• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጎንደር የተነሳው አመጽ እየሰፋ ነው!

July 13, 2016 10:10 am by Editor 2 Comments

በጎንደር የሰዎች ህይወት ከማለፉ በተጨማሪ ሕዝብ የማያምንባቸውንና ከትግራይ ተገንጣይ ቡድን ጋር ግንኙነት አላቸው ባላቸው ንብረቶች ላይ ርምጃ መውሰዱ ታውቁዋል። ማክሰኞ ሊነጋጋ አካባቢ ተነሳ የተባለውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለመቀላቀል ወደ ጎንደር ያመሩ ወገኖችም መበራከታቸው እየተሰማ ነው። ለዓመጹ ውጤታማነት የዘር ትግል ሳይሆን ኅብረብሔራዊ እንቅስቃሴ እንደሚበጅ ተገለጸ።

አመጹ የተቀሰቀሰው የማንነት ጥያቄ ባነሱና “እኛ አማራ እንጂ ትግሬ አይደለንም” በሚል የተነሳውን ጥያቄ ከውጤት ለማድረስ ከተመረጡት የኮሚቴ አባላት መካከል አራት የሚሆኑትን ከትግራይ የመጡ ነፍጥ አንጋቾች ከያዟቸው በኋላ እንደሆነ ለኢሳት በድምጽ ማብራሪያ የሰጡ አረጋገጠዋል። ከዚያም ኮሎኔል ዘውዱ ደመቀን ለመያዝ ሙከራ ተደረገ። ይህን ጊዜ ኮሎኔሉ “በሬን አልከፍትም ጥዬ እወድቃለሁ” በማለት ሊያስሯቸው ከመጡት ሃይሎች መካከል ሁለቱን” ጣሉ። ይህንን የሰሙ የወልቃይት ሚሊሻዎች በስድስት አውቶቡስ ጎንደር ደረሱ። ቀደም ሲል ህዝብ የኮሎኔሉን ቤት ከቦ አላስነካም ብሎ ቆየቶ ነበርና በመደጋገፍ ኮሎኔል ዘውዴ ጥቃት ሳይደርስባቸው ከቤታቸው ማስወጣት እንደተቻለ ለኢሳት ማብራሪያ ከሰጡት ለማወቅ ተችሏል። tmp_29027-image-0-02-01-69d0f7f2ea563ae5a74916cea250d7fd0bc0411a96d357cca5c257fb60b23503-V-1175058064

አክለውም የዞኑ አስተዳደርና የክልሉ ሃላፊዎች እየሆነ ስላለው ሲነገራቸው ያለማቅማማት “የምናውቀው ነገር የለም። የምትችሉትን ርምጃ ውሰዱ። ነገር ግን መሳሪያ አንሰጣችሁም” የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው ስም ጠቅሰው ተናግረዋል።

ከትግራይ መጡ የተባሉትና የክልሉንም ሆነ የዞኑን ፈቃድ ካላገኙት ታጣቂዎች መካከል 6 የሚሆኑት የተገደሉ ሲሆን ከህዝብ ወገን ቁጥሩ በትክክል ያልተገለጸ ህይወት ማለፉን የማህበራዊ ገጾች እየዘገቡ ነው። የህወሃት ሚዲያም 4 የፖሊስ አባላት መገደላቸውን ይፋ አድርጓል። ጉዳዩንም ከዘረፋና ከሽብር ጋር አያይዞታል።

ኢሳት በተከታታይ ያነጋገራቸው ሰው እንዳሉት የወረቀት ጥያቄ ላቀረቡ የህብረተሰብ ክፍሎች ምን በደል ሰርተው ይህ ሁሉ ስቃይ እንደሚደርስባቸው ግልጽ አይደለም። በዚሁ መነሻ በህወሃት የበረሃ ትግል ወቅት ምግብ፣ መሬት፣ ከለላ በመስጠት፣ ደግሶና አካፍሎ ሲያበላ የነበረ የወልቃይት ህዝብ ውለታው ይህ መሆኑን በማስታውስ “የትግራይን ህዝብ ከወንድሙ የአማራ ህዝብ ጋር የህወሃት ባለስልጣናት ደም እያቃቡት ነው። የትግራይ ህዝብ ይህን ጉዳይ እንዴት ያየዋል?” ሲሉ ጠየቀዋል። አያይዘውም “ለወደፊትስ አስቸጋሪ አይሆንም? አማራ ምን አደረገ?” ሲሉ መልዕት አስተላልፈዋል።

ሕዝባዊ ቁጣው መጠኑን እየጨመረ ሲሆን በዳባት ተመሳሳይ ተቃውሞ መጀመሩም ተጠቁሟል። እንደ ማብራሪያ ሰጪዎቹ ከሆነ አሁን የተነሳው ህዝባዊ አመጽ “አማራውን ሊያጠፉት ነው ሳትጠፋ የቻልከውን አጥፋ” ወደሚል ምሬትና አልሞት ባይ ተጋዳይነት ተሸጋግሯል።

አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች “አማራውን ገፍተው ገፍተው እዚህ አደረሱት” ሲሉ አሁንም ህወሃት ጥንቃቄ ሊወስድ እንደሚገባው፣ በሃይል እገፋበታለሁ ካለ ነገሮች መስመራቸውን ሊስቱ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። ስለሆነም ዓመጹ ውጤታማ እንዲሆን በዘር ወይም በወገን ወይም በብሄር ላይ ያተኮረ ከመሆኑ ይልቅ ሁሉንም ያካተተ ህብረብሄራዊ ሊሆን እንደሚገባ ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ወገኖች አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ  በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ በህወሃት ጥቃት ያልደረሰበት፥ ያልተጎዳ፥ ስቃይ ያላየ አለመኖሩ ሁሉንም የጥቃት ሰለባ በአንድነት ሊያስተባብር የሚችል ችግር መኖሩ ግልጽ ነው የሚሉት ወገኖች መፍትሔውንም በጋራ መቀመም ብልሃት የሚጠይቅ ለሁሉም ወገን የሚጠቅም አማራጭ ነው በማለት ተደማጭነት ያላቸው፥ በሁሉም ሰው ዘንድ መሰማት የሚችሉ ግለሰቦች መሪውን መጨበጥ የሚገባቸው ሰዓት አሁን ነው ይላሉ። ከዚህ በታች ያለውን የፎቶ መረጃ ያገኘነው በተለያዩ ግለሰቦች ከተሰራጩ የማህበራዊ ሚዲያዎችና ገጾች መሆኑንን እንገልጻለን።

tmp_15399-13710715_1148946795144607_2017281093280564382_o1685727325

tmp_15399-13707789_1148946778477942_5492643436133731161_n1133332102

tmp_15399-image-0-02-01-a572473c5f641bb9c088bffa0ec9465f701552bd58cb1ab86268e062f5fe18c4-V1971705821

 

tmp_15399-image-0-02-01-192a9dfe6bfff5d1bbd8b8b45b7dee506627e8c650f3c9ac6700b63c3aebd185-V-2001290385

tmp_15399-image-0-02-01-217e92e8d567ef5197bad2cc41ee07318670e2389390764fddc5cb213001bcdc-V-700063890

tmp_15399-image-0-02-01-96ff643f388aedca3a1c22a1890a46afc5212539577470929da8ee23541083d8-V1771574122

tmp_15399-image-0-02-01-e2b4a6beeda20c7bb79e07a810ec11845b76f82d1ce9398e551b9eef24b8f356-V-1123621149

tmp_15399-image-0-02-01-583bd9387c71fef30efd1277e624b14a10b32aa36188424c264b19885e17afba-V-1576589714

tmp_15399-image-0-02-01-faa277e39bd106e02fc549d93327c7ac1d7f8734b33c97ef035a84f15d05131f-V1666556473

tmp_15399-image-0-02-01-e1f0b35e678abf0e5053381d1bf46724ce5787a104e5e2fb23a690072c44c068-V-163156207

tmp_15399-image-0-02-01-7c0f8afa0205c40e7248f09bc94493431a3c9b7adf0613f71b82fe84512d6887-V1152039146

tmp_15399-image-0-02-01-2bf417e10269578b47350508804ee9da8f3a4bf3342fd0c8b561628ed3509250-V1318858571

tmp_15399-image-0-02-01-b751af1f29aabede0f48a26913c0788c7754e1111872b2cbaae01fe1ace66904-V521799796

tmp_15399-image-0-02-01-22f4f68275868ccd7108f6c5307805a6c70944df005ed6bb11da0416dab59196-V1197009622

tmp_15399-image-0-02-01-f6a5c95cac38eabc84d1a160a0ab4f46fa8e5ed63c6c5b98b14a6361690cf075-V-873836785

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    July 16, 2016 07:10 pm at 7:10 pm

    Aye Gura

    Gonder has never truly ruled itself in its history

    Bekafa (Oromo ) ,Michael Shehul (tigrai ) Tewodros ( Wello Oromo ) ruled it for centuries

    Melaku Tefera under Mengistu ( Gimira )order ( Gondere) ruled it for years

    Reply
  2. gud says

    July 16, 2016 07:12 pm at 7:12 pm

    Fukera

    These people r In 18th century . Need proper education .

    Hwala kernet at its best !

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule