• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

Tank Man 1989

June 5, 2018 08:00 pm by Editor 7 Comments

የዛሬ 29 ዓመት በቻይና የታይናንመን አደባባይ የሆነውን ታሪክ ስናስብ “ታንክ ማን” ወይም በግልቡ የአማርኛ ትርጉም “ታንክ ሰው”ን እናስባለን። እናያለን። የወቅቱን ገድሉን እናስባለን። ወደ አገራችን ስንመለስ ምንም እንኳን ምንም ያልተባለላቸው ጀግኖች ያለመታወሳቸው ሊያሳዝነን ሲገባ፣ አሉ የሚባሉት ላይ መማማል መመረጡ በቃላት ሊገለጽ የማይችል የሃዘን አዙሪት ውስጥ ይከተናል።

ከሁሉም በላይ ደም ሰፍረን ትርፍ እንሻለን። ለአገር ክብርና ልዕልና ያለፉትን የማይተኩ ዜጎች የግብር ማወራረጃ ለማድረግ ይዳዳናል። ህወሓት “በሞተብኝ መጠን ልዝረፍ” በሚል ቀረርቶ ል27 ዓመታት ያደነቆረንና ለዚሁ ግልብ ዓላማው የጨፈጨፈን፣ የደገንብን ታንክና አፈሙዝ፣ ያሰረን፣ ያቆሰለን፣ የገረፈን ሳያንስ ዛሬም በተመሳሳይ “የእኛ ደም” በሚል ክፍያ ሲጠየቅ ሰምተናል።

ከሁሉም በላይ ደግሞ አሳዛኙና አስገራሚው ስህተትን ከመቀበልና ይቅርታ ከመጠየቅ ይልቅ ማስተባበያ በመስጠት በአንድ ጀንበር ስህተት በስህተት ሲሞሸር ማየት ነው። በርካቶች ተመሳሳይ ስህተት ቢሰሩም የሰሞኑ የአቶ በቀለ ገርባ አካሄድ ጎልቶ የሚወጣ ነው።

አቶ በቀለ በበርካቶች የሚመሰገኑ፣ የሚወደዱ ናቸው። ትንሽ ትልቅ ሳይባል፣ ክልልና አድራሻ ሳይለይ ሁሉም አልቅሶላቸዋል። ዘምሮላቸዋል። ጮሆላቸዋል። እሳቸውም ከእስር ሲወጡ ይህንኑ የሕዝብ እሪታና መስዋዕትነት በወጉ አክብረው ምስጋና አቅርበዋል።

ዋሽንግቶን ዲሲ ስለኢትዮጵያ ለአሜሪካኖቹ ሲናገሩ ከቆዩ በኋላ ሚኖሶታን ሲረግጡ ቋንቋቸው ተቀየረ። ቀጥሎም አንዱን ከሌላው ስለማወዳደር እንዴት ሊያስቡና እንዴት እዚያ ጉሮኖ ውስጥ ሊገቡ እንደቻሉ ግራ በሚያጋባ ደረጃ “ተጠቃሚነትን” በኦሮሞ ልጆች ደም ሰፍረው መናገራቸው፤ “ፍቱኝ ብዬ አልጠይቃችሁም አብሬያችሁ የሠራሁበትን ጊዜ እንደውለታ ቆጥራችሁ የሞት ፍርዱን ተግባራዊ አድርጉ፤ “ሰው እየሳቀ መሞት እንደሚችል አሳያችኋለሁ” ብሎ የተናገረን ታጋይ ለንፅፅር ማቅረብን ምን አመጣው? እንዴትስ ታሰበ? አሳዛኝ፣ አስደንጋጭ፣ ለማመን የሚያስቸግር! “እነሱ”ና “እኛ” ብሎ ማስላት!! ሰው “ውለታ ቆጥራችሁ ግደሉኝ” ሲል ደም በመስፈር ውለታን መናፈቅ!!

የትርጉም ስህተት እንደተሠራና እንዲስተባበል ቢሞከርም፣ የተባለው የትርጉም ስህተት ተፈጽሞ ቢሆንም፣ የተኬደበት የንፅፅር መንገድ አቶ በቀለን ከተቀመጡበት የክብር ማማ እንዳወረዳቸው አያጠራጥርም። ከምንም በላይ ሊገሩ የሚገባቸውን ከመግራት ይልቅ እሳቸው “የሚገሩ” ሆነው መገኘታቸው አስደምሞናል። ከአንድ የፊደል አባት፣ ከአንድ ፈጣሪውን እንደሚያምን ከሚናገር ሰው፣ ከአንድ ብሩክ ቤተስብ መውጣቱን ከሚናገር ሰው፣ አንድ አገሪቱን አሁን ከገባችበት ቀውስ አሻግራለሁ ከሚል የተፈተነ ታጋይና አታጋይ … የማይጠበቅ ተግባር በመስማታችን ማዘናችንን አጠንክረን ስንገልጽ በቂ ምክንያት አለን።

በርካታ ፖለቲከኛና አክትቪስት ነን የሚሉ ስህተት ውስጥ ገብተው ሲንቦጫረቁ ለይተን አልተናገርንም። በኦሮሚያ የተከፈለውን ዋጋ ብናውቅም በጋምቤላ፣ በአማራ፣ በኦጋዴን፣ በደቡብ፣ በሁሉም አቅጣጫ ደም መፈሰሱን፣ ግፍ መፈጸሙን፣ አሁንም ድረስ እየተፈጸመ መሆኑንን የሚከራከር ባይኖርም ደምን ለክቶና ሰፍሮ በደም የነገደ የምናውቀው ወያኔን ብቻ በመሆኑ አቶ በቀለን በግልጽ ይቅርታ እንዲጠይቁ ማበረታታት ግድ ሆኖብናል፤ “ትሳስቻለሁ” ብሎ ይቅርታ መጠየቅ ቀላልና የሰላማዊ ታጋይ መለያው ነው። ምክንያቱም ለአገራችን የሚያስፈልጉ ሰው ናቸውና! ከፈለጉ! እስኪ ወደ “ታንክ ሰው” ታሪክ እንመለስ!

በተለያዩ ስሞች ይጠራል፤ ታንክ ሰው፣ ያልታወቀው ተቃዋሚ፣ ያልታወቀው ዓማጺ፣ ወዘተ። ስሙን ያገኘው የዛሬ 29 ዓመት ነበር።

በወቅቱ የተማሪዎች እንቅስቃሴ ቻይናን እየናጣት ነበር። ተማሪዎቹ ያነሷቸው ጥያቄዎች ዘርፈ ብዙ ቢሆኑም ዋንኛዎቹ ግን ከውሱን የፖለቲካ ተሳትፎ፣ ከዋጋ ንረት፣ ከኢኮኖሚ ተሃድሶ፣ ከፖለቲካ ሙስና፣ ከወገንተኝነት፣ ወዘተ ጋር የተጣመረ ነበር። በመሆኑም ዴሞክራሲ፣ ተጠያቂነት፣ የፕሬስና የመናገር ነጻነት፣ ወዘተ በቻይና እንዲሰፍን በተማሪዎቹ ጥያቄዎች ውስጥ የተካተቱ ነበር።

ለበርካታ ወራት በተቃውሞ ጥያቄያቸውን ሲያሰሙ የነበሩት ተማሪዎች የተሰበሰቡት በቤይጅንግ በሚገኘው የታይናንመን አደባባይ ነበር። አደባባዩ በተቃውሞ ሲናጥ ከከረመ በኋላ የቻይና ኮሙኒስታዊ አገዛዝ 200,000 የጦር ሠራዊቱን ወደ ወደዚያው ላከ። በዚያም በጥይት እሩምታ በርካታዎችን ገደለ፤ አቆሰለ። የሞቱትን ቁጥር እስካሁን ለማወቅ ካለመቻሉ የተነሳ የሚሰጠው ግምትም የዚያኑ ያህል በጣም የሰፋ ነው፤ ከ180 – 10,454!

ይህ እጅግ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ከተካሄደ በኋላ በነጋታው ጁን ፭ ቀን ተጨማሪ በርካታ ታንኮች ወደ አደባባዩ ይላካሉ። አንድ ነጭ ሸሚዝ የለበሰና በሁለት እጆቹ ፌስታል ላስቲኮች የያዘ ሰው ቀዳሚው ታንክ ፊት ይቆማል። ከፊት ለፊቱ ሲደርስ ታንኩ ይቆማል። በቪዲዮው ላይ በግልጽ እንደሚታየው ታንኩ ወደ ግራና ቀኝ ብሎ ለማለፍ በሁለቱም አቅጣጫ ሲሞክር ሰውየው ይከላከላል። በእጁም ከዚህ ሂዱ በሚመስል ሁኔታ ተቃውሞ ያሳያል። በመቀጠልም ታንኩ ላይ ይወጣል፤ ውስጥ ካሉት ጋር የሚነጋገር በሚመስል ሁኔታ ትንሽ ከቆየ በኋላ ይወርዳል።

በመቀጠል ፊት መሪው ታንክ ለመሄድ ሲያኮበኩብ ሰውየው አሁንም በፊት ለፊት በመቆም ታንኩን ይጋፈጣል። በመጨረሻ ሁለት ሰዎች እየሮጡ ሄደው ከመንገድ ካወጡት በኋላ ታንኮቹ ጉዟቸውን ቀጠሉ። ከዚያ ወዲህ የዚህ ታንክ ያስደገደገ፤ ለብቻው ብረት ለበስ የተገዳደረ ሰው መጨረሻ አልታወቀም። አንዳንዶች በቻይና አገዛዝ ተገድሏል ይላሉ። ሌሎች ደግሞ አምልጦ ወደ ታይዋን ሄዷል ሲሉ ይህንን የማይቀበሉ ደግሞ እስካሁን የት እንዳለ አለመታወቁ እዚያው ቻይና ውስጥ ድምጹን አጥፍቶ እየኖረ በመሆኑ ነው ይላሉ።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገራችን እየታየ ለሚገኘው ለውጥ እጅግ በርካታ ታንክ ያንበረከኩ ወገኖቻችን ተሰውተዋል። ክቡርና መልሶ የማይገኝ ህይወታቸውን ሰውተዋል። ዘር፣ ቋንቋ፣ ቀለም፣ አካባቢ፣ የትውልድ ሐረግ፣ ወዘተ ሳይለይ የህወሓትን አግአዚ ፊትለፊት በመጋፈጥ ደማቸውን አፍስሰዋል፤ አጥንታቸውን ከስክሰዋል።

ሰልፍ የማይወጣላቸውና ያልተወጣላቸው፤ መዝሙር ያልተዘመረላቸውና የማይዘመርላቸው፤ በመስዋዕትነታቸው ምንም ያልተጠቀሙና ወደፊትም የማይጠቀሙ፤ ከነጻነት በስተቀር ለሚያራምዱት የፖለቲካ ርዕዮትም ወይም ወገኔ ለሚሉት ዘር ያልኖሩ፣ ያልሞቱ፤ ለዚህች ታላቅ አገር ግን የማይመለሰውን ህይወታቸውን የገበሩ ብዙ ኢትዮጵያውያን ነበሩ፤ አሁንም አሉ፤ ወደፊትም ይኖራሉ። ኢትዮጵያ እስካለች ድረስ ሁልጊዜ መስዋዕትነታቸው ሲታሰብ ይኖራል። እነዚህ የኢትዮጵያ “ታንክ ሰዎች” ናቸው! ከታንክም በላይ!! ደም ሰፍረው ጥቅምን በንፅፅር የማይጠይቁ!!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: bekele gerba, Full Width Top, Middle Column, tank man

Reader Interactions

Comments

  1. Ezira says

    June 7, 2018 01:07 am at 1:07 am

    ያስለቅሳል !!! የኦቦ በቀለ ነገር። ያችን ሽሙንሙን ወጣት ንግሥት ይረጋንም አሰብኳት። ሽሙንሙኗ ወጣት ዕስር ቤት ወጥታ ቮኦኤ ስለ እስሯ ሁኔታ ሲጠይቃት በእግረ መንገዷ ስለ አቶ በቀለ ገረባ አንስታ ነበር። ስለሳቸውው ስታነሳ እንዲህ ብላ ነበር አቶ በቀለ ገረባን የጠራቻቸው። በተለይ አባታችን አቶ በቀለ ገርባ ብላ የጐንደሯ ልዕልት በሚጣፍጥ ለዛዋ ስትጠራቸው ፣ አንጀት ታላውስ ነበር። ሰሞኑን ግን ከ አቶ በቀለ ገርባ አንደበት የሠማነው ነገር ሆድ ይቆርጣል። ያዉም አብሯቸው በእስር ሲማቅቅ የቆየን ሰው አንስተው (ለምን ተፋታ) እስኪመስለን ድረስ አሳዝኖናል።የሰው ልጅ በሠው ሲጨቅን ከዚህ በላይ ምን ማሳያ አለ?

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    June 7, 2018 07:40 pm at 7:40 pm

    ጎልጉሎች!! ምን ይሁን ነው የምትሉት!?? እናንት ጨበርባሪዎች! ዛሬ መርካቶ፣ ነገ ኣጋሮ፣ ከነገ ወዲያ ሓዋሳ፣ከዚያም ወዲያ ወልቂጤ፣ቀና ኣለፍ ፣ሰንበትበት ስትል፣ ጥቢ ሲሆን በመስቀል ኣሳባችሁ፣ ተመልሳችሁ፣መርኬ ቁጭ ነዋ!!! ኣይደል ጭብርብሮች??

    Reply
  3. Salem says

    June 8, 2018 08:24 pm at 8:24 pm

    Dear Golgul Editors,
    Mulugeta Andargie is a cyber bully; his comments are ethnic slurs and essentially racist. By publishing them your journal is complicit and liable to censure, including loss of the privilege of using your account. I hope you understand and take your responsibility seriously. Thanks.

    Reply
    • Editor says

      June 11, 2018 08:13 am at 8:13 am

      Salem,

      Your comment is noted. We know all about him – we’ve got the needed info.

      If this comes more from our readers we can go as far as banning him from here.

      Thanks

      Editor

      Reply
      • Salem says

        June 12, 2018 07:42 pm at 7:42 pm

        Thank you for your response. I think you need to delete all comments by Mulugeta Andargie that contain ethnic slurs and report him to Google. Thanks again for your good work.

        Reply
        • Editor says

          June 13, 2018 10:19 pm at 10:19 pm

          We always monitor those – be it a comment by him or anyone else. However, if you have seen one, please let’s know.

          Thanks

          Editor

          Reply
  4. Rose says

    June 12, 2018 07:06 pm at 7:06 pm

    ልብ ላለዉ የአቶ በቀለ ገርባ የሰሞኑ ድርጊት ታላቅ ትምህርት ነዉ። ሰዉ ቋሚ አይደለም፣ ሁሌም ይሁዳዎች አሉ። ሰወችን ማጀገን እንጅ ማምለክ ማቆም አለብን። ማንንም ቢሆን።
    ልደቱ በ1995 የቤት ዉስጥ እገታ በተደረገበት ጊዜ ሂደቱ ድራማ መሆኑን ከልደቱና ከበረከት በስተቀር ማን ያዉቅ ነበር? ለዚህ ነበር የኢትዬጵያ ህዝብ ሰማዕት ሆነልኝ ብሎ ያሰበዉን ልደቱ በቁም የተነሳዉን ፎቶ፣ ፎቶ ኮፒ 10ብር (በወቅቱ10ብር ብዙ ነበር) እየገዛ ጾለት ቤቱ የሰቀለዉ። ሰወች ጥቂት መልካም ነገር ሲያረጉ ማዕረጋቸዉን ከቅዱሳን ከፍታ ጋር ማድረስ ቢቀር። ሰዉ ሲሞት ብቻ ነዉ በትክክል ስለማንነቱ መናገር የሚቻለዉ። አመሟቴን አሳምርልኝ የሚለዉ ጾለት ትርጉምም ይኸዉ ነዉ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule