• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ

April 14, 2021 09:06 am by Editor Leave a Comment

በትግራይ ክልል በስምንት ቡድኖችና አካባቢዎች ሲንቀሳቀስ የነበረው የሕወሓት ቡድን ሙሉ ለሙሉ መደምሰሱን፣ በአገር መከላከያ ሠራዊት የደቡብ ግንባር ዋና አዛዥ ሌተና ጄኔራል ባጫ ደበሌ ማክሰኞ ሚያዝያ 5 ቀን 2013 ዓ.ም. አስታወቁ፡፡

“በትግራይ ውስጥ በስምንት ቡድኖች የተደራጀ ኃይል በአንድ ጊዜ ለመደምሰስ በሠራዊታችን ዘመቻ ተደርጎበታል፡፡ አካባቢዎቹም በምሥራቅ ትግራይ አፅቢ፣ ሐይቅ መሳል፣ ደሴአ፣ በደቡብ ትግራይ ዋጅራት፣ ቦራ፣ በሰሜን ምሥራቅ ትግራይ ጽጌረዳ፣ ሐውዜን፣ እንዲሁም በሰሜን ትግራይ ውቅሮ ማርያም፣ ዛና ናቸው፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች ሰፋ ያለ የጥቃት ድርጊት ሲፈጽሙ ስለነበር ወታደራዊ ዘመቻ ተካሂዶባቸው ተደምስሰዋል” ሲሉ ጄኔራል መኮንኑ አስረድተዋል፡፡

ባለፈው ሳምንት ሠራዊቱ ባደረገው ዘመቻ ትንንሽ ማሠልጠኛዎችንና የሕወሓት መሪዎችን እንደ ጠባቂ የሚያገለግሉ ተዋጊዎችን በማጥቃት በቁጥጥር ሥር ማዋል መቻሉን፣ አመራሮቹ ከዚህ በኋላ ሌላ ሠራዊትና ጠባቂ ይዘው ሊቀጥሉ እንደማይችሉ፣ ዘመቻውን በውጤታማነት ለማጠናቀቅም ሠራዊቱ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎችን መጠቀሙን አስረድተዋል፡፡

“ትንንሽ ማሠልጠኛዎችንና እነሱን ከቦ የሚከላከላቸውን ኃይል ማጥቃትና መደምሰስ ስለነበረ ዓላማው፣ እነዚህን አጥቅተን ሙሉ በሙሉ ተደምስሰዋል፡፡ ማሠልጠኛዎቹ ሙሉ በሙሉ እንዲጠፉ ተደርጓል፣ በማሠልጠኛዎቹ ውስጥ የነበረው የሞተው ሞቶ ሌላው ተበታትኗል፡፡ እነሱንም ከቦ ሲከላከል የነበረው ሠራዊትም በከፍተኛ ደረጃ ተመቷል፡፡ ከአሁን በኋላ ሌላ ሠራዊት መሆን በማይችልበት ሁኔታ ተደምስሷል” ሲሉ ሌተና ጄኔራል ባጫ ተናግረዋል፡፡

ሕወሓት በዚህ ደረጃ ሙሉ በሙሉ በመደምሰሱ አካባቢው ነፃ መሆኑንና ቡድኑን ለመያዝም ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጠር ያስረዱት ጄኔራል መኮንኑ፣ አመራሩን የከበበውን ሠራዊት መደምሰስ ትልቅ ፋይዳ እንደለው አስታውቀዋል፡፡

ሕወሓት የሚደርስበትን ጥቃት ለመቋቋም የሚያስችለው አቅም ላይ ባይሆንም፣ በሠራዊቱ ላይ ምንም ዓይነት የሰው ኃይል ኪሳራ እንዳይኖር ታቅዶ ዘመቻው መከናወኑን አስታውቀዋል፡፡

የሕወሓት ቡድን በተጠቀሱት ስምንት አካባቢዎች ለመቆየት የመረጠው ወደ መቀሌ የሚወስዱ መንገዶችን በመዝጋት የኅብረተሰቡን የዕለት ተዕለት ደራሽ ዕርዳታና አገልግሎት ለማጨናገፍ መሆኑን ጠቁመው፣ ነገር ግን በተካሄደበት ወታደራዊ ኦፕሬሽን ዓላማው መጨናገፉን ገልጸዋል፡፡

ብቻውን የቀረው ኃይል በሱዳን በኩል ለማምለጥ እየሞከረ ነው የሚል መረጃ መኖሩን ገልጸው፣ የመከላከያ ሠራዊቱ በሁሉም አቅጣጫ በቂ ዝግጅት ያደረገ በመሆኑ ሱዳን እንደ አዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን እንደ መቀሌም እንዲርቀው ይደረጋል ብለዋል፡፡ (ሪፖርተር)

የጄነራል ባጫ ደበሌ መግለጫ ባጭሩ

በዋነኝነት መግለጫውን የሰጡት የሰሞኑን የሰራዊቱን ወታደራዊ ኦፕሬሽን ለህዝብ ለማሳወቅ እንደሆነ ተገልጿል።

ሌ/ጄኔራል ባጫ በቅርቡ ዶ/ር አብይ አህመድ በ8 ግንባሮች ውጊያ እየተደረገ እንደነበር መግለፃቸውን አስታውሰው ይህን ጉዳይ በተመለከተ ግልፅ ማብራሪያ መስጠት ማስፈለጉን ገልፀዋል።

በትግራይ ክልል ፥ በ8 ቡድን የተደራጀና በ8 የህወሓት ቡድን አመራሮች የሚመሩ ኃይሎች ላይ በተመሳሳይ ጊዜ እርምጃ ለመውሰድ ዘመቻ መደረጉን ተናግረዋል።

አካባቢዎቹ፥ አፅቢ እና ሃይቀመሳል፣ ዴሴኣ (ምስራቅ ትግራይ)፣ ዋጅራት፣ ቦራ (ደቡባዊ ክፍል ራያ አካባቢ ያለው)፣ ፅግሬዳ (ሰሜን ምስራቅ መቐለ)፣ ሃውዜን (ሰሜን) ፣ ውቅሮ ማርያ፣ ዛና (አክሱም አካባቢ) ናቸው።

ሌ/ጄነራሉ ፥ በተገለፁት አካባቢዎች የሰፋ የ “ሽፍትነት ተግባር” በመፈፀሙ ዘመቻ ተደርጓል ብለዋል።

በእካባቢዎቹ ህወሓት ኃይል ትንንሽ ማሰልጠኛ ቦታዎች እንደነበሩት፣ የቀሩ የህወሓት አመራሮችን የሚጠብቁ ወታደሮች እንደነበሩ ተገልጿል።

አመራሮቹን ለመያዝ የከበባቸውን ወታደር ማጥቃት እና መደምሰሱ አስፈላጊ ስለነበረ ሙሉ በሙሉ መደምሰስ መቻሉን ሌ/ጄነራል ባጫ ተናግረዋል።

ማሰልጠኛዎቹ ጠፍተዋል፣ በጥቃቱ የሞተው ሞቶ የቀረው ተበታትኗል፣ አመራሮቹን ከቦ ሲከላከል የነበረው ኃይል በከፍተኛ ደረጃ ተመቷል ብለዋል። በከፍተኛ ደረጃ ተመቷል ያሉትን ሲያብራሩም የተመታው ኃይል ከአሁን በኃላ ሌላ ሰራዊት ሆኖ መቀጠል አይችልም ብለዋል።

ሌ/ጄነራል ባጫ፥ “…በእኛ የሚደርሰውን የሰው ኃይል ኪሳራ ለመቀነስ ቴክኖሎጂ እንጠቀማለን ፣ የአውሮፕላን እንጠቀማለን፣ ሂሊኮፕተር እንጠቀማለን፣ ረጃጅም ርቀት የሚሄዱ መድፌች እና ሚሳኤሎች ጥቅም ላይ እናውላለን፥ በዚህ አይነት መንገድ ነው አብሮት የነበረው ኃይል እንዲደመሰስ የተደረገው” ብለዋል።

በተጨማሪ እነሱን በተስፋ የሚጠብቁትን ተስፋ እንዲያደርጉ፣ እንዲሁም ዓለም አቅፍ በሆነ ደረጃ መኖራቸውን ለማሳየት ከላይ በተገለፁት አካባቢዎች መንቀሳቀስ እንዳስፈለጋቸው ተናግረዋል።

ነገር ግን በቅርቡ መቀሌን እንቆጣጠራለን፣ አዲስ አበባ እንገባለን፣ የሚባለውን ነገር በነሱ አቅም ፈፅሞ የሚሞከር እና የሚቀመስ አይደለም ብለዋል።

ሌ/ጄነራሉ ፥ “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀለ እና አዲስ አበባ እይገቡም” ሲሉ ተደምጠዋል።

ከላይ ከተገለፁት አካባቢዎች በተጨማሪ በአንድ ሳምንቱ ዘመቻ በተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶች እንደነበሩ የገለፁ ሲሆን በጨርጨር፣ መቻሬ፣ ዳንዲ፣ መሆኒ አካባቢዎች ችግር ለመፍጠር ሲሞክሩ የነበሩ ኃይሎች ተደምስሰዋል ሲሉ ተናግረዋል።

በተወሰደው እርምጃ ፥ ተኩሶ እንኳን ከማይመታው አውሮፕላን እና ሂሊኮፍተር ጋር የሚወጋው የህውሓታ ኃይል በብዛት እጁን እየሰጠ ነው ብለዋል።

የህወሓት ቡድን ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ደርሶበታል የሚሉት ሌ/ጄነራል ባጫ ፥ ቡድኑ ከቻለ በምስራቅ አልያም በምዕራብ በኩል ወደ ሱዳን ለመውጣት ዝግጅት እያደረገ ነው /እየተሰባሰበ ነው ብለዋል። ዝግጅቱ እዚህ ኢትዮጵያ ባለው የህወሓት ቡድን ብቻ ሳይሆን በውጭ በሱዳን በኩልም ዝግጅቶችን አሉ ሲሉ ተናግረዋል።

ሌ/ጄነራል ባጫ ፥ በመከላከያ በኩል ያለውን ዝግጅት ሲገልፁ ፥ ” እነሱ የሚያመልጡበት ፣ እኛ የማንደርስበት የኢትዮጵያ ምድር የለም፤ የትግራይ ምድርም አይኖርም” ብለዋል።

“ሱዳን እንደ መቀሌ ትርቃቸዋለች፣ የሱዳን መውጫ መንገድም እንደ አዲስ አበባ አይደልም እንደ መቐለ ትርቃቸዋለች፤ አይወጧትም” ሲሉ ተደምጠዋል። (tikvahethiopia)

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: bacha debele, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule