• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእኔ፣ ያንተ፣ የእናንተ፣ የእኛ ተጠቂዎች!

November 1, 2015 05:09 pm by Editor Leave a Comment

የብላቴናው መሀመድን እናት እርዳታ አድራጊ ወገኖቸ የቻልኩትን እርዳታ ለመሰብሰብ ወጣ ባልኩበት አጋጣሚ ስልክ ተደወለልኝ። አነሳሁት፣ ከሰላምታ በኋላ “ጠፋህ? የት ነው ያለህ?”  ከሚለው አጭር የተለመደ የሰላምታ ማጀቢያ በኋላ ወዳጀ ወደ መልዕክታቸው  ገቡ …

“አንተ ነብዩ የት ጠፋህ?” ሲሉ ደገሙና ስመለጥፋቴ ጠይቀውኝ ሲቀጥሉ “ናና አንድ እህት ከጅዳ ቆንስል በር ወድቃለች፣ ጸሀይ እየደበደበ አድክሟታል! እነሱ (የቆንስል ሰዎች ማለታቸው ነው) ቢነግሯቸው አይሰሙም። ሌላም ሶስት እህቶች ከቆንስሉ አጠገብ ካለው ንጉድ ፉአድ ሆስፒታል ያለ ጠያቂ ተኝተዋል። ጎብኟቸውና ችግራቸውን ተረዱ ወይ መፍትሄ ፈልጉ ወይ ወደ ሀገር  ስደዷቸው ብል የሚሰማ የለም! አንተን ከሰሙህ ናና እያቸው!” ብለው ቁጣ የተቀላቀለበት መልዕክት አስተላለፈውልኝ ተጣድፈው ስልኩን ዘጉት … ! የእኒህ ወንድም መረጃ ሲያቀብሉኝ በስጨት ማለት ምክንያቱ ገብቶኛልና አልተከፋሁም፣ ይልቁንም ስለሰጡኝ መረጃ አመሰገንኳቸው። …

አሁን አሁን በኮንትራት መጥተው ጠፍተው ሲሰሩ የነበሩት፣ በባህርም ሆነ በቀድሞው ሃጅና ኡምራ  መጥተው በአሰሪዎቻቸው መደፈር መደብደብን ጨምሮ ፈርጀ ብዙ በሆነ ምክንያት  የተለያየ ጥቃትም ሆነ ህመም ሲያጠቃቸው መጥተው የሚወድቁት በዚሁ በጅዳ ቆንሰል በር ነው። ለምን ቢባል ዘንድሮ  ህጋዊ መኖሪያ ፍቃድ የሌላቸውን ማስጠጋት አደጋ አለውና ነው፣ አደጋው ደግሞ ቤተሰብን ጠቅልሎ ከሀገር መባረር ነውና ያስፈራል። ይህ የከፋ ችግር የተጋረጠበት የጨነቀው ነዋሪ እየፈራ እየተባ ያስጠጋው ነዋሪ ወደ ሀገር ይገባ ዘንድ ከቆንሰል መስሪያ ቤቱ ጋር ሞግቶ አልሳካለት ሲል ከቀጣዩ አደጋ ራሱን ለመከላከል የስጋ ዘመዱን ሳይቀር በጠራራው ጸሀይ ጨክኖ አምጥቶ የሚጥለው በቆንስሉ በር ላይ ነው!eth

ያን ሰሞን አንድ ወዳጀ “በቆንስሉ በር የወደቀች ልጅ አለች እያት ታሳዝናለች!” የሚል መረጃ አደረሰኝና ወደ ዚያው አቀናሁ፣ ሙቀት ያደከማት፣ ውሃ ጥም ያደረቃትን እህት አገኘኋት፣ ከመኪናየ ውስጥ የነበረውን ውሃ ስሰጣት ተንሰፍስፋ ስትጠታው የተሰማኝን ህመም ሳስበው እታመማለሁ … ልጅቱ በዥጉርጉሩ ፎቴ ተዘርራ የምታዮዋትን ናት፣ ውሃው ድካሟን አልመለሰውም፣ ተንፈስ ማለት ችላለች … ያም ቢሆን የዋለባት ሙቀቱ አድክሟት ያዝ ለቀቅ እያደረገች ያጫወተችኝ የቅርብ ዘመዶችዋ በቆንስል መስሪያ ቤቱ በኩል ወደ ሀገር የመጓጓዣ ሰነድ አውጥተው ለመስደድ ሞክረው አልሆን ሲላቸው አምጥተው እንደጣሏት ነበር  … ስሜቴ በጣሙን ተነክቶ ወደ አምባሳደር ውብሸት በላኩት መልዕክት ቦታውን ሳልለቅ ወደ መጠለያው ለመግባት ፈቃድ በማግኘቷ ቆንስሉ ልትሞት የነበረቸውን እህትን የታደጋትን ያህል ተደሰትኩ …

ዛሬ ከሰዓታት በፊት ያየኋት እህት በጠራራው ጸሃይ በቆንስሉ በር ተዘርራ ተኝታ ነበር፣ አትሰማም አትናገር ። ብዙዎቻችን ከንፈራችን እየመጠጥን ስናልፋት በመኪና የሚተላለፉት አረቦች ሲያዩዋት መኪናቸውን አቁመው “ለምን ወደ ግቢ  አታስገቧትም? ለምን አንቡላንስ አትጠሩም?” እያለ እያዘኑ “ፈጣሪ ይድረስልሽ ፣ ምስኪን!” እያሉ  ይሄዳሉ … እያየን ወደ ሀላፊዎች ስልክ ደውለን ለማሳወቅ እንኳ “ተቃዋሚ ምንቴስ ” እንባላለን ብለን ከምንፈራው ብዙዎች የተሻሉ የምላቸው የሳውዲ መንግስት የቆንስሉ ጠባቂዎች ደጋግመው ወደ ቀይ ጨረቃ ደውለው አምቡላንስ አልመጣ ቢልም ጉዳዩን ወደ አንድ ጉምቱ ባለስልጣን በመድረሱ አምቡላንሱ ፈጥኖ ሳይመጣ አይቀርም! እኔም እንደ አልፎ ሂያጁ አረብ “ምስኪን! ፈጣሪ ይድረስልሽ!” ከማለት ውጭ የምለው የለም… !

እኛ ቅንጡዎች “ራሳችን፣ ሆድ እቃ፣ እግር እጅ፣ አይናችን አመመን!” ብለን አገር ይያዝ ብለን በምንቀውጥበት ሰማይ ስር ያየሁት የማይታመን አይደለም፣ ይህችና ይህችን መሰል እህቶች በሀገራችን የመንግስት ተወካይ፣ የማህበረሰብና የፖለቲካ ድርጅት ተወካዮችና የደላ የሞላልን ሳይሆን ሳይደላን በሽፍንፍን ህይዎት አሸሸ ገዳሜ በምንልበት አዳራሽና ቆንስል በር በተደጋጋሚ ይጣላሉ፣ ያለላቸው ተርፈው ያላለላቸው “ሰርታ ታሻሽለኛለች!” ብሎ ለላከላቸው ወላጅ የህይዎት እንቆቅልሽ ይሆኑ ዘንድ  ማንነታቸው ሳይታወቅ ወደ ማይቀረው አለም ይሸኛሉ (… የሳውዲ መንግስት በነጻ የሚሰጠው  ህክምና አይደለም ቀዝቃዛ ውሃ ናፍቋቸው፣ ይህችን አለም ሲሰናበቱ ማየት በእርግጥ ያማል … (ይህን አይቶ ዝም ማለቱም ለእኔ ሌላ እዳ ነውና ያማችሁ ዘንድ ብቻ ሳይሆን የሚመለከታቸው መፍትሄ ይፈልጉለት ዘንድ እነግራችኋለሁ!

ደረቁ እውነት ይህ ነው … እኒህ በየሜዳው ተጥለው የሚጠፉት እህቶች ከወላጅ ጀምሮ፣ የመንግስት፣ የነዋሪው፣  የማህበረሰብ ተወካዮች፣ ይህ መከራ መቋጫ እንዲመጣ ያልተጉት ፖለቲከኞችን  ጨምሮ በግል የእኔ፣ ያንተ፣ ያንችም የሁላችንም ተጠቂዎች ናቸው! በጅዳ ቆንስልና በሪያ ኢምባሲ በር የሚጣሉ ወገኖች … ተጠቂዎች ናቸው!

ቸር ያሰማን ስል ለብላቴናው መሀመድ እናት ለእናት ሀሊማ የምታደርጉትን እርዳታ እንዳትረሱ በማስታወስ ነው! የመሀመድ ቤተሰብ ፍትህ እስኪያገኙ ከንፈር ከመምጠጥ ባለፈ የከበደውን አንግልትና ወጫቸው ለመሸፈን ቢገድ ለቤት ኪራይና ትራንስፖርት የቻልነውን በማድረግ መከራውን ልንጋራ ይገባል። አነሰ በዛ አትበሉ፣ ብርቱዋን እናት ሃሊማን ቢያንስ ለማረፊያና ለትራንስፖርት ለመርዳት ፈቃደኛ የሆናችሁ በስልክ ቁጥር 0505682531 ደውሉ ካላችሁበት ድረስ መጥቸ እርዳታውን እቀበላለሁ!

ሰላም!

ነቢዩ ሲራክ
ጥቅምት 20 ቀን 2008 ዓም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule