• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ካድሬውና ገጣሚው

February 5, 2020 10:30 am by Editor 1 Comment

ሁለትም ናቸው። በግብ ግን የሚለያቸው የለም። ያን ጊዜ በአካል ላይተዋወቁ ይችሉ ይሆናል። በመንፈስ ግን የአንድ እናት ልጆች ናቸው። ትላንት ገጽ ለገጽ ሳይገናኙ፡ በስምም ሳይተዋወቁ በአንድ ካምፕ ለአንድ ሰፈር ሲጫወቱ ነበር። በመሃል መንገዳቸው ተለያየና በየፊናቸው ህይወትን ቀጠሉ። አንደኛው የህወሀት ቃለቀባይ ስጋጃ አንጣፊ ሆኖ ተከሰተ። ሌላኛው በኪነጥበብና መዝናኛ መድረኮች የጭቃ ውስጥ እሾህ ባህርይ ተላብሶ ብቅ አለ። ነገ እንደሚገናኙ ላያውቁ ይችሉ ይሆናል።

አንድ ቀን የመንፈስ ጥምረታቸውን በአካል ተገናኝተው የሚያጠናክሩበት ጊዜ እንደሚኖር ሀገር ቤት ሳሉ ላያውቁት ይችሉም ይሆናል። የባህርይ አምላክ፡ በመንፈስ ያጣመራቸው ጌታ ፍቃድ ሆኖ ግን ሳያውቁት በባህር ማዶ ተገናኙ። በአካልም በመንፈስም ተቀራረቡ። በየግል በልባቸው የተከመረውን የጥላቻና የእኩይ መንፈስ በጋራ የሚያራግቡበት፡ ትላንት ሳይተዋወቁ ለተሰለፉበት ክፉ ዓላማ ከግብ መድረስ በአንድነት የሚሰሩበት መድረክ ተመቻቸላቸው። ማን ያውቃል? ይህ ይሆን ዘንድ ቀድሞ የታቀደ ቢሆንስ? መጠርጠሩ አይከፋም።

ከሚለያያቸው ይልቅ የሚያመሳስላቸው ነገሮች ብዙ ናቸው። የባህርይ ጥምረታቸው መንታ አስመስሏቸዋል። ሲበዛ ክፉዎች ናቸው። ከሞላው ይልቅ የጎደለው የሚታያቸው፡ ከፍቅር ይልቅ ጥላቻ የሚቀናቸው፡ የሰላሙ መንገድ የሚጎረብጣቸው፡ ለቀውስና ብጥብጥ አእምሮአቸው የሚፈጥንባቸው፡ ህይወትን ከሴራ ትብታብ ውጪ ለማየት ፈጣሪ ያላደላቸው፡ ከብርሃን ይልቅ የጨለማው እድምተኛ መሆንን የመረጡ፡ አንድነት ሲኖር የሚነስራቸው፡ የልዩነት ዜማ ከአንደበታቸው የማይጠፋ በጥቅሉ እኩይ ባህሪያትና መንፈሶች ጓዛቸውን ጠቅልለው በልባቸው ቤት የሰሩባቸው የክፉዎች ሁሉ ክፉ ናቸው። ለራሳቸው ያላቸው ፍቅር የትየለሌ ነው። በራስ ፍቅር ጨርቃቸውን ጥለው ሊያብዱ የደረሱ፡ በጋጠወጥ ባህሪያቸው የሚኮሩ፡ ባልተገራ አንደበታቸው የሚመጻደቁ፡ ገብረገብ በራቀው ማንነታቸው የሚኮፈሱ፡ ሰው ሰው አለመሽተትን የስኬቶች ሁሉ ስኬት አድርገው የሚዘባነኑ የትውልድ እርግማኖች ናቸው። ኤርሚያስ ለገሰና ቴዎድሮስ ጸጋዬ።

ከሰሞኑ እፍ ያለ ፍቅር ውስጥ ናቸው። በአንድ ቂጥ ካልፈሳን ዓይነት ጥምረታቸውን ይዘው ብቅ ብለዋል። በመሃላችን ንፋስ እንኳን አይግባ ሲሉም አንድም ሁለትነታቸውን እያስተዋወቁ ነው። ስለአንድ ዓላማ የተሰለፉ ሁለት ሚዲያዎችን ይቆጣጠራሉ። በአንደኛው የጀመሩትን የጥላቻ ስብከት በሌላኛው ሚዲያ መቋጨት የየዕለት ስራቸው አድርገውታል። የዩቲዩብ ዘመን ነውና ሽቀላው ጦፎላቸዋል። ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተጎልቶ ለሚጠብቃቸው ግሪሳ የሚሆን የወሬ ቀለብ እያመረቱ በየቀኑ ብቅ ይላሉ። መቆሚያ የሌለው የጥላቻ ስብከታቸው፡ ሉጋም ያጣው የሴራ ትርክታቸው፡ መጨረሻው የማይታወቅ የውሸት ዲስኩራቸው በግሪሳው ተከታያቸው ዘንድ ክብርና ሞገስን አስገኝቶላቸዋል።

ትላንት የተናገሩትን ትተው በአዲስ መስመር አዲስ ታሪክ ሲናገሩ የማይጠይቃቸው መንጋ አላቸው። ዶ/ር አብይና ጃዋር መሀመድ አንድ ናቸው ብለው በተናገሩ ማግስት አንድ አለመሆናቸው ሲረጋገጥ ምነው ዋሻችሁን ብለው የሚይዛችው የለም። ዶ/ር አብይና አቶ ለማ መገርሳ የሚለያቸው ምንም ነገር የለም ሲሉ ከርመው ሁለቱ ሰዎች መንገዳቸው ለየቅል መሆኑ በአደባባይ ሲገለጥ ‘’አሁንስ አበዛችሁት’’ የሚላቸው ወዳጅ ከአጠገባቸው አይገኝም። ውሸታቸውንም፡ ቅጥፈታቸውንም እያላመጠ በሚውጥ ግሪሳ ተከበዋልና ነገም ከዚህ የተወላገደ መስመር የሚመልሳቸው አይኖርም። ፈጣሪ ከሰማይ ወርዶ ካልታረቃቸው በቀር።

እውነት ለመናገር እነዚህን ሁለት የአንድ መንፈስ ልጆች ሁኔታ ሳጤን አስተዳደጋቸው እንዴት ይሆን የሚል ጥያቄ ይጭርብኛል። እንደኛ ተቆንጥጠው አላደጉ ይሆን? ዘወትር ቅዳሜና እሁድ ጠዋት በቴሌቪዥን ስር ቁጭ ብለው የአባባ ተስፋዬን ምክርና ተረት እየሰሙ ልጅነታቸውን አላሳለፉ ይሆን? ታላቅን ማክበር፡ ይሉኝታ፡ ገብረገብነት፡ ጨዋነትና መሰል ኢትዮጵያዊ መገለጫ በሆኑ መልካም ነገሮች ውስጥ ሳያልፉ ይሆን የጎለመሱት? የልጅነት ስነልቦናቸው እንዴት ይሆን? ክፉው ብቻ የሚታያቸው ምክንያቱ ምንድን ነው? ጥላቻን የሚዘምሩት፡ ልዩነትን የሚሰብኩት፡ እንዴት ሆነው ቢያድጉ ነው? አንድ የእግዚያብሄር ፍጡር ከክፋት በቀር እንዴት በጎ ነገር አልታይህ ይለዋል? በኢትዮጵያ ስም እየማሉ በልባቸው የተጠመቀውን ጥላቻ እየረጩ እሰከመቼ ህይወትን ይገፏት ይሆን?

Ermias Nimani


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    February 8, 2020 06:45 am at 6:45 am

    ስለ እብዶቹ ሁለት ራህይ የሌላቸው ያለኛ ማን የሚሉ ካድሬና ቀባጣሪ የፓለቲካ ሀሁ ቆጣሪዎች ጋር ቦታ ሰጥቶ መፃፍ ጊዜ ማጥፋት ነው። ኤርምያስ ለገሰ ሶስት ምላስ ያለው አዲስ ዘንዶ ሳይሆን ይቀራል ብላችሁ ነው። ሁሉን ሰድቦና ተቃውሞ ካለኔ ኣዋቂ የለም ያለን ትዕቢተኛ ትዕቢቱ አፍርጦ እስኪጥለው ድረስ መመልከት ነው። “ስጋ ቁጠር ቢሉ ጣፊያ አንድ ኣለ እነሱ ናቸው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule