• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ክፋት በዛ

November 17, 2015 12:17 am by Editor 1 Comment

ክፉ ቀን ብዙ ክፉ ምግባሮች ይዞ ይመጣል።

በቀይሽብር ወቅ በመቀሌ ከተማ ያጋጠመ አንድ የክፉ ምግባር ምሳሌ ነበር።

ዘስላሰ የተባለ ወጣት በፀረ ደርግነት ተጠርጥሮ የቀይ ሽብር ሰለባ በመሆን በባዛር እየተባለ የሚታወቀውና አሁን በስሙ ዘላሰ የተሰየመው የአፄ ዮሐንስ ቤተ መንግሥት ፊትለፊት የሚገኝ አደባባይ ይረሸናል። ወላጅ እናቱ በደርግ ወታደሮች ተገድደው እልልል እያሉ፣ እያጨበጨቡ ደስታቸው እንዲገልፁ ተደርገዋል።

ያ ቀይ ሽብር ክፉ ቀን የወለደው ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል። አሁንም ይሄ ጥቁር ታሪክ ዳግማዊ ትንሳኤውን አግኝቷል።

የጥቁር ታሪክ ባለቤት የሆነችው የሰሜን ወሎ ዞን፣ ቆቦ ወረዳ 027 ቀበሌ ነዋሪ እናት ወይዘሮ ብርቱኳን ዓሊ ነች። የ5 ዓመት ልጇን በረሃብ አጥታ እያነባች ለቢቢሲ የሰጠችው ቃለ ምልልስ ኢህአዴግን አስቆጥቶ ልክ እንደ የዘስላሰ እናት አስገድደው እንድታስተባብል አድርጓታል።

የአማራ ክልል ጋዜጠኞች ልክ እንደ የደርግ ወታደሮች ሁሉ ወይዘሮ ብርቱኳን የልጇን ሞት ሃዘን እንዳትችል እያዋከቡና እያስፈራሩ እንድታስተባብል አስገደዷት። ይባስ ብሎ የአሜሪካ ድምፅ VOA ጋዜጠኛ ግርማይ ገብሩም የወንጀሉ አካል መሆኑ እጅግ ያሳዝናል።

ግርማይ ገብሩ የህወሓትን ሴራ እያወቀው ልጇ በድንገተኛ ሞት እንዳጣች፣ በሬ፣ ላም፣ እህል ወዘተ እንዳገኘባት መዘገቡ ያስገምተዋል። እዚህ ላይ የአማራ ክልል ጋዜጠኞች ያስተላለፉት በቀጣይ ልጆችዋ በረሃብ እንዳታጣ መስጋትዋ ገልፃለች። ግርማይ ግን ከነሱ ብሶ መዘገቡ ያሳዝናል።

ህወሃት “የትግራይ ገበሬ 100% ሞዴል፣ የአንድ ዓመት ምርት 113 ሚሊዮን ኩንታል አመረተ”፤ ብሎ የሚዋሽ ድርጅት መሆኑ እያወቀና ጋዜጠኞች እንደሚሄዱ አውቀው የጠቀሳቸው ከብቶችና እህል አስቀድመው በቤትዋ ማስቀመጥ እንዴት ያቅታቸዋል ብሎ ያስባል?

ቅለል ያለው … ሆነ እንጂ የቢቢሲ መግለጫዋ ያስኮነነው ህወሃት UN በየቀኑ ሁለት ሰዎች ድርቅ ባስከተለው ረሃብ እየሞቱ እንዳሉ ገልፀዋል።

የቀይ ሽብር ተግባር በድርቅ ሲደገም እጅጉን ያማል። (Amdom Gebreslasie)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    November 18, 2015 11:53 pm at 11:53 pm

    >>>በቅርቡ በተካሄደው የሕወሓት 12ኛ ጉባዔ ላይ በነባሩ መሥራች አቶ ስብሃት ነጋ (አቦይ ስብሃት) ተጠቁመው የድርጅቱ ማዕክላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው የተመረጡት የሕግ መምህሩ አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ ‹‹እኔ የምለው በሙሉ የመንግሥት አቋም ነው፡፡ የተናገርኩት መንግሥት ማለት ስለፈለገው ነው፡፡ አትቆራርጡት፡፡ እንዳለ አስተላልፉት፤››ሲሉ ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋዜጠኛ ነገሩት፡፡

    __ ይህንን እኛም በምርጫው ማግስት’እንደወረደ ከወርቃማ ህዝቦች ሳይበረዝ ሳይከለስና ሳይሸራረፍ ዜና እንደምንሰማ አውቀናል..የመንግስት ኮምንኬየሽንን ቦታ ከድምፅ ማጉሊያ ጋር በመፃ ይዘውት የነበሩት ሁሉ በህወአት ጥላ ሥር ሆነው የግልና ክልላዊ የበታችነት አመለካከታቸውን መቅረፊያ መዝለፊያና የመሳደቢያ መድረክ፣ ያለነጥብ ቃላት ሲደረድሩ (GOOD) ጉድ(ፅቡቅ) ብለናል::‹‹እንግዲህ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አሉ የምትሉዋቸውን ጥያቄዎች ማንሳት ትችላላችሁ፤›› በማለት ነበር ግልፅና ተጠያቂነት ያለው ደፋር፣ብሔራዊ ቡድን የአምስት ዓመት ኮንትራቱን ለመጨረስ ‹‹አሁንም በመጥፎ ሥራው መጠየቅ ያለበት ኃላፊ ካለ ይጠየቅ!፡፡ መሰቀል ያለበትም እሱ ከሆነ የሚገባው ይሰቀል!፡፡ ሥርዓቱን ለማስተካከል ስንንቀሳቀስ ይህንን በማደናቀፍ በግልጽ ሚና ያላቸው ወገኖችና ተቋማትም ካሉ መፍረስ ያለበት ይፍረስ! መመታት ያለበት ይመታ! ›› ሲሉ መንግሥት የተግባር ዕርምጃ ለመውሰድ ቁርጠኛ አቋም መያዙን ተናግረዋል፡፡

    **አሁን በድርቅና በርሃብ መካካል ያለው የርዮተዓለምና የአተረጓጘም ልዩነት በህወአት/ኢህአዴግ ምሁራን፣ በቢቢ ጋዜጠኞች፣ አስለማኝና አበዳሪ ወይም (partners) በእያሉ በሚያቀማጥሏቸው ኪራይ ሰብሳቢ የውጭ ሕዝቦች የርሃብተኛ ቁጥር፣ የዕርዳታው በገፍና በፍጥነት መድረስ ላይ ማን ነው በበለጠና በሰለጠነ መልኩ የዋሸው? የሚለው ፍትጊያው ቀጥሏል።
    “ርሃብተኞችም የእውነት ዝናብ እስኪመጣ የርሃብን ዕንባ ያዘንባሉ!።
    … “ቢቢሲ ስለተከሰተው ድርቅ ቢጽፍ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብን የማንቃት ዓላማ ይኖረዋል ከሚል ፍላጐት እንደነበር ይናገራሉ፡፡ ‹‹የሄዱበት መንገድ ግን ሌላ ነው፡፡ ያቀረቡትም ውሸት ነው፡፡ ዘገባው የተሠራው ከቆቦ ነው የሚሉት፡፡ ልጇ የሞተባት እናት ግን ከመርሳ ናት፤›› በማለት በዘገባው ሐሰተኝነት ‹‹ያልተቀናጀ የሰነፍ ሥራ ነው የሠሩት፣ያሳዝናል፤›› ብለዋል፡፡… አቶ ጌታቸው ረዳ፡፡ ‹‹እስከ ዛሬ በረሃብ ምክንያት ለሞት የተዳረገ ሰው የለም፡፡ በድርቁ ምክንያት ለሕመም የተጋለጠ ሰው ካለ ግን የመዳን ያለመዳን ዕድሉ ከመንግሥት ሳይሆን ከእግዚአብሔር ነው፤›› ብለዋል፡፡
    … መንግሥት በስድስት ቢሊዮን ብር ከውጭ የእህል ግዥ ማከናወኑን የገለጹት አቶ ጌታቸው፣ እስካሁን ፕሮጀክቶችን ለማጠፍ የሚያስችል አደጋ አለመድረሱን አስረድተዋል፡፡‹‹በእርግጥ አንዳንድ ወገኖች ችግሩ በዚሁ ደረጃ ግዙፍ ሆኖ ከመንግሥት ቁጥጥር ውጪ ሆኖ ማየት ይፈልጋሉ፤›› በማለት፣ የአደጋው ደረጃ ግን ግዙፍ ግብረ ኃይል ለመመሥረትም እንዳልደረሰ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ምናልባት ፕሮጀክቶችን በሁለትና በሦስት ወራት ልናዘገይ እንችላለን፤›› በማለት፡፡ ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ ዕርዳታ እየቀረበ ስለመሆኑ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹እንደ ፀበል አንረጭም፡፡ ዜጐችን ከተከሰተው ድርቅ ሕይወታቸውን ለመታደግ በሚያስችል መንገድ ግን እያደረስን ነው፤›› ብለዋል፡፡ አሜሪካ በዚሁ የበጋ ወር ጀምሮ 246ሚሊዮን የምግብና የገንዘብ እርዳታ…በዚህ ሳምንት እንኳን የአሜሪካ መንግስት 97 ሚሊዮን ዶላር፣ የተባበሩት መንግስታት የስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ 17 ሚሊዮን ዶላር፣ ቻይና 8 ሚሊዮን ዶላር ፣ የአውሮፓ ህብረት (የጀርመን መንግስት) አንድ ሚሊዮን ዩሮ ሰጥተዋል።ጋዜጠኞቻችን ሆይ፣ በወቅታዊ ጉዳያዮች ላይ እንደፈለጋችሁ ጠይቁ ከተባላችሁ ታዲያ…አንድም ሰው ካልተራበ የቢቢሲና የተባበሩት መንግስታት ሪፖርት ውሸት ከሆነ ይህ ሁሉ ርብርብ ለምን አስፈለገ? በእውነት በአሁኑ ሰዓት የተራበ ሰው ባይኖር ኖሮና መንግስት በቂ በጀት ከመደበ፣ ለለጋሽ ድርጅቶች ጥሪ ማቅረብ ለምን አስፈለገ? ብሎ የጠየቀ አለን ? ለሚሰቀል ገመድ ማቀበል ሳይሆን ተራው የማነው ብሎ መጠየቅ ጥሩ ነው ነግ በእኔ ነውና ። ሠላም በቸር ይግጠመን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule