• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ካድሬውና ገጣሚው

February 5, 2020 10:30 am by Editor 1 Comment

ሁለትም ናቸው። በግብ ግን የሚለያቸው የለም። ያን ጊዜ በአካል ላይተዋወቁ ይችሉ ይሆናል። በመንፈስ ግን የአንድ እናት ልጆች ናቸው። ትላንት ገጽ ለገጽ ሳይገናኙ፡ በስምም ሳይተዋወቁ በአንድ ካምፕ ለአንድ ሰፈር ሲጫወቱ ነበር። በመሃል መንገዳቸው ተለያየና በየፊናቸው ህይወትን ቀጠሉ። አንደኛው የህወሀት ቃለቀባይ ስጋጃ አንጣፊ ሆኖ ተከሰተ። ሌላኛው በኪነጥበብና መዝናኛ መድረኮች የጭቃ ውስጥ እሾህ ባህርይ ተላብሶ ብቅ አለ። ነገ እንደሚገናኙ ላያውቁ ይችሉ ይሆናል።

አንድ ቀን የመንፈስ ጥምረታቸውን በአካል ተገናኝተው የሚያጠናክሩበት ጊዜ እንደሚኖር ሀገር ቤት ሳሉ ላያውቁት ይችሉም ይሆናል። የባህርይ አምላክ፡ በመንፈስ ያጣመራቸው ጌታ ፍቃድ ሆኖ ግን ሳያውቁት በባህር ማዶ ተገናኙ። በአካልም በመንፈስም ተቀራረቡ። በየግል በልባቸው የተከመረውን የጥላቻና የእኩይ መንፈስ በጋራ የሚያራግቡበት፡ ትላንት ሳይተዋወቁ ለተሰለፉበት ክፉ ዓላማ ከግብ መድረስ በአንድነት የሚሰሩበት መድረክ ተመቻቸላቸው። ማን ያውቃል? ይህ ይሆን ዘንድ ቀድሞ የታቀደ ቢሆንስ? መጠርጠሩ አይከፋም።

ከሚለያያቸው ይልቅ የሚያመሳስላቸው ነገሮች ብዙ ናቸው። የባህርይ ጥምረታቸው መንታ አስመስሏቸዋል። ሲበዛ ክፉዎች ናቸው። ከሞላው ይልቅ የጎደለው የሚታያቸው፡ ከፍቅር ይልቅ ጥላቻ የሚቀናቸው፡ የሰላሙ መንገድ የሚጎረብጣቸው፡ ለቀውስና ብጥብጥ አእምሮአቸው የሚፈጥንባቸው፡ ህይወትን ከሴራ ትብታብ ውጪ ለማየት ፈጣሪ ያላደላቸው፡ ከብርሃን ይልቅ የጨለማው እድምተኛ መሆንን የመረጡ፡ አንድነት ሲኖር የሚነስራቸው፡ የልዩነት ዜማ ከአንደበታቸው የማይጠፋ በጥቅሉ እኩይ ባህሪያትና መንፈሶች ጓዛቸውን ጠቅልለው በልባቸው ቤት የሰሩባቸው የክፉዎች ሁሉ ክፉ ናቸው። ለራሳቸው ያላቸው ፍቅር የትየለሌ ነው። በራስ ፍቅር ጨርቃቸውን ጥለው ሊያብዱ የደረሱ፡ በጋጠወጥ ባህሪያቸው የሚኮሩ፡ ባልተገራ አንደበታቸው የሚመጻደቁ፡ ገብረገብ በራቀው ማንነታቸው የሚኮፈሱ፡ ሰው ሰው አለመሽተትን የስኬቶች ሁሉ ስኬት አድርገው የሚዘባነኑ የትውልድ እርግማኖች ናቸው። ኤርሚያስ ለገሰና ቴዎድሮስ ጸጋዬ።

ከሰሞኑ እፍ ያለ ፍቅር ውስጥ ናቸው። በአንድ ቂጥ ካልፈሳን ዓይነት ጥምረታቸውን ይዘው ብቅ ብለዋል። በመሃላችን ንፋስ እንኳን አይግባ ሲሉም አንድም ሁለትነታቸውን እያስተዋወቁ ነው። ስለአንድ ዓላማ የተሰለፉ ሁለት ሚዲያዎችን ይቆጣጠራሉ። በአንደኛው የጀመሩትን የጥላቻ ስብከት በሌላኛው ሚዲያ መቋጨት የየዕለት ስራቸው አድርገውታል። የዩቲዩብ ዘመን ነውና ሽቀላው ጦፎላቸዋል። ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተጎልቶ ለሚጠብቃቸው ግሪሳ የሚሆን የወሬ ቀለብ እያመረቱ በየቀኑ ብቅ ይላሉ። መቆሚያ የሌለው የጥላቻ ስብከታቸው፡ ሉጋም ያጣው የሴራ ትርክታቸው፡ መጨረሻው የማይታወቅ የውሸት ዲስኩራቸው በግሪሳው ተከታያቸው ዘንድ ክብርና ሞገስን አስገኝቶላቸዋል።

ትላንት የተናገሩትን ትተው በአዲስ መስመር አዲስ ታሪክ ሲናገሩ የማይጠይቃቸው መንጋ አላቸው። ዶ/ር አብይና ጃዋር መሀመድ አንድ ናቸው ብለው በተናገሩ ማግስት አንድ አለመሆናቸው ሲረጋገጥ ምነው ዋሻችሁን ብለው የሚይዛችው የለም። ዶ/ር አብይና አቶ ለማ መገርሳ የሚለያቸው ምንም ነገር የለም ሲሉ ከርመው ሁለቱ ሰዎች መንገዳቸው ለየቅል መሆኑ በአደባባይ ሲገለጥ ‘’አሁንስ አበዛችሁት’’ የሚላቸው ወዳጅ ከአጠገባቸው አይገኝም። ውሸታቸውንም፡ ቅጥፈታቸውንም እያላመጠ በሚውጥ ግሪሳ ተከበዋልና ነገም ከዚህ የተወላገደ መስመር የሚመልሳቸው አይኖርም። ፈጣሪ ከሰማይ ወርዶ ካልታረቃቸው በቀር።

እውነት ለመናገር እነዚህን ሁለት የአንድ መንፈስ ልጆች ሁኔታ ሳጤን አስተዳደጋቸው እንዴት ይሆን የሚል ጥያቄ ይጭርብኛል። እንደኛ ተቆንጥጠው አላደጉ ይሆን? ዘወትር ቅዳሜና እሁድ ጠዋት በቴሌቪዥን ስር ቁጭ ብለው የአባባ ተስፋዬን ምክርና ተረት እየሰሙ ልጅነታቸውን አላሳለፉ ይሆን? ታላቅን ማክበር፡ ይሉኝታ፡ ገብረገብነት፡ ጨዋነትና መሰል ኢትዮጵያዊ መገለጫ በሆኑ መልካም ነገሮች ውስጥ ሳያልፉ ይሆን የጎለመሱት? የልጅነት ስነልቦናቸው እንዴት ይሆን? ክፉው ብቻ የሚታያቸው ምክንያቱ ምንድን ነው? ጥላቻን የሚዘምሩት፡ ልዩነትን የሚሰብኩት፡ እንዴት ሆነው ቢያድጉ ነው? አንድ የእግዚያብሄር ፍጡር ከክፋት በቀር እንዴት በጎ ነገር አልታይህ ይለዋል? በኢትዮጵያ ስም እየማሉ በልባቸው የተጠመቀውን ጥላቻ እየረጩ እሰከመቼ ህይወትን ይገፏት ይሆን?

Ermias Nimani


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    February 8, 2020 06:45 am at 6:45 am

    ስለ እብዶቹ ሁለት ራህይ የሌላቸው ያለኛ ማን የሚሉ ካድሬና ቀባጣሪ የፓለቲካ ሀሁ ቆጣሪዎች ጋር ቦታ ሰጥቶ መፃፍ ጊዜ ማጥፋት ነው። ኤርምያስ ለገሰ ሶስት ምላስ ያለው አዲስ ዘንዶ ሳይሆን ይቀራል ብላችሁ ነው። ሁሉን ሰድቦና ተቃውሞ ካለኔ ኣዋቂ የለም ያለን ትዕቢተኛ ትዕቢቱ አፍርጦ እስኪጥለው ድረስ መመልከት ነው። “ስጋ ቁጠር ቢሉ ጣፊያ አንድ ኣለ እነሱ ናቸው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule