• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዲስ አበባ ሳያርፉ በቀጥታ ወደ ትግራይ ክልል በአየር ዕርዳታ ማድረስ አይቻልም

July 11, 2021 07:10 pm by Editor Leave a Comment

ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ማስጠንቀቂያ መስጠቱን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ።  

መንግሥት ዓርብ ሐምሌ 2 ቀን 2013 ዓ.ም. አመሻሽ ላይ ባወጣው መግለጫ እንዳሰታወቀው፣ የተባበሩት መንግሥትታት ድርጅት የሰብዓዊ ዕርዳታ አስተባባሪ የሆነው ተቋም፣ የኢትዮጵያን ሕግ ያላከበረ ድርጊት በተደጋጋሚ እየፈጸመ ከመሆኑም በላይ፣ በትግራይ ክልል ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ የሚያዛባ መግለጫ እያወጣ መሆኑን በመግለጽ ለተቋሙ ማስጠንቀቂያ ጽፏል፡፡

“በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀውን ድርጅት የትግራይ መከላከያ ኃይል በማለት በሚያወጣው መግለጫ በተደጋጋሚ ጊዜ እየጠቀሰ ነው፡፡ በትግራይ ክልል ስላለው ሁኔታ የሚያወጣው መረጃ የተዛባና ሕገወጥ የተባለውን ኃይል የሚያበረታታ ነው” በማለት ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ አስጠንቅቋል።

ተቋሙ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት ከሚያበላሹ ድርጊቶቹ እንዲታቀብና የእርማት ዕርምጃዎችን እንዲወሰድ፣ ለተቋሙ በደብዳቤ ማሳወቁንም መግለጫው አመልክቷል።

በሌላ በኩል በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ዕርዳታ በአየር ትራንስፖርት ማቅረብ ለሚፈልጉ አካላት የበረራ ፈቃድ መሰጠት መጀመሩን መንግሥት ያሳወቀ ሲሆን፣ ይህም ደንብና አሠራርን ተከትሎ እንደሚከናወን ገልጿል።

በዚሁ መሠረት ማንኛውም የሰብዓዊ ዕርዳታ ድርጅት አውሮፕላን፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ ጭኖ ሲመጣ በቀጥታ ማረፍ ያለበት አዲስ አበባ እንደሚሆንና ዕርዳታውን ወደ ክልሉ ካደረሰ በኋላም ተመልሶ አዲስ አበባ ማረፍ እንዳለበት አስታውቋል፡፡

በመሆኑም አዲስ አበባ ሳያርፍ በቀጥታ ወደ ትግራይ ክልል የሚደረግ በረራ እንደማይኖር፣ ከትግራይ ክልል ወደ አዲስ አበባ ሳይመለስ በቀጥታ ከኢትዮጵያ የአየር ክልል መውጣት እንደማይቻል አስታውቋል።

ከሰኞ ሐምሌ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ለሰብዓዊ ዕርዳታ አቅራቢዎች ወደ ትግራይ ክልል የአየር በረራ ፈቃድ መስጠት መጀመሩን ያስታወቀው መንግሥት፣ እስካሁን ወደ ክልሉ በረራ ለማድረግ የጠየቀው የዓለም የምግብ ድርጅት የዕርዳታ ሠራተኞችን ለማጓጓዝ መሆኑን አስታውቋል።

በትግራይ ክልል ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ምግብና ምግብ ነክ ድጋፎችን የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች፣ ከሐምሌ 2 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ክልሉ መንቀሳቀስ መጀመራቸውንም መንግሥት አስታውቋል።

በዚህም መሠረት በዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች አማካይነት ከ40 የሚበልጡ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ከአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ሰብዓዊ ዕርዳታ ጭነው ወደ ትግራይ መንቀሳቀሳቸውን ገልጿል። (ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tigray

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule