• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ክፋት በዛ

November 17, 2015 12:17 am by Editor 1 Comment

ክፉ ቀን ብዙ ክፉ ምግባሮች ይዞ ይመጣል።

በቀይሽብር ወቅ በመቀሌ ከተማ ያጋጠመ አንድ የክፉ ምግባር ምሳሌ ነበር።

ዘስላሰ የተባለ ወጣት በፀረ ደርግነት ተጠርጥሮ የቀይ ሽብር ሰለባ በመሆን በባዛር እየተባለ የሚታወቀውና አሁን በስሙ ዘላሰ የተሰየመው የአፄ ዮሐንስ ቤተ መንግሥት ፊትለፊት የሚገኝ አደባባይ ይረሸናል። ወላጅ እናቱ በደርግ ወታደሮች ተገድደው እልልል እያሉ፣ እያጨበጨቡ ደስታቸው እንዲገልፁ ተደርገዋል።

ያ ቀይ ሽብር ክፉ ቀን የወለደው ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል። አሁንም ይሄ ጥቁር ታሪክ ዳግማዊ ትንሳኤውን አግኝቷል።

የጥቁር ታሪክ ባለቤት የሆነችው የሰሜን ወሎ ዞን፣ ቆቦ ወረዳ 027 ቀበሌ ነዋሪ እናት ወይዘሮ ብርቱኳን ዓሊ ነች። የ5 ዓመት ልጇን በረሃብ አጥታ እያነባች ለቢቢሲ የሰጠችው ቃለ ምልልስ ኢህአዴግን አስቆጥቶ ልክ እንደ የዘስላሰ እናት አስገድደው እንድታስተባብል አድርጓታል።

የአማራ ክልል ጋዜጠኞች ልክ እንደ የደርግ ወታደሮች ሁሉ ወይዘሮ ብርቱኳን የልጇን ሞት ሃዘን እንዳትችል እያዋከቡና እያስፈራሩ እንድታስተባብል አስገደዷት። ይባስ ብሎ የአሜሪካ ድምፅ VOA ጋዜጠኛ ግርማይ ገብሩም የወንጀሉ አካል መሆኑ እጅግ ያሳዝናል።

ግርማይ ገብሩ የህወሓትን ሴራ እያወቀው ልጇ በድንገተኛ ሞት እንዳጣች፣ በሬ፣ ላም፣ እህል ወዘተ እንዳገኘባት መዘገቡ ያስገምተዋል። እዚህ ላይ የአማራ ክልል ጋዜጠኞች ያስተላለፉት በቀጣይ ልጆችዋ በረሃብ እንዳታጣ መስጋትዋ ገልፃለች። ግርማይ ግን ከነሱ ብሶ መዘገቡ ያሳዝናል።

ህወሃት “የትግራይ ገበሬ 100% ሞዴል፣ የአንድ ዓመት ምርት 113 ሚሊዮን ኩንታል አመረተ”፤ ብሎ የሚዋሽ ድርጅት መሆኑ እያወቀና ጋዜጠኞች እንደሚሄዱ አውቀው የጠቀሳቸው ከብቶችና እህል አስቀድመው በቤትዋ ማስቀመጥ እንዴት ያቅታቸዋል ብሎ ያስባል?

ቅለል ያለው … ሆነ እንጂ የቢቢሲ መግለጫዋ ያስኮነነው ህወሃት UN በየቀኑ ሁለት ሰዎች ድርቅ ባስከተለው ረሃብ እየሞቱ እንዳሉ ገልፀዋል።

የቀይ ሽብር ተግባር በድርቅ ሲደገም እጅጉን ያማል። (Amdom Gebreslasie)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    November 18, 2015 11:53 pm at 11:53 pm

    >>>በቅርቡ በተካሄደው የሕወሓት 12ኛ ጉባዔ ላይ በነባሩ መሥራች አቶ ስብሃት ነጋ (አቦይ ስብሃት) ተጠቁመው የድርጅቱ ማዕክላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው የተመረጡት የሕግ መምህሩ አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ ‹‹እኔ የምለው በሙሉ የመንግሥት አቋም ነው፡፡ የተናገርኩት መንግሥት ማለት ስለፈለገው ነው፡፡ አትቆራርጡት፡፡ እንዳለ አስተላልፉት፤››ሲሉ ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋዜጠኛ ነገሩት፡፡

    __ ይህንን እኛም በምርጫው ማግስት’እንደወረደ ከወርቃማ ህዝቦች ሳይበረዝ ሳይከለስና ሳይሸራረፍ ዜና እንደምንሰማ አውቀናል..የመንግስት ኮምንኬየሽንን ቦታ ከድምፅ ማጉሊያ ጋር በመፃ ይዘውት የነበሩት ሁሉ በህወአት ጥላ ሥር ሆነው የግልና ክልላዊ የበታችነት አመለካከታቸውን መቅረፊያ መዝለፊያና የመሳደቢያ መድረክ፣ ያለነጥብ ቃላት ሲደረድሩ (GOOD) ጉድ(ፅቡቅ) ብለናል::‹‹እንግዲህ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አሉ የምትሉዋቸውን ጥያቄዎች ማንሳት ትችላላችሁ፤›› በማለት ነበር ግልፅና ተጠያቂነት ያለው ደፋር፣ብሔራዊ ቡድን የአምስት ዓመት ኮንትራቱን ለመጨረስ ‹‹አሁንም በመጥፎ ሥራው መጠየቅ ያለበት ኃላፊ ካለ ይጠየቅ!፡፡ መሰቀል ያለበትም እሱ ከሆነ የሚገባው ይሰቀል!፡፡ ሥርዓቱን ለማስተካከል ስንንቀሳቀስ ይህንን በማደናቀፍ በግልጽ ሚና ያላቸው ወገኖችና ተቋማትም ካሉ መፍረስ ያለበት ይፍረስ! መመታት ያለበት ይመታ! ›› ሲሉ መንግሥት የተግባር ዕርምጃ ለመውሰድ ቁርጠኛ አቋም መያዙን ተናግረዋል፡፡

    **አሁን በድርቅና በርሃብ መካካል ያለው የርዮተዓለምና የአተረጓጘም ልዩነት በህወአት/ኢህአዴግ ምሁራን፣ በቢቢ ጋዜጠኞች፣ አስለማኝና አበዳሪ ወይም (partners) በእያሉ በሚያቀማጥሏቸው ኪራይ ሰብሳቢ የውጭ ሕዝቦች የርሃብተኛ ቁጥር፣ የዕርዳታው በገፍና በፍጥነት መድረስ ላይ ማን ነው በበለጠና በሰለጠነ መልኩ የዋሸው? የሚለው ፍትጊያው ቀጥሏል።
    “ርሃብተኞችም የእውነት ዝናብ እስኪመጣ የርሃብን ዕንባ ያዘንባሉ!።
    … “ቢቢሲ ስለተከሰተው ድርቅ ቢጽፍ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብን የማንቃት ዓላማ ይኖረዋል ከሚል ፍላጐት እንደነበር ይናገራሉ፡፡ ‹‹የሄዱበት መንገድ ግን ሌላ ነው፡፡ ያቀረቡትም ውሸት ነው፡፡ ዘገባው የተሠራው ከቆቦ ነው የሚሉት፡፡ ልጇ የሞተባት እናት ግን ከመርሳ ናት፤›› በማለት በዘገባው ሐሰተኝነት ‹‹ያልተቀናጀ የሰነፍ ሥራ ነው የሠሩት፣ያሳዝናል፤›› ብለዋል፡፡… አቶ ጌታቸው ረዳ፡፡ ‹‹እስከ ዛሬ በረሃብ ምክንያት ለሞት የተዳረገ ሰው የለም፡፡ በድርቁ ምክንያት ለሕመም የተጋለጠ ሰው ካለ ግን የመዳን ያለመዳን ዕድሉ ከመንግሥት ሳይሆን ከእግዚአብሔር ነው፤›› ብለዋል፡፡
    … መንግሥት በስድስት ቢሊዮን ብር ከውጭ የእህል ግዥ ማከናወኑን የገለጹት አቶ ጌታቸው፣ እስካሁን ፕሮጀክቶችን ለማጠፍ የሚያስችል አደጋ አለመድረሱን አስረድተዋል፡፡‹‹በእርግጥ አንዳንድ ወገኖች ችግሩ በዚሁ ደረጃ ግዙፍ ሆኖ ከመንግሥት ቁጥጥር ውጪ ሆኖ ማየት ይፈልጋሉ፤›› በማለት፣ የአደጋው ደረጃ ግን ግዙፍ ግብረ ኃይል ለመመሥረትም እንዳልደረሰ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ምናልባት ፕሮጀክቶችን በሁለትና በሦስት ወራት ልናዘገይ እንችላለን፤›› በማለት፡፡ ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ ዕርዳታ እየቀረበ ስለመሆኑ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹እንደ ፀበል አንረጭም፡፡ ዜጐችን ከተከሰተው ድርቅ ሕይወታቸውን ለመታደግ በሚያስችል መንገድ ግን እያደረስን ነው፤›› ብለዋል፡፡ አሜሪካ በዚሁ የበጋ ወር ጀምሮ 246ሚሊዮን የምግብና የገንዘብ እርዳታ…በዚህ ሳምንት እንኳን የአሜሪካ መንግስት 97 ሚሊዮን ዶላር፣ የተባበሩት መንግስታት የስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ 17 ሚሊዮን ዶላር፣ ቻይና 8 ሚሊዮን ዶላር ፣ የአውሮፓ ህብረት (የጀርመን መንግስት) አንድ ሚሊዮን ዩሮ ሰጥተዋል።ጋዜጠኞቻችን ሆይ፣ በወቅታዊ ጉዳያዮች ላይ እንደፈለጋችሁ ጠይቁ ከተባላችሁ ታዲያ…አንድም ሰው ካልተራበ የቢቢሲና የተባበሩት መንግስታት ሪፖርት ውሸት ከሆነ ይህ ሁሉ ርብርብ ለምን አስፈለገ? በእውነት በአሁኑ ሰዓት የተራበ ሰው ባይኖር ኖሮና መንግስት በቂ በጀት ከመደበ፣ ለለጋሽ ድርጅቶች ጥሪ ማቅረብ ለምን አስፈለገ? ብሎ የጠየቀ አለን ? ለሚሰቀል ገመድ ማቀበል ሳይሆን ተራው የማነው ብሎ መጠየቅ ጥሩ ነው ነግ በእኔ ነውና ። ሠላም በቸር ይግጠመን

    Reply

Leave a Reply to በለው ! Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule