• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወልቃይትን በኢትዮጵያዊነት መነፅር

August 19, 2016 12:14 am by Editor 4 Comments

ምሁርን መተቸት ይቻላል? ይቻላል እንደምትሉ በማመን መቀጠሌ ነው። አዎ ደሞም የሚቻል ይመስለኛል። በኛ ሀገር ነውር ሆኖ የሚያስቀጣው መንግስትን መተቸት እንጂ በሌላው ማንኛውም ሰው ሃሳብ ላይ ሃሳብ ቢሰጡ ክፋት የለውም። እርግጥ ከፖለቲካ ውጭም ቢሆን መተቻቸት የለመድነው ባህል ስላልሆነ ሲተች የሚወድ ብዙ ሰው የለም። ለነገሩማ የብልሹ ፖለቲካ ባህላችን ምንጭ ይኼው አሳዛኝ ማህበራዊ አስተሳሰባችን አይደል? ብቻ ፕሮፌሰር በክርክር የሚያምኑ በሳል ምሁር እንደሆኑ ስለማምን ያለስጋት በሃሳባቸው ላይ ሃሳብ ልሰነዝር ደፈርኩ።

ፕሮፌሰር፥ወልቃይት የማነው? የማይረባ ጥያቄ፥ በሚል ርእስ በብሎጋቸው ያወጡትን በጎልጉል ድረገፅ ላይ ካነበብኩ በኋላ የሚደገፍም የሚነቀፍም ነጥብ አገኘሁበት። በአንድ በኩል ጥያቄው በዘር ሳይሆን ባገር መነፅር ሊታይ ይገባል። ወልቃይት የትግራይም ያማራም ሳይሆን የኢትዮጵያ ነው ማለት በተለይ የጎሰኝነትን መርዘኛ ፖለቲካ ለምንፀየፍ ሰዎች ምቾት ይሰጣል። ምናልባትም ለ25 አመታት ከዘረኝነት ሸሽቶ ግን ደግሞ የዘረኝነት ጦስ ሰለባ በመሆን ፍዳውን ሲቆጥር የኖረውን ያማራ ህዝብ በቁጭትና በንዴት ዘረኞች ባዘጋጁለት የዘረኝነት ወጥመድ እንዳይገባ ለመከላከል ይጠቅም ይሆናል። እኔም ብሆን ወልቃይትን ሱዳኖች ወሰዱት እስካላሉኝ ድረስ አማራ ሰፈረበትም ትግሬ, ዖሮሞ ያዘውም ጉራጌ አያሳስበኝም።

ወልቃይት በትግራይ አስተዳደር ስር እንዲሆን የተፈለገበት ምክንያት አስተዳደራዊ ሳይሆን ጎሰኝነት መሆኑ ሲታሰብ ግን ወልቃይት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ያማራም ነው ለማለት ያስገድዳል። ዘረኛው መንግስት ወልቃይት ወደትግራይ ቢጠቃለል ላስተዳደር ያመቻል ቢለን ይገባን ነበር። ወልቃይቶች ትግርዎች ናቸው፦ ስለዚህ ወልቃይት የትግራይ ነው ሲል ግን ራሱ በቆረጠው ዱላ ከመከላከል ሌላ አማራጭ የሚኖር አይመስለኝም። ከዚህም ሌላ ክርክሩ ወልቃይት የትግራይ ነው ወይስ የኢትዮጵያ የሚል አይደለም። በተግባር የቀረበው ጥያቄ አካባቢው ያማራ ክልል ነው ወይስ የትግራይ የሚል ነው። ወልቃይት ያማራም የትግሬም ሳይሆን የኢትዮጵያ ነው የሚል ክርክር ማቅረብ ምርጫ ውስጥ የሌለ መልስ ነው። ምርጫው ውስጥ የሌለ መልስ መስጠት ደግሞ ነጥብ ስለማያሰጥ በዚህ ክርክር ላይ ለፕሮፌሰር ነጥብ አልሰጠኋቸውም። እርሳቸውም ቢሆኑ በመምህርነት ዘመናቸው ምርጫው ውስጥ የሌለ መልስ ለሰጠ ተማሪ ነጥብ የሰጡ አይመስለኝምና በዳኝነቴ አይቀየሙም።

በመጨረሻም በወቅቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያለሁ ከአቶ መለስ ጋር ያደረጋችሁትን ያማራ አለ የለም ክርክር ሰምቼ በሃሳብቆ ተስማምቼ ነበር። ምክንያቱም በኔም የትውልድ አካባቢ ?አማራ? የሚለው ቃል የሃይማኖት እንጂ የዘር ወይም የጎሳ መጠሪያ ስላልነበረ ነው። ከ25 አመታት በኋላ ግን ሃሳብዎን ያለመለወጥዎን ስረዳ አቶ መለስን አመሰገንሁት። ምክንያቱም እሱ አማራን በፈጠረበት ዘመን አማራ እንደአማራ ያልነበረ ቢሆንም ከ25 አመታት የግፍና ጭፍጨፋ ዘመን በኋላ ግን አማራ ሳይወድ በግዱ የራሱን ማንነት ፈጥሯል። ኢትዮጵያዊነት ብቻውን ከሞት እንዳላዳነው ሲረዳ ለራሱ ተጨማሪ ስም ለማውጣት ተገዷል። እናም ዛሬ አማራ አለ። አማራ ባይኖር ኖሮ አማራ አይሞትም ነበር። በገዢው መንግስት ፊታውራሪነት በየክልሉ ያለቀው ኢትዮጵያዊ ብቻ ሳይሆን አማራም ነበር። እናም አማራ ዛሬ ሲጠሩት ወይ ለማለት ተገዷል። ሌሎች በስሙ እየጠሩ አለህ ሲሉት ለኢትዮጵያ ሲል ብቻ የለሁም ቢል አንድ እግሩን ጅብ እየበላው አጠገቡ የተኛውን ጓደኛውን፥ እባክህ አትንቀሳቀስ፤ ጅብ ታስበላኛለህ፥ ያለውን ፈሪ ያስመስላል። እና ፕሮፌሰር ይቅርታ ያድርጉልኝ እንጂ በጠንካራ ያንድነት ስሜትዎ ባደንቀዎትም በዚህ ክርክር ላይ ግን አላሳመኑኝም። ረጅም እድሜ እመኛለሁ።

ህሩይ ደምሴ

zobar2006@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Endale KETEFO says

    August 20, 2016 01:46 pm at 1:46 pm

    Politely expressed critiques. I like that. This is a good material to teach people how critiques should be forwarded. Critiques should be directed to the idea not the person.

    Reply
  2. rasdejen says

    August 24, 2016 05:33 pm at 5:33 pm

    Heruy, my complements for your careful yet accurate arguments. I believe prof. won’t refuse your point of view. It is not only due to the enforcement of accepting the identity but because TPLF’s sustained goal is to weaken or if possible wipe it out massacre take over its land area and establish a new country, greater Tigray. In that case Wolkait, etc will not be part of Ethiopia.

    Thus, we need to accept the identify at least for 2 strategic overlapping reasons:
    – to hold on our (Ethiopian) resources
    – and to eradicate TPLF.

    Reply
  3. Benyam says

    August 26, 2016 04:48 am at 4:48 am

    Bravoo! I missed such critiques pro. Hope pro. will give you nice replay. In the near we should involved.
    God bless Ethiopia and it’s people.

    Benyam/TX

    Reply
  4. Bereket Tolosa says

    August 28, 2016 10:42 am at 10:42 am

    I think prof mesfin says the quation itself is wrong , we better think about our country border line not intetnal boundaries unforunatly this government did big mistake , thinking ethinically is not big problem for the last century pepoles are moving and mixing themaelves , what is our future pepoles dont have ethink or biher mix of oromo amhara tigray somale and others

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule