• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእኔ፣ ያንተ፣ የእናንተ፣ የእኛ ተጠቂዎች!

November 1, 2015 05:09 pm by Editor Leave a Comment

የብላቴናው መሀመድን እናት እርዳታ አድራጊ ወገኖቸ የቻልኩትን እርዳታ ለመሰብሰብ ወጣ ባልኩበት አጋጣሚ ስልክ ተደወለልኝ። አነሳሁት፣ ከሰላምታ በኋላ “ጠፋህ? የት ነው ያለህ?”  ከሚለው አጭር የተለመደ የሰላምታ ማጀቢያ በኋላ ወዳጀ ወደ መልዕክታቸው  ገቡ …

“አንተ ነብዩ የት ጠፋህ?” ሲሉ ደገሙና ስመለጥፋቴ ጠይቀውኝ ሲቀጥሉ “ናና አንድ እህት ከጅዳ ቆንስል በር ወድቃለች፣ ጸሀይ እየደበደበ አድክሟታል! እነሱ (የቆንስል ሰዎች ማለታቸው ነው) ቢነግሯቸው አይሰሙም። ሌላም ሶስት እህቶች ከቆንስሉ አጠገብ ካለው ንጉድ ፉአድ ሆስፒታል ያለ ጠያቂ ተኝተዋል። ጎብኟቸውና ችግራቸውን ተረዱ ወይ መፍትሄ ፈልጉ ወይ ወደ ሀገር  ስደዷቸው ብል የሚሰማ የለም! አንተን ከሰሙህ ናና እያቸው!” ብለው ቁጣ የተቀላቀለበት መልዕክት አስተላለፈውልኝ ተጣድፈው ስልኩን ዘጉት … ! የእኒህ ወንድም መረጃ ሲያቀብሉኝ በስጨት ማለት ምክንያቱ ገብቶኛልና አልተከፋሁም፣ ይልቁንም ስለሰጡኝ መረጃ አመሰገንኳቸው። …

አሁን አሁን በኮንትራት መጥተው ጠፍተው ሲሰሩ የነበሩት፣ በባህርም ሆነ በቀድሞው ሃጅና ኡምራ  መጥተው በአሰሪዎቻቸው መደፈር መደብደብን ጨምሮ ፈርጀ ብዙ በሆነ ምክንያት  የተለያየ ጥቃትም ሆነ ህመም ሲያጠቃቸው መጥተው የሚወድቁት በዚሁ በጅዳ ቆንሰል በር ነው። ለምን ቢባል ዘንድሮ  ህጋዊ መኖሪያ ፍቃድ የሌላቸውን ማስጠጋት አደጋ አለውና ነው፣ አደጋው ደግሞ ቤተሰብን ጠቅልሎ ከሀገር መባረር ነውና ያስፈራል። ይህ የከፋ ችግር የተጋረጠበት የጨነቀው ነዋሪ እየፈራ እየተባ ያስጠጋው ነዋሪ ወደ ሀገር ይገባ ዘንድ ከቆንሰል መስሪያ ቤቱ ጋር ሞግቶ አልሳካለት ሲል ከቀጣዩ አደጋ ራሱን ለመከላከል የስጋ ዘመዱን ሳይቀር በጠራራው ጸሀይ ጨክኖ አምጥቶ የሚጥለው በቆንስሉ በር ላይ ነው!eth

ያን ሰሞን አንድ ወዳጀ “በቆንስሉ በር የወደቀች ልጅ አለች እያት ታሳዝናለች!” የሚል መረጃ አደረሰኝና ወደ ዚያው አቀናሁ፣ ሙቀት ያደከማት፣ ውሃ ጥም ያደረቃትን እህት አገኘኋት፣ ከመኪናየ ውስጥ የነበረውን ውሃ ስሰጣት ተንሰፍስፋ ስትጠታው የተሰማኝን ህመም ሳስበው እታመማለሁ … ልጅቱ በዥጉርጉሩ ፎቴ ተዘርራ የምታዮዋትን ናት፣ ውሃው ድካሟን አልመለሰውም፣ ተንፈስ ማለት ችላለች … ያም ቢሆን የዋለባት ሙቀቱ አድክሟት ያዝ ለቀቅ እያደረገች ያጫወተችኝ የቅርብ ዘመዶችዋ በቆንስል መስሪያ ቤቱ በኩል ወደ ሀገር የመጓጓዣ ሰነድ አውጥተው ለመስደድ ሞክረው አልሆን ሲላቸው አምጥተው እንደጣሏት ነበር  … ስሜቴ በጣሙን ተነክቶ ወደ አምባሳደር ውብሸት በላኩት መልዕክት ቦታውን ሳልለቅ ወደ መጠለያው ለመግባት ፈቃድ በማግኘቷ ቆንስሉ ልትሞት የነበረቸውን እህትን የታደጋትን ያህል ተደሰትኩ …

ዛሬ ከሰዓታት በፊት ያየኋት እህት በጠራራው ጸሃይ በቆንስሉ በር ተዘርራ ተኝታ ነበር፣ አትሰማም አትናገር ። ብዙዎቻችን ከንፈራችን እየመጠጥን ስናልፋት በመኪና የሚተላለፉት አረቦች ሲያዩዋት መኪናቸውን አቁመው “ለምን ወደ ግቢ  አታስገቧትም? ለምን አንቡላንስ አትጠሩም?” እያለ እያዘኑ “ፈጣሪ ይድረስልሽ ፣ ምስኪን!” እያሉ  ይሄዳሉ … እያየን ወደ ሀላፊዎች ስልክ ደውለን ለማሳወቅ እንኳ “ተቃዋሚ ምንቴስ ” እንባላለን ብለን ከምንፈራው ብዙዎች የተሻሉ የምላቸው የሳውዲ መንግስት የቆንስሉ ጠባቂዎች ደጋግመው ወደ ቀይ ጨረቃ ደውለው አምቡላንስ አልመጣ ቢልም ጉዳዩን ወደ አንድ ጉምቱ ባለስልጣን በመድረሱ አምቡላንሱ ፈጥኖ ሳይመጣ አይቀርም! እኔም እንደ አልፎ ሂያጁ አረብ “ምስኪን! ፈጣሪ ይድረስልሽ!” ከማለት ውጭ የምለው የለም… !

እኛ ቅንጡዎች “ራሳችን፣ ሆድ እቃ፣ እግር እጅ፣ አይናችን አመመን!” ብለን አገር ይያዝ ብለን በምንቀውጥበት ሰማይ ስር ያየሁት የማይታመን አይደለም፣ ይህችና ይህችን መሰል እህቶች በሀገራችን የመንግስት ተወካይ፣ የማህበረሰብና የፖለቲካ ድርጅት ተወካዮችና የደላ የሞላልን ሳይሆን ሳይደላን በሽፍንፍን ህይዎት አሸሸ ገዳሜ በምንልበት አዳራሽና ቆንስል በር በተደጋጋሚ ይጣላሉ፣ ያለላቸው ተርፈው ያላለላቸው “ሰርታ ታሻሽለኛለች!” ብሎ ለላከላቸው ወላጅ የህይዎት እንቆቅልሽ ይሆኑ ዘንድ  ማንነታቸው ሳይታወቅ ወደ ማይቀረው አለም ይሸኛሉ (… የሳውዲ መንግስት በነጻ የሚሰጠው  ህክምና አይደለም ቀዝቃዛ ውሃ ናፍቋቸው፣ ይህችን አለም ሲሰናበቱ ማየት በእርግጥ ያማል … (ይህን አይቶ ዝም ማለቱም ለእኔ ሌላ እዳ ነውና ያማችሁ ዘንድ ብቻ ሳይሆን የሚመለከታቸው መፍትሄ ይፈልጉለት ዘንድ እነግራችኋለሁ!

ደረቁ እውነት ይህ ነው … እኒህ በየሜዳው ተጥለው የሚጠፉት እህቶች ከወላጅ ጀምሮ፣ የመንግስት፣ የነዋሪው፣  የማህበረሰብ ተወካዮች፣ ይህ መከራ መቋጫ እንዲመጣ ያልተጉት ፖለቲከኞችን  ጨምሮ በግል የእኔ፣ ያንተ፣ ያንችም የሁላችንም ተጠቂዎች ናቸው! በጅዳ ቆንስልና በሪያ ኢምባሲ በር የሚጣሉ ወገኖች … ተጠቂዎች ናቸው!

ቸር ያሰማን ስል ለብላቴናው መሀመድ እናት ለእናት ሀሊማ የምታደርጉትን እርዳታ እንዳትረሱ በማስታወስ ነው! የመሀመድ ቤተሰብ ፍትህ እስኪያገኙ ከንፈር ከመምጠጥ ባለፈ የከበደውን አንግልትና ወጫቸው ለመሸፈን ቢገድ ለቤት ኪራይና ትራንስፖርት የቻልነውን በማድረግ መከራውን ልንጋራ ይገባል። አነሰ በዛ አትበሉ፣ ብርቱዋን እናት ሃሊማን ቢያንስ ለማረፊያና ለትራንስፖርት ለመርዳት ፈቃደኛ የሆናችሁ በስልክ ቁጥር 0505682531 ደውሉ ካላችሁበት ድረስ መጥቸ እርዳታውን እቀበላለሁ!

ሰላም!

ነቢዩ ሲራክ
ጥቅምት 20 ቀን 2008 ዓም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule