• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዲስ አበባ ሳያርፉ በቀጥታ ወደ ትግራይ ክልል በአየር ዕርዳታ ማድረስ አይቻልም

July 11, 2021 07:10 pm by Editor Leave a Comment

ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ማስጠንቀቂያ መስጠቱን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ።  

መንግሥት ዓርብ ሐምሌ 2 ቀን 2013 ዓ.ም. አመሻሽ ላይ ባወጣው መግለጫ እንዳሰታወቀው፣ የተባበሩት መንግሥትታት ድርጅት የሰብዓዊ ዕርዳታ አስተባባሪ የሆነው ተቋም፣ የኢትዮጵያን ሕግ ያላከበረ ድርጊት በተደጋጋሚ እየፈጸመ ከመሆኑም በላይ፣ በትግራይ ክልል ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ የሚያዛባ መግለጫ እያወጣ መሆኑን በመግለጽ ለተቋሙ ማስጠንቀቂያ ጽፏል፡፡

“በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀውን ድርጅት የትግራይ መከላከያ ኃይል በማለት በሚያወጣው መግለጫ በተደጋጋሚ ጊዜ እየጠቀሰ ነው፡፡ በትግራይ ክልል ስላለው ሁኔታ የሚያወጣው መረጃ የተዛባና ሕገወጥ የተባለውን ኃይል የሚያበረታታ ነው” በማለት ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ አስጠንቅቋል።

ተቋሙ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት ከሚያበላሹ ድርጊቶቹ እንዲታቀብና የእርማት ዕርምጃዎችን እንዲወሰድ፣ ለተቋሙ በደብዳቤ ማሳወቁንም መግለጫው አመልክቷል።

በሌላ በኩል በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ዕርዳታ በአየር ትራንስፖርት ማቅረብ ለሚፈልጉ አካላት የበረራ ፈቃድ መሰጠት መጀመሩን መንግሥት ያሳወቀ ሲሆን፣ ይህም ደንብና አሠራርን ተከትሎ እንደሚከናወን ገልጿል።

በዚሁ መሠረት ማንኛውም የሰብዓዊ ዕርዳታ ድርጅት አውሮፕላን፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ ጭኖ ሲመጣ በቀጥታ ማረፍ ያለበት አዲስ አበባ እንደሚሆንና ዕርዳታውን ወደ ክልሉ ካደረሰ በኋላም ተመልሶ አዲስ አበባ ማረፍ እንዳለበት አስታውቋል፡፡

በመሆኑም አዲስ አበባ ሳያርፍ በቀጥታ ወደ ትግራይ ክልል የሚደረግ በረራ እንደማይኖር፣ ከትግራይ ክልል ወደ አዲስ አበባ ሳይመለስ በቀጥታ ከኢትዮጵያ የአየር ክልል መውጣት እንደማይቻል አስታውቋል።

ከሰኞ ሐምሌ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ለሰብዓዊ ዕርዳታ አቅራቢዎች ወደ ትግራይ ክልል የአየር በረራ ፈቃድ መስጠት መጀመሩን ያስታወቀው መንግሥት፣ እስካሁን ወደ ክልሉ በረራ ለማድረግ የጠየቀው የዓለም የምግብ ድርጅት የዕርዳታ ሠራተኞችን ለማጓጓዝ መሆኑን አስታውቋል።

በትግራይ ክልል ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ምግብና ምግብ ነክ ድጋፎችን የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች፣ ከሐምሌ 2 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ክልሉ መንቀሳቀስ መጀመራቸውንም መንግሥት አስታውቋል።

በዚህም መሠረት በዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች አማካይነት ከ40 የሚበልጡ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ከአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ሰብዓዊ ዕርዳታ ጭነው ወደ ትግራይ መንቀሳቀሳቸውን ገልጿል። (ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tigray

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule