻው ጣቢያዎች እንዳሉ ያውቃል፡፡ የመጨረሻ ጣቢያ ስለመድረሱ ግን ምንም በእርግጠኝነት የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ ሃዲዱ እየሰራ ይሁን፣ ያደርሰው ይሆን፣ መንገድ ላይ አደጋ ይኑር፣ … ምንም እርግጠኛ ሆኖ የሚያውቀው ነገር የለም፡፡

“ስለ ክብር አልባ ታላቅነት፣ ጥበብ አልባ ሃብት፣ ሕግ አልባ ኃይልና ሥልጣን ታሪክ ምን ይላል? መልሱ በባቢሎን፣ በሜዶንና ፋርስ፣ በግሪክ እንዲሁም በሮም ታላላቅ ግዛተ አጼዎች መገርሰስ በተደጋጋሚ ተነግሯል፡፡ እነዚህ አራት ተከታታይ ዓለምን የገዙ ኃያላን ነበሩ፡፡ አሁን በምን ሁኔታና የት ይሆን ያሉት?” ኦርሰን ኤፍ ዊትኒይ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule