• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጎንደር የተነሳው አመጽ እየሰፋ ነው!

July 13, 2016 10:10 am by Editor 2 Comments

በጎንደር የሰዎች ህይወት ከማለፉ በተጨማሪ ሕዝብ የማያምንባቸውንና ከትግራይ ተገንጣይ ቡድን ጋር ግንኙነት አላቸው ባላቸው ንብረቶች ላይ ርምጃ መውሰዱ ታውቁዋል። ማክሰኞ ሊነጋጋ አካባቢ ተነሳ የተባለውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለመቀላቀል ወደ ጎንደር ያመሩ ወገኖችም መበራከታቸው እየተሰማ ነው። ለዓመጹ ውጤታማነት የዘር ትግል ሳይሆን ኅብረብሔራዊ እንቅስቃሴ እንደሚበጅ ተገለጸ።

አመጹ የተቀሰቀሰው የማንነት ጥያቄ ባነሱና “እኛ አማራ እንጂ ትግሬ አይደለንም” በሚል የተነሳውን ጥያቄ ከውጤት ለማድረስ ከተመረጡት የኮሚቴ አባላት መካከል አራት የሚሆኑትን ከትግራይ የመጡ ነፍጥ አንጋቾች ከያዟቸው በኋላ እንደሆነ ለኢሳት በድምጽ ማብራሪያ የሰጡ አረጋገጠዋል። ከዚያም ኮሎኔል ዘውዱ ደመቀን ለመያዝ ሙከራ ተደረገ። ይህን ጊዜ ኮሎኔሉ “በሬን አልከፍትም ጥዬ እወድቃለሁ” በማለት ሊያስሯቸው ከመጡት ሃይሎች መካከል ሁለቱን” ጣሉ። ይህንን የሰሙ የወልቃይት ሚሊሻዎች በስድስት አውቶቡስ ጎንደር ደረሱ። ቀደም ሲል ህዝብ የኮሎኔሉን ቤት ከቦ አላስነካም ብሎ ቆየቶ ነበርና በመደጋገፍ ኮሎኔል ዘውዴ ጥቃት ሳይደርስባቸው ከቤታቸው ማስወጣት እንደተቻለ ለኢሳት ማብራሪያ ከሰጡት ለማወቅ ተችሏል። tmp_29027-image-0-02-01-69d0f7f2ea563ae5a74916cea250d7fd0bc0411a96d357cca5c257fb60b23503-V-1175058064

አክለውም የዞኑ አስተዳደርና የክልሉ ሃላፊዎች እየሆነ ስላለው ሲነገራቸው ያለማቅማማት “የምናውቀው ነገር የለም። የምትችሉትን ርምጃ ውሰዱ። ነገር ግን መሳሪያ አንሰጣችሁም” የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው ስም ጠቅሰው ተናግረዋል።

ከትግራይ መጡ የተባሉትና የክልሉንም ሆነ የዞኑን ፈቃድ ካላገኙት ታጣቂዎች መካከል 6 የሚሆኑት የተገደሉ ሲሆን ከህዝብ ወገን ቁጥሩ በትክክል ያልተገለጸ ህይወት ማለፉን የማህበራዊ ገጾች እየዘገቡ ነው። የህወሃት ሚዲያም 4 የፖሊስ አባላት መገደላቸውን ይፋ አድርጓል። ጉዳዩንም ከዘረፋና ከሽብር ጋር አያይዞታል።

ኢሳት በተከታታይ ያነጋገራቸው ሰው እንዳሉት የወረቀት ጥያቄ ላቀረቡ የህብረተሰብ ክፍሎች ምን በደል ሰርተው ይህ ሁሉ ስቃይ እንደሚደርስባቸው ግልጽ አይደለም። በዚሁ መነሻ በህወሃት የበረሃ ትግል ወቅት ምግብ፣ መሬት፣ ከለላ በመስጠት፣ ደግሶና አካፍሎ ሲያበላ የነበረ የወልቃይት ህዝብ ውለታው ይህ መሆኑን በማስታውስ “የትግራይን ህዝብ ከወንድሙ የአማራ ህዝብ ጋር የህወሃት ባለስልጣናት ደም እያቃቡት ነው። የትግራይ ህዝብ ይህን ጉዳይ እንዴት ያየዋል?” ሲሉ ጠየቀዋል። አያይዘውም “ለወደፊትስ አስቸጋሪ አይሆንም? አማራ ምን አደረገ?” ሲሉ መልዕት አስተላልፈዋል።

ሕዝባዊ ቁጣው መጠኑን እየጨመረ ሲሆን በዳባት ተመሳሳይ ተቃውሞ መጀመሩም ተጠቁሟል። እንደ ማብራሪያ ሰጪዎቹ ከሆነ አሁን የተነሳው ህዝባዊ አመጽ “አማራውን ሊያጠፉት ነው ሳትጠፋ የቻልከውን አጥፋ” ወደሚል ምሬትና አልሞት ባይ ተጋዳይነት ተሸጋግሯል።

አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች “አማራውን ገፍተው ገፍተው እዚህ አደረሱት” ሲሉ አሁንም ህወሃት ጥንቃቄ ሊወስድ እንደሚገባው፣ በሃይል እገፋበታለሁ ካለ ነገሮች መስመራቸውን ሊስቱ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ስለሆነም ዓመጹ ውጤታማ እንዲሆን በዘር ወይም በወገን ወይም በብሄር ላይ ያተኮረ ከመሆኑ ይልቅ ሁሉንም ያካተተ ህብረብሄራዊ ሊሆን እንደሚገባ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ወገኖች አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ  በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ በህወሃት ጥቃት ያልደረሰበት፥ ያልተጎዳ፥ ስቃይ ያላየ አለመኖሩ ሁሉንም የጥቃት ሰለባ በአንድነት ሊያስተባብር የሚችል ችግር መኖሩ ግልጽ ነው የሚሉት ወገኖች መፍትሔውንም በጋራ መቀመም ብልሃት የሚጠይቅ ለሁሉም ወገን የሚጠቅም አማራጭ ነው በማለት ተደማጭነት ያላቸው፥ በሁሉም ሰው ዘንድ መሰማት የሚችሉ ግለሰቦች መሪውን መጨበጥ የሚገባቸው ሰዓት አሁን ነው ይላሉ። ከዚህ በታች ያለውን የፎቶ መረጃ ያገኘነው በተለያዩ ግለሰቦች ከተሰራጩ የማህበራዊ ሚዲያዎችና ገጾች መሆኑንን እንገልጻለን።

tmp_15399-13710715_1148946795144607_2017281093280564382_o1685727325

tmp_15399-13707789_1148946778477942_5492643436133731161_n1133332102

tmp_15399-image-0-02-01-a572473c5f641bb9c088bffa0ec9465f701552bd58cb1ab86268e062f5fe18c4-V1971705821

 

tmp_15399-image-0-02-01-192a9dfe6bfff5d1bbd8b8b45b7dee506627e8c650f3c9ac6700b63c3aebd185-V-2001290385

tmp_15399-image-0-02-01-217e92e8d567ef5197bad2cc41ee07318670e2389390764fddc5cb213001bcdc-V-700063890

tmp_15399-image-0-02-01-96ff643f388aedca3a1c22a1890a46afc5212539577470929da8ee23541083d8-V1771574122

tmp_15399-image-0-02-01-e2b4a6beeda20c7bb79e07a810ec11845b76f82d1ce9398e551b9eef24b8f356-V-1123621149

tmp_15399-image-0-02-01-583bd9387c71fef30efd1277e624b14a10b32aa36188424c264b19885e17afba-V-1576589714

tmp_15399-image-0-02-01-faa277e39bd106e02fc549d93327c7ac1d7f8734b33c97ef035a84f15d05131f-V1666556473

tmp_15399-image-0-02-01-e1f0b35e678abf0e5053381d1bf46724ce5787a104e5e2fb23a690072c44c068-V-163156207

tmp_15399-image-0-02-01-7c0f8afa0205c40e7248f09bc94493431a3c9b7adf0613f71b82fe84512d6887-V1152039146

tmp_15399-image-0-02-01-2bf417e10269578b47350508804ee9da8f3a4bf3342fd0c8b561628ed3509250-V1318858571

tmp_15399-image-0-02-01-b751af1f29aabede0f48a26913c0788c7754e1111872b2cbaae01fe1ace66904-V521799796

tmp_15399-image-0-02-01-22f4f68275868ccd7108f6c5307805a6c70944df005ed6bb11da0416dab59196-V1197009622

tmp_15399-image-0-02-01-f6a5c95cac38eabc84d1a160a0ab4f46fa8e5ed63c6c5b98b14a6361690cf075-V-873836785

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    July 16, 2016 07:10 pm at 7:10 pm

    Aye Gura

    Gonder has never truly ruled itself in its history

    Bekafa (Oromo ) ,Michael Shehul (tigrai ) Tewodros ( Wello Oromo ) ruled it for centuries

    Melaku Tefera under Mengistu ( Gimira )order ( Gondere) ruled it for years

    Reply
  2. gud says

    July 16, 2016 07:12 pm at 7:12 pm

    Fukera

    These people r In 18th century . Need proper education .

    Hwala kernet at its best !

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule