• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ካድሬውና ገጣሚው

February 5, 2020 10:30 am by Editor 1 Comment

ሁለትም ናቸው። በግብ ግን የሚለያቸው የለም። ያን ጊዜ በአካል ላይተዋወቁ ይችሉ ይሆናል። በመንፈስ ግን የአንድ እናት ልጆች ናቸው። ትላንት ገጽ ለገጽ ሳይገናኙ፡ በስምም ሳይተዋወቁ በአንድ ካምፕ ለአንድ ሰፈር ሲጫወቱ ነበር። በመሃል መንገዳቸው ተለያየና በየፊናቸው ህይወትን ቀጠሉ። አንደኛው የህወሀት ቃለቀባይ ስጋጃ አንጣፊ ሆኖ ተከሰተ። ሌላኛው በኪነጥበብና መዝናኛ መድረኮች የጭቃ ውስጥ እሾህ ባህርይ ተላብሶ ብቅ አለ። ነገ እንደሚገናኙ ላያውቁ ይችሉ ይሆናል።

አንድ ቀን የመንፈስ ጥምረታቸውን በአካል ተገናኝተው የሚያጠናክሩበት ጊዜ እንደሚኖር ሀገር ቤት ሳሉ ላያውቁት ይችሉም ይሆናል። የባህርይ አምላክ፡ በመንፈስ ያጣመራቸው ጌታ ፍቃድ ሆኖ ግን ሳያውቁት በባህር ማዶ ተገናኙ። በአካልም በመንፈስም ተቀራረቡ። በየግል በልባቸው የተከመረውን የጥላቻና የእኩይ መንፈስ በጋራ የሚያራግቡበት፡ ትላንት ሳይተዋወቁ ለተሰለፉበት ክፉ ዓላማ ከግብ መድረስ በአንድነት የሚሰሩበት መድረክ ተመቻቸላቸው። ማን ያውቃል? ይህ ይሆን ዘንድ ቀድሞ የታቀደ ቢሆንስ? መጠርጠሩ አይከፋም።

ከሚለያያቸው ይልቅ የሚያመሳስላቸው ነገሮች ብዙ ናቸው። የባህርይ ጥምረታቸው መንታ አስመስሏቸዋል። ሲበዛ ክፉዎች ናቸው። ከሞላው ይልቅ የጎደለው የሚታያቸው፡ ከፍቅር ይልቅ ጥላቻ የሚቀናቸው፡ የሰላሙ መንገድ የሚጎረብጣቸው፡ ለቀውስና ብጥብጥ አእምሮአቸው የሚፈጥንባቸው፡ ህይወትን ከሴራ ትብታብ ውጪ ለማየት ፈጣሪ ያላደላቸው፡ ከብርሃን ይልቅ የጨለማው እድምተኛ መሆንን የመረጡ፡ አንድነት ሲኖር የሚነስራቸው፡ የልዩነት ዜማ ከአንደበታቸው የማይጠፋ በጥቅሉ እኩይ ባህሪያትና መንፈሶች ጓዛቸውን ጠቅልለው በልባቸው ቤት የሰሩባቸው የክፉዎች ሁሉ ክፉ ናቸው። ለራሳቸው ያላቸው ፍቅር የትየለሌ ነው። በራስ ፍቅር ጨርቃቸውን ጥለው ሊያብዱ የደረሱ፡ በጋጠወጥ ባህሪያቸው የሚኮሩ፡ ባልተገራ አንደበታቸው የሚመጻደቁ፡ ገብረገብ በራቀው ማንነታቸው የሚኮፈሱ፡ ሰው ሰው አለመሽተትን የስኬቶች ሁሉ ስኬት አድርገው የሚዘባነኑ የትውልድ እርግማኖች ናቸው። ኤርሚያስ ለገሰና ቴዎድሮስ ጸጋዬ።

ከሰሞኑ እፍ ያለ ፍቅር ውስጥ ናቸው። በአንድ ቂጥ ካልፈሳን ዓይነት ጥምረታቸውን ይዘው ብቅ ብለዋል። በመሃላችን ንፋስ እንኳን አይግባ ሲሉም አንድም ሁለትነታቸውን እያስተዋወቁ ነው። ስለአንድ ዓላማ የተሰለፉ ሁለት ሚዲያዎችን ይቆጣጠራሉ። በአንደኛው የጀመሩትን የጥላቻ ስብከት በሌላኛው ሚዲያ መቋጨት የየዕለት ስራቸው አድርገውታል። የዩቲዩብ ዘመን ነውና ሽቀላው ጦፎላቸዋል። ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተጎልቶ ለሚጠብቃቸው ግሪሳ የሚሆን የወሬ ቀለብ እያመረቱ በየቀኑ ብቅ ይላሉ። መቆሚያ የሌለው የጥላቻ ስብከታቸው፡ ሉጋም ያጣው የሴራ ትርክታቸው፡ መጨረሻው የማይታወቅ የውሸት ዲስኩራቸው በግሪሳው ተከታያቸው ዘንድ ክብርና ሞገስን አስገኝቶላቸዋል።

ትላንት የተናገሩትን ትተው በአዲስ መስመር አዲስ ታሪክ ሲናገሩ የማይጠይቃቸው መንጋ አላቸው። ዶ/ር አብይና ጃዋር መሀመድ አንድ ናቸው ብለው በተናገሩ ማግስት አንድ አለመሆናቸው ሲረጋገጥ ምነው ዋሻችሁን ብለው የሚይዛችው የለም። ዶ/ር አብይና አቶ ለማ መገርሳ የሚለያቸው ምንም ነገር የለም ሲሉ ከርመው ሁለቱ ሰዎች መንገዳቸው ለየቅል መሆኑ በአደባባይ ሲገለጥ ‘’አሁንስ አበዛችሁት’’ የሚላቸው ወዳጅ ከአጠገባቸው አይገኝም። ውሸታቸውንም፡ ቅጥፈታቸውንም እያላመጠ በሚውጥ ግሪሳ ተከበዋልና ነገም ከዚህ የተወላገደ መስመር የሚመልሳቸው አይኖርም። ፈጣሪ ከሰማይ ወርዶ ካልታረቃቸው በቀር።

እውነት ለመናገር እነዚህን ሁለት የአንድ መንፈስ ልጆች ሁኔታ ሳጤን አስተዳደጋቸው እንዴት ይሆን የሚል ጥያቄ ይጭርብኛል። እንደኛ ተቆንጥጠው አላደጉ ይሆን? ዘወትር ቅዳሜና እሁድ ጠዋት በቴሌቪዥን ስር ቁጭ ብለው የአባባ ተስፋዬን ምክርና ተረት እየሰሙ ልጅነታቸውን አላሳለፉ ይሆን? ታላቅን ማክበር፡ ይሉኝታ፡ ገብረገብነት፡ ጨዋነትና መሰል ኢትዮጵያዊ መገለጫ በሆኑ መልካም ነገሮች ውስጥ ሳያልፉ ይሆን የጎለመሱት? የልጅነት ስነልቦናቸው እንዴት ይሆን? ክፉው ብቻ የሚታያቸው ምክንያቱ ምንድን ነው? ጥላቻን የሚዘምሩት፡ ልዩነትን የሚሰብኩት፡ እንዴት ሆነው ቢያድጉ ነው? አንድ የእግዚያብሄር ፍጡር ከክፋት በቀር እንዴት በጎ ነገር አልታይህ ይለዋል? በኢትዮጵያ ስም እየማሉ በልባቸው የተጠመቀውን ጥላቻ እየረጩ እሰከመቼ ህይወትን ይገፏት ይሆን?

Ermias Nimani


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    February 8, 2020 06:45 am at 6:45 am

    ስለ እብዶቹ ሁለት ራህይ የሌላቸው ያለኛ ማን የሚሉ ካድሬና ቀባጣሪ የፓለቲካ ሀሁ ቆጣሪዎች ጋር ቦታ ሰጥቶ መፃፍ ጊዜ ማጥፋት ነው። ኤርምያስ ለገሰ ሶስት ምላስ ያለው አዲስ ዘንዶ ሳይሆን ይቀራል ብላችሁ ነው። ሁሉን ሰድቦና ተቃውሞ ካለኔ ኣዋቂ የለም ያለን ትዕቢተኛ ትዕቢቱ አፍርጦ እስኪጥለው ድረስ መመልከት ነው። “ስጋ ቁጠር ቢሉ ጣፊያ አንድ ኣለ እነሱ ናቸው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule