• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

100% ደፋኝ “ጎበዞች”

June 21, 2015 08:01 pm by Editor Leave a Comment

በ1994ዓም የኢራቁ ፕሬዚዳንት ሳዳም ሁሴን “በምርጫ” 100% ደፍነው ነበር፡፡ ያለፈው ዓመት ደግሞ የሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ-ኧን ያለአንዳች ተቀናቃኝ ባደረጉት “ከፍተኛ ትንቅንቅ” በነበረበት የምርጫ ውድድር ብቻቸውን ተወዳድረው በመጨረሻው ላይ ትንፋሻቸውን ይዘው 100% ለመድፈን በቅተዋል፡፡

ሳዳም 100 ከደፈኑ በኋላ ብዙም አልቆዩም፡፡ በሌላ በኩል የቀድሞው የሰሜን ኮሪያ ታላቁ ባለራዕይ መሪ ኪም ጆንግ ኢል ከልጃቸው ኪም ጆንግ-ኧን በ0.1% በመበለጥ በ2001ዓም 99.9% ያገኙ “ጎበዝ” ነበሩ፡፡

የኩባው ራዑል ካስትሮ በ2000ዓም 99.4% ሲያገኙ የሶሪያው ባሽር አል አሳድ 97.6% ያስቆጠሩ ሌላው “ደፋኝ” ናቸው፡፡ የቱርክሜኒስታኑ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በ1984 እንዲሁም የቼችኒያው የተባበሩት ሩሲያ ፓርቲ በ2003ዓም 99.5% ያስቆጠሩ ሌሎቹ “ጎበዞች” ናቸው፡፡ በ1996ዓም በጆርጂያ ሚኻኤል ሳካሽቪሊ ሌላው 96% ያገኙ ታታሪ “ተመራጭ” ናቸው፡፡

በአምባገነን አገዛዞች ውስጥ የሚደረግ ምርጫ አንድ ተወዳዳሪ ራሱን በማቅረብ የሚወዳደር ከመሆኑ ባሻገር መራጮች የሚሰጣቸው ምርጫ አምባገነኑን መምረጥ ወይም ስቃይና መከራ መቀበል ነው፡፡ አንዳንዶቹ አምባገነኖች “ፉክክር” ተደርጎ ነበር ለማስባል “ታማኝ ተፎካካሪዎችን” ራሳቸው እንደሚፈጥሩና “ምርጫው ፍትሃዊ፣ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሁም የምርጫ መስፈርቶችን ያሟላ” እንዲመስል እንደሚያደርጉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በግላስጎው ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንቲስት የሆኑት ቶማስ ሉንድበርግ ሲናገሩ “ከሁለት ሦስተኛ በላይ ድምጽ አግኝቶ በማንኛውም ምርጫ የሚያል (ፓርቲ) ሲኖር ጥርጣሬ ሊያስነሳ ይገባል” ብለዋል፡፡ ምክንያቱን ሲጠቅሱም በፍትሃዊና ሰላማዊ ምርጫ ይህ ዓይነቱ ውጤት ያልተለመደ ስለሆነ ነው ይላሉ፡፡ የተበታተኑ (ኅብረት ያልፈጠሩ) የተቀናቃኝ ፓርቲዎች በሚኖሩበት ምርጫ የሚገኘው ውጤት 60-80% ሊያልፍ አይችልም ይላሉ፡፡

አምባገነናዊ ሥርዓቶች የሚጋልቡት ባቡር የታሰበበት መድረሻ እንደሚደርስ አምባገነኖቹ እርግጠኞች ናቸው፡፡ ባቡሩ የሚያውቀው ጣቢያ መኖሩን ብቻ ነው፡፡ አልፎ ስለመጣው ሃዲድና መሰል ጉዳዮች የሚያውቀው አንዳች ነገር የለም፡፡ መድረሻ ጣቢያ እንዳለው ያውቃል፤ አሁን ካለበት ጣቢያ እስከመድረሻው ጣቢያዎች እንዳሉ ያውቃል፡፡ የመጨረሻ ጣቢያ ስለመድረሱ ግን ምንም በእርግጠኝነት የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ ሃዲዱ እየሰራ ይሁን፣ ያደርሰው ይሆን፣ መንገድ ላይ አደጋ ይኑር፣ … ምንም እርግጠኛ ሆኖ የሚያውቀው ነገር የለም፡፡

“ስለ ክብር አልባ ታላቅነት፣ ጥበብ አልባ ሃብት፣ ሕግ አልባ ኃይልና ሥልጣን ታሪክ ምን ይላል? መልሱ በባቢሎን፣ በሜዶንና ፋርስ፣ በግሪክ እንዲሁም በሮም ታላላቅ ግዛተ አጼዎች መገርሰስ በተደጋጋሚ ተነግሯል፡፡ እነዚህ አራት ተከታታይ ዓለምን የገዙ ኃያላን ነበሩ፡፡ አሁን በምን ሁኔታና የት ይሆን ያሉት?” ኦርሰን ኤፍ ዊትኒይ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule