• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዕርቅና ድርድር ቢያይዋቸው፤ ቢያይዋቸው!

January 21, 2017 05:20 am by Editor 3 Comments

(ርዕሰ አንቀጽ)

ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታትና ከዚያም በፊት ስለዕርቅ ያልተናገረ የፖለቲካ ቡድን የለም ለማለት አይቻልም፡፡ ደርግ ስለ ዕርቅ ተጠይቆ አልሰማም አለ፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግም የአገዛዝ መንበሩ ላይ ከመቆናጠጡ ጀምሮ ስለ ዕርቅ ይወራል፡፡ አዳዲስ የሚፈለፈሉ የተቀናቃኝ ድርጅቶች በአገር ውስጥም ይሁን በውጪ ስለ ዕርቅ ያወራሉ፡፡ የገባውም ያልገባውም ስለ ዕርቅ ይናገራል፤ ይሰብካል፤ ያስተምራል፤ … ይህንን ሁሉ አልፎ “እኔም ያገባኛል” በማለት ህወሃትም ስለዕርቅ ያወራል፡፡ ከማውራትም አልፎ ያስተምራል፤ ያሠለጥናል፡፡ ሰላማዊ ጦርነት፤ ጥቁር ብርሃን፤ እንደሌለ ሁሉ ህወሃትና ዕርቅም እንደዚያው ናቸው፡፡

ስለ ድርድርም እንዲሁ ይወራል! አሸማጋይ፤ አደራዳሪ፤ አወያይ በሌለበት እንወያይ ይባላል፡፡ ሁሉንም የተቆጣጠረው ህወሃት የሚደራደሩ ተቃዋሚ ሳይሆኑ “ተጠቃሚ” ፓርቲዎችን ከመፍጠር ጀምሮ፤ አደራዳሪ፤ ተደራዳሪና ሸምጋይ ሆኖ ይቀርባል፡፡ ሥርዓት ያወጣል፤ በዚህ ተመሩ ይላል፤ አልመራም ያለውን ወደ እስር ቤት ይመራል፤ ድርድሩ አሁንም በህወሃት የበላይነት ያበቃል፡፡

የተቀናቃኝ ፖለቲካ አመራሮችን በየእስር ቤቱ እያሰቃዩ ድርጅቶችን ለድርድር መጥራት ምን ማለት ይሆን? መቼም ህወሃት/ኢህአዴግ እስር ቤት እየሄደ ሊደራደር እንዳላሰበ ግልጽ ነው፡፡ የፓርቲዎቹስ አመራሮች ይህችን ያህል ቀዳዳ ስላገኙ መስክ እንደተለቀቀ ጥጃ የሚያስቦርቃቸው ምንድነው? የህወሃት/ኢህአዴግ ቅድመ ሁኔታ ማንሳት? ሲጀመር ለምን ቅድመ ሁኔታ ተቀመጠ? ሲቀጥል መቼ ተነሳ? እውነት ይነገር ከተባለ ማነው ቅድመ ሁኔታ ማስቀመት ያለበት? ህወሃት/ኢህአዴግ ወይስ ተቃዋሚዎች? አመራሮቻቸው እና አባሎቻቸው በየእስርቤቱ እየተሰቃዩ፤ ጽ/ቤታቸው እየተዘጋና እየተዘረፈ፤ የመናገር፣ ሃሳብን የመግለጽ፣ የመጻፍና የማሰብ ድረስ መብታቸው በግልጽ እየተነፈገ ማነው ቅድመ ሁኔታ ማስቀመት የነበረበት?

ድርድርና ዕርቅ የህወሃት/ኢህአዴግ የሰሞኑ ዜማዎች የሆኑት ለምንድነው? ለኢትዮጵያ ሕዝብ ስለታሰበለት ነው? ህወሃት/ኢህአዴግ ለመሻሻል ስለፈለገ ነው? ይህ ከሆነ ሃሳቡ ሁሉን ነገር ትቶ ሚዲያውንና ምርጫ ቦርድን ብቻ ነጻ ያድርግ! ይልቅ ጉዳዩ ያለው ሌላ ቦታ ነው – ህወሃት በአንጋሽ ጌቶቹ ግልምጫ ስለደረሰበት ነው፡፡ እነርሱም ለኢትዮጵያ ሕዝብ አስበው ባይሆንም ህወሃትን ግን ክፉኛ ስላስደነገጠውና የወደፊቱ አልጨበጥ ስላለው “ዕርቅ፣ ዕርቅ፤ ድርድር፤ ድርድር” እንዲል አስገድዶታል፡፡

ለመሆኑ ዕርቅን እንዴት እንገልጸዋለን? የቀድሞዋ የፊሊፒንስ ፕሬዚዳንት ኮራዞን አኩዊኖ በጥሩ መልኩ ስለገለጹት የእርሳቸውን እንዋስ፤ እንዲህ ነበር ያሉት፤ “ዕርቅ ከፍትሕ ጋር መታጀብ አለበት አለበለዚያ ዘላቂ አይሆንም፡፡ ሁላችንም ስለ ሰላም ተስፋ ስናደርግ ሰላም በምንም መልኩ ይምጣ ማለት የለብንም፤ ነገር ግን በመርህና በፍትሕ ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት፡፡” የህወሃት/ኢህአዴግ የዕርቅ ሃሳብ ከዚህ እውነታ ፍጹም የራቀ ነው፤ ፍትሕ አልባ፤ እውነት አልባ፤ ግልጽነት አልባ – የግፍ ዕርቅ ነው! ይህ ደግሞ ዕርቅ ሊባል ፈጽሞ አይችልም፡፡

ዜጎችን ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ከመግደል እስከ ማሰቃየት ተሰምቶ የማይታወቅ ግፍ እንደፈለገ የፈጸመ፤ የልጇ አስከሬን ላይ ተቀመጪ ብሎ እናትን ያሰቃየ የወንበዴዎች ቡድን እንዴት ነው ራሱ የዕርቅ ሐዋሪያ ሆኖ፤ ራሱ የሚያዛቸውን ፓርቲዎች ለድርድር፤ ራሱ የሾማቸውን የሃይማኖት መሪዎች ለዕርቅ የሚጠራው? የሃይማኖት መሪዎችስ በየትኛው ቅዱስ መጽሐፍ የተጻፈ ዕርቅ ሊሰብኩ ነው ግፈኛ በጠራው ጉባዔ ላይ የህወሃት ሹም በከፈተውና በዘጋው ስብሰባ ስለ ዕርቅ የሚናገሩት? የተጻፈላቸውን ካላነበቡ በስተቀር በሚያስተምሩት መጽሐፍት ላይ የሚናገረው፤ ግፍ የተሰራበት ፈጣሪ አምላክ ራሱን ዝቅ አድርጎ በደል ከፈጸሙበት ጋር ሲታረቅ ነው የሚነበበው እንጂ እንደ ህወሃት/ኢህአዴግ የፈለገውን ግፍ ፈጽሞ ሲያበቃ ኑ ታረቁ እያለ ሲያስገድድ አይደለም፡፡

ዴዝሞንድ ቱቱ ይህንን ብለዋል፤ “እውነተኛ ዕርቅ ርካሽ አይደለም፤ ምክንቱም በይቅርታ ላይ የተመሠረተ ስለሆነ በጣም ውድ ነው፤ ይቅርታ በተራው ደግሞ በንሰሐ ላይ የተመሠረተ ነው፤ ይህ ደግሞ ለተሰራ ስህተት ዕውቅና በመስጠትና እውነትን ግልጽ በማድረግ ተግባር ላይ የተመሠረተ ነው፡፡”

እውነት ፍርጥርጥ ብሎ ሳይነገር ዕርቅ የለም! በእውነት አጋቢነት ፍትህና ዕርቅ በአደባባይ ጋብቻ ሲፈጽሙ ካልታየ በስተቀር ግፈኛውም ግፉን ይቀጥላል፤ ዕርቅም የግፈኛው ትርከት ሆኖ ይቀጥላል፡፡


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Lusif says

    January 21, 2017 10:39 pm at 10:39 pm

    I do not care who or what that entity is, I always admire, that is consistent and loyal to its words and objectives. The ruling party has never asked for reconciliation or peace. It believes in its strength and peace can only be maintained through the barrel of the gun. Whenever the ruling party is faced with strong demands or some kind problems, it send out let us discuss invitation letters to opposition groups. The moment the opposition receive that letter, the leadership go on setting up an equation, which never get right, but that give time and space for the ruling party to breath freely, comfortably.
    So who is naive, ignorant, shortsighted? The ruling party wants to stay in power. It wants to control the economic resources. That is what it doing whether we like it or not. Look in every aspect. The ruling party is doing what takes. Look the so called opposition, let alone being strong, the opposition is not close to match up. When one compare the ratio, it is 1:70.
    That is what I said the ruling party deserves my administration. Equally and on the other hand, I despise myself and the likes for not standing firm and consistent, as a result losing the struggle.

    Reply
  2. Ezira says

    January 23, 2017 02:20 pm at 2:20 pm

    ትክክል ብላችኋል ጎልጉሎች። እውነትና ነጋት እያደር ይጠራል እንደተባለው ሁሉ ሃቅ ተደብቆ አይኖረም። እዉነቱ ይፍረጥረጥና እርቅ መጀመሪያ ከፈጣሪ ጋር ሲቀጥል ከራስ ጋር በሰተመጨረሻም ከህዝብ ጋር የሚደረግ እርቅ ብቻ ነው ራስን ነጻ የሚያውጣ እንጅ የ COMMAND POST ጋጋታ አይደለም አራት ነጥብ።

    Reply
  3. Ezira says

    January 23, 2017 02:31 pm at 2:31 pm

    ግሩም ርዕሰ አንቀጽ ብራቮ ጎልጉሎች!
    በርቱ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule