• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

100% ደፋኝ “ጎበዞች”

June 21, 2015 08:01 pm by Editor Leave a Comment

በ1994ዓም የኢራቁ ፕሬዚዳንት ሳዳም ሁሴን “በምርጫ” 100% ደፍነው ነበር፡፡ ያለፈው ዓመት ደግሞ የሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ-ኧን ያለአንዳች ተቀናቃኝ ባደረጉት “ከፍተኛ ትንቅንቅ” በነበረበት የምርጫ ውድድር ብቻቸውን ተወዳድረው በመጨረሻው ላይ ትንፋሻቸውን ይዘው 100% ለመድፈን በቅተዋል፡፡

ሳዳም 100 ከደፈኑ በኋላ ብዙም አልቆዩም፡፡ በሌላ በኩል የቀድሞው የሰሜን ኮሪያ ታላቁ ባለራዕይ መሪ ኪም ጆንግ ኢል ከልጃቸው ኪም ጆንግ-ኧን በ0.1% በመበለጥ በ2001ዓም 99.9% ያገኙ “ጎበዝ” ነበሩ፡፡

የኩባው ራዑል ካስትሮ በ2000ዓም 99.4% ሲያገኙ የሶሪያው ባሽር አል አሳድ 97.6% ያስቆጠሩ ሌላው “ደፋኝ” ናቸው፡፡ የቱርክሜኒስታኑ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በ1984 እንዲሁም የቼችኒያው የተባበሩት ሩሲያ ፓርቲ በ2003ዓም 99.5% ያስቆጠሩ ሌሎቹ “ጎበዞች” ናቸው፡፡ በ1996ዓም በጆርጂያ ሚኻኤል ሳካሽቪሊ ሌላው 96% ያገኙ ታታሪ “ተመራጭ” ናቸው፡፡

በአምባገነን አገዛዞች ውስጥ የሚደረግ ምርጫ አንድ ተወዳዳሪ ራሱን በማቅረብ የሚወዳደር ከመሆኑ ባሻገር መራጮች የሚሰጣቸው ምርጫ አምባገነኑን መምረጥ ወይም ስቃይና መከራ መቀበል ነው፡፡ አንዳንዶቹ አምባገነኖች “ፉክክር” ተደርጎ ነበር ለማስባል “ታማኝ ተፎካካሪዎችን” ራሳቸው እንደሚፈጥሩና “ምርጫው ፍትሃዊ፣ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሁም የምርጫ መስፈርቶችን ያሟላ” እንዲመስል እንደሚያደርጉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በግላስጎው ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንቲስት የሆኑት ቶማስ ሉንድበርግ ሲናገሩ “ከሁለት ሦስተኛ በላይ ድምጽ አግኝቶ በማንኛውም ምርጫ የሚያል (ፓርቲ) ሲኖር ጥርጣሬ ሊያስነሳ ይገባል” ብለዋል፡፡ ምክንያቱን ሲጠቅሱም በፍትሃዊና ሰላማዊ ምርጫ ይህ ዓይነቱ ውጤት ያልተለመደ ስለሆነ ነው ይላሉ፡፡ የተበታተኑ (ኅብረት ያልፈጠሩ) የተቀናቃኝ ፓርቲዎች በሚኖሩበት ምርጫ የሚገኘው ውጤት 60-80% ሊያልፍ አይችልም ይላሉ፡፡

አምባገነናዊ ሥርዓቶች የሚጋልቡት ባቡር የታሰበበት መድረሻ እንደሚደርስ አምባገነኖቹ እርግጠኞች ናቸው፡፡ ባቡሩ የሚያውቀው ጣቢያ መኖሩን ብቻ ነው፡፡ አልፎ ስለመጣው ሃዲድና መሰል ጉዳዮች የሚያውቀው አንዳች ነገር የለም፡፡ መድረሻ ጣቢያ እንዳለው ያውቃል፤ አሁን ካለበት ጣቢያ እስከመድረሻው ጣቢያዎች እንዳሉ ያውቃል፡፡ የመጨረሻ ጣቢያ ስለመድረሱ ግን ምንም በእርግጠኝነት የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ ሃዲዱ እየሰራ ይሁን፣ ያደርሰው ይሆን፣ መንገድ ላይ አደጋ ይኑር፣ … ምንም እርግጠኛ ሆኖ የሚያውቀው ነገር የለም፡፡

“ስለ ክብር አልባ ታላቅነት፣ ጥበብ አልባ ሃብት፣ ሕግ አልባ ኃይልና ሥልጣን ታሪክ ምን ይላል? መልሱ በባቢሎን፣ በሜዶንና ፋርስ፣ በግሪክ እንዲሁም በሮም ታላላቅ ግዛተ አጼዎች መገርሰስ በተደጋጋሚ ተነግሯል፡፡ እነዚህ አራት ተከታታይ ዓለምን የገዙ ኃያላን ነበሩ፡፡ አሁን በምን ሁኔታና የት ይሆን ያሉት?” ኦርሰን ኤፍ ዊትኒይ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule