
ምሁርን መተቸት ይቻላል? ይቻላል እንደምትሉ በማመን መቀጠሌ ነው። አዎ ደሞም የሚቻል ይመስለኛል። በኛ ሀገር ነውር ሆኖ የሚያስቀጣው መንግስትን መተቸት እንጂ በሌላው ማንኛውም ሰው ሃሳብ ላይ ሃሳብ ቢሰጡ ክፋት የለውም። እርግጥ ከፖለቲካ ውጭም ቢሆን መተቻቸት የለመድነው ባህል ስላልሆነ ሲተች የሚወድ ብዙ ሰው የለም። ለነገሩማ የብልሹ ፖለቲካ ባህላችን ምንጭ ይኼው አሳዛኝ ማህበራዊ አስተሳሰባችን አይደል? ብቻ ፕሮፌሰር በክርክር የሚያምኑ በሳል ምሁር እንደሆኑ ስለማምን ያለስጋት በሃሳባቸው ላይ ሃሳብ ልሰነዝር ደፈርኩ።
ፕሮፌሰር፥ወልቃይት የማነው? የማይረባ ጥያቄ፥ በሚል ርእስ በብሎጋቸው ያወጡትን በጎልጉል ድረገፅ ላይ ካነበብኩ በኋላ የሚደገፍም የሚነቀፍም ነጥብ አገኘሁበት። በአንድ በኩል ጥያቄው በዘር ሳይሆን ባገር መነፅር ሊታይ ይገባል። ወልቃይት የትግራይም ያማራም ሳይሆን የኢትዮጵያ ነው ማለት በተለይ የጎሰኝነትን መርዘኛ ፖለቲካ ለምንፀየፍ ሰዎች ምቾት ይሰጣል። ምናልባትም ለ25 አመታት ከዘረኝነት ሸሽቶ ግን ደግሞ የዘረኝነት ጦስ ሰለባ በመሆን ፍዳውን ሲቆጥር የኖረውን ያማራ ህዝብ በቁጭትና በንዴት ዘረኞች ባዘጋጁለት የዘረኝነት ወጥመድ እንዳይገባ ለመከላከል ይጠቅም ይሆናል። እኔም ብሆን ወልቃይትን ሱዳኖች ወሰዱት እስካላሉኝ ድረስ አማራ ሰፈረበትም ትግሬ, ዖሮሞ ያዘውም ጉራጌ አያሳስበኝም።
ወልቃይት በትግራይ አስተዳደር ስር እንዲሆን የተፈለገበት ምክንያት አስተዳደራዊ ሳይሆን ጎሰኝነት መሆኑ ሲታሰብ ግን ወልቃይት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ያማራም ነው ለማለት ያስገድዳል። ዘረኛው መንግስት ወልቃይት ወደትግራይ ቢጠቃለል ላስተዳደር ያመቻል ቢለን ይገባን ነበር። ወልቃይቶች ትግርዎች ናቸው፦ ስለዚህ ወልቃይት የትግራይ ነው ሲል ግን ራሱ በቆረጠው ዱላ ከመከላከል ሌላ አማራጭ የሚኖር አይመስለኝም። ከዚህም ሌላ ክርክሩ ወልቃይት የትግራይ ነው ወይስ የኢትዮጵያ የሚል አይደለም። በተግባር የቀረበው ጥያቄ አካባቢው ያማራ ክልል ነው ወይስ የትግራይ የሚል ነው። ወልቃይት ያማራም የትግሬም ሳይሆን የኢትዮጵያ ነው የሚል ክርክር ማቅረብ ምርጫ ውስጥ የሌለ መልስ ነው። ምርጫው ውስጥ የሌለ መልስ መስጠት ደግሞ ነጥብ ስለማያሰጥ በዚህ ክርክር ላይ ለፕሮፌሰር ነጥብ አልሰጠኋቸውም። እርሳቸውም ቢሆኑ በመምህርነት ዘመናቸው ምርጫው ውስጥ የሌለ መልስ ለሰጠ ተማሪ ነጥብ የሰጡ አይመስለኝምና በዳኝነቴ አይቀየሙም።
በመጨረሻም በወቅቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያለሁ ከአቶ መለስ ጋር ያደረጋችሁትን ያማራ አለ የለም ክርክር ሰምቼ በሃሳብቆ ተስማምቼ ነበር። ምክንያቱም በኔም የትውልድ አካባቢ ?አማራ? የሚለው ቃል የሃይማኖት እንጂ የዘር ወይም የጎሳ መጠሪያ ስላልነበረ ነው። ከ25 አመታት በኋላ ግን ሃሳብዎን ያለመለወጥዎን ስረዳ አቶ መለስን አመሰገንሁት። ምክንያቱም እሱ አማራን በፈጠረበት ዘመን አማራ እንደአማራ ያልነበረ ቢሆንም ከ25 አመታት የግፍና ጭፍጨፋ ዘመን በኋላ ግን አማራ ሳይወድ በግዱ የራሱን ማንነት ፈጥሯል። ኢትዮጵያዊነት ብቻውን ከሞት እንዳላዳነው ሲረዳ ለራሱ ተጨማሪ ስም ለማውጣት ተገዷል። እናም ዛሬ አማራ አለ። አማራ ባይኖር ኖሮ አማራ አይሞትም ነበር። በገዢው መንግስት ፊታውራሪነት በየክልሉ ያለቀው ኢትዮጵያዊ ብቻ ሳይሆን አማራም ነበር። እናም አማራ ዛሬ ሲጠሩት ወይ ለማለት ተገዷል። ሌሎች በስሙ እየጠሩ አለህ ሲሉት ለኢትዮጵያ ሲል ብቻ የለሁም ቢል አንድ እግሩን ጅብ እየበላው አጠገቡ የተኛውን ጓደኛውን፥ እባክህ አትንቀሳቀስ፤ ጅብ ታስበላኛለህ፥ ያለውን ፈሪ ያስመስላል። እና ፕሮፌሰር ይቅርታ ያድርጉልኝ እንጂ በጠንካራ ያንድነት ስሜትዎ ባደንቀዎትም በዚህ ክርክር ላይ ግን አላሳመኑኝም። ረጅም እድሜ እመኛለሁ።
ህሩይ ደምሴ
zobar2006@gmail.com
“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡
Politely expressed critiques. I like that. This is a good material to teach people how critiques should be forwarded. Critiques should be directed to the idea not the person.
Heruy, my complements for your careful yet accurate arguments. I believe prof. won’t refuse your point of view. It is not only due to the enforcement of accepting the identity but because TPLF’s sustained goal is to weaken or if possible wipe it out massacre take over its land area and establish a new country, greater Tigray. In that case Wolkait, etc will not be part of Ethiopia.
Thus, we need to accept the identify at least for 2 strategic overlapping reasons:
– to hold on our (Ethiopian) resources
– and to eradicate TPLF.
Bravoo! I missed such critiques pro. Hope pro. will give you nice replay. In the near we should involved.
God bless Ethiopia and it’s people.
Benyam/TX
I think prof mesfin says the quation itself is wrong , we better think about our country border line not intetnal boundaries unforunatly this government did big mistake , thinking ethinically is not big problem for the last century pepoles are moving and mixing themaelves , what is our future pepoles dont have ethink or biher mix of oromo amhara tigray somale and others