• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወልቃይትን በኢትዮጵያዊነት መነፅር

August 19, 2016 12:14 am by Editor 4 Comments

ምሁርን መተቸት ይቻላል? ይቻላል እንደምትሉ በማመን መቀጠሌ ነው። አዎ ደሞም የሚቻል ይመስለኛል። በኛ ሀገር ነውር ሆኖ የሚያስቀጣው መንግስትን መተቸት እንጂ በሌላው ማንኛውም ሰው ሃሳብ ላይ ሃሳብ ቢሰጡ ክፋት የለውም። እርግጥ ከፖለቲካ ውጭም ቢሆን መተቻቸት የለመድነው ባህል ስላልሆነ ሲተች የሚወድ ብዙ ሰው የለም። ለነገሩማ የብልሹ ፖለቲካ ባህላችን ምንጭ ይኼው አሳዛኝ ማህበራዊ አስተሳሰባችን አይደል? ብቻ ፕሮፌሰር በክርክር የሚያምኑ በሳል ምሁር እንደሆኑ ስለማምን ያለስጋት በሃሳባቸው ላይ ሃሳብ ልሰነዝር ደፈርኩ።

ፕሮፌሰር፥ወልቃይት የማነው? የማይረባ ጥያቄ፥ በሚል ርእስ በብሎጋቸው ያወጡትን በጎልጉል ድረገፅ ላይ ካነበብኩ በኋላ የሚደገፍም የሚነቀፍም ነጥብ አገኘሁበት። በአንድ በኩል ጥያቄው በዘር ሳይሆን ባገር መነፅር ሊታይ ይገባል። ወልቃይት የትግራይም ያማራም ሳይሆን የኢትዮጵያ ነው ማለት በተለይ የጎሰኝነትን መርዘኛ ፖለቲካ ለምንፀየፍ ሰዎች ምቾት ይሰጣል። ምናልባትም ለ25 አመታት ከዘረኝነት ሸሽቶ ግን ደግሞ የዘረኝነት ጦስ ሰለባ በመሆን ፍዳውን ሲቆጥር የኖረውን ያማራ ህዝብ በቁጭትና በንዴት ዘረኞች ባዘጋጁለት የዘረኝነት ወጥመድ እንዳይገባ ለመከላከል ይጠቅም ይሆናል። እኔም ብሆን ወልቃይትን ሱዳኖች ወሰዱት እስካላሉኝ ድረስ አማራ ሰፈረበትም ትግሬ, ዖሮሞ ያዘውም ጉራጌ አያሳስበኝም።

ወልቃይት በትግራይ አስተዳደር ስር እንዲሆን የተፈለገበት ምክንያት አስተዳደራዊ ሳይሆን ጎሰኝነት መሆኑ ሲታሰብ ግን ወልቃይት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ያማራም ነው ለማለት ያስገድዳል። ዘረኛው መንግስት ወልቃይት ወደትግራይ ቢጠቃለል ላስተዳደር ያመቻል ቢለን ይገባን ነበር። ወልቃይቶች ትግርዎች ናቸው፦ ስለዚህ ወልቃይት የትግራይ ነው ሲል ግን ራሱ በቆረጠው ዱላ ከመከላከል ሌላ አማራጭ የሚኖር አይመስለኝም። ከዚህም ሌላ ክርክሩ ወልቃይት የትግራይ ነው ወይስ የኢትዮጵያ የሚል አይደለም። በተግባር የቀረበው ጥያቄ አካባቢው ያማራ ክልል ነው ወይስ የትግራይ የሚል ነው። ወልቃይት ያማራም የትግሬም ሳይሆን የኢትዮጵያ ነው የሚል ክርክር ማቅረብ ምርጫ ውስጥ የሌለ መልስ ነው። ምርጫው ውስጥ የሌለ መልስ መስጠት ደግሞ ነጥብ ስለማያሰጥ በዚህ ክርክር ላይ ለፕሮፌሰር ነጥብ አልሰጠኋቸውም። እርሳቸውም ቢሆኑ በመምህርነት ዘመናቸው ምርጫው ውስጥ የሌለ መልስ ለሰጠ ተማሪ ነጥብ የሰጡ አይመስለኝምና በዳኝነቴ አይቀየሙም።

በመጨረሻም በወቅቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያለሁ ከአቶ መለስ ጋር ያደረጋችሁትን ያማራ አለ የለም ክርክር ሰምቼ በሃሳብቆ ተስማምቼ ነበር። ምክንያቱም በኔም የትውልድ አካባቢ ?አማራ? የሚለው ቃል የሃይማኖት እንጂ የዘር ወይም የጎሳ መጠሪያ ስላልነበረ ነው። ከ25 አመታት በኋላ ግን ሃሳብዎን ያለመለወጥዎን ስረዳ አቶ መለስን አመሰገንሁት። ምክንያቱም እሱ አማራን በፈጠረበት ዘመን አማራ እንደአማራ ያልነበረ ቢሆንም ከ25 አመታት የግፍና ጭፍጨፋ ዘመን በኋላ ግን አማራ ሳይወድ በግዱ የራሱን ማንነት ፈጥሯል። ኢትዮጵያዊነት ብቻውን ከሞት እንዳላዳነው ሲረዳ ለራሱ ተጨማሪ ስም ለማውጣት ተገዷል። እናም ዛሬ አማራ አለ። አማራ ባይኖር ኖሮ አማራ አይሞትም ነበር። በገዢው መንግስት ፊታውራሪነት በየክልሉ ያለቀው ኢትዮጵያዊ ብቻ ሳይሆን አማራም ነበር። እናም አማራ ዛሬ ሲጠሩት ወይ ለማለት ተገዷል። ሌሎች በስሙ እየጠሩ አለህ ሲሉት ለኢትዮጵያ ሲል ብቻ የለሁም ቢል አንድ እግሩን ጅብ እየበላው አጠገቡ የተኛውን ጓደኛውን፥ እባክህ አትንቀሳቀስ፤ ጅብ ታስበላኛለህ፥ ያለውን ፈሪ ያስመስላል። እና ፕሮፌሰር ይቅርታ ያድርጉልኝ እንጂ በጠንካራ ያንድነት ስሜትዎ ባደንቀዎትም በዚህ ክርክር ላይ ግን አላሳመኑኝም። ረጅም እድሜ እመኛለሁ።

ህሩይ ደምሴ

zobar2006@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Endale KETEFO says

    August 20, 2016 01:46 pm at 1:46 pm

    Politely expressed critiques. I like that. This is a good material to teach people how critiques should be forwarded. Critiques should be directed to the idea not the person.

    Reply
  2. rasdejen says

    August 24, 2016 05:33 pm at 5:33 pm

    Heruy, my complements for your careful yet accurate arguments. I believe prof. won’t refuse your point of view. It is not only due to the enforcement of accepting the identity but because TPLF’s sustained goal is to weaken or if possible wipe it out massacre take over its land area and establish a new country, greater Tigray. In that case Wolkait, etc will not be part of Ethiopia.

    Thus, we need to accept the identify at least for 2 strategic overlapping reasons:
    – to hold on our (Ethiopian) resources
    – and to eradicate TPLF.

    Reply
  3. Benyam says

    August 26, 2016 04:48 am at 4:48 am

    Bravoo! I missed such critiques pro. Hope pro. will give you nice replay. In the near we should involved.
    God bless Ethiopia and it’s people.

    Benyam/TX

    Reply
  4. Bereket Tolosa says

    August 28, 2016 10:42 am at 10:42 am

    I think prof mesfin says the quation itself is wrong , we better think about our country border line not intetnal boundaries unforunatly this government did big mistake , thinking ethinically is not big problem for the last century pepoles are moving and mixing themaelves , what is our future pepoles dont have ethink or biher mix of oromo amhara tigray somale and others

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule