• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእኔ፣ ያንተ፣ የእናንተ፣ የእኛ ተጠቂዎች!

November 1, 2015 05:09 pm by Editor Leave a Comment

የብላቴናው መሀመድን እናት እርዳታ አድራጊ ወገኖቸ የቻልኩትን እርዳታ ለመሰብሰብ ወጣ ባልኩበት አጋጣሚ ስልክ ተደወለልኝ። አነሳሁት፣ ከሰላምታ በኋላ “ጠፋህ? የት ነው ያለህ?”  ከሚለው አጭር የተለመደ የሰላምታ ማጀቢያ በኋላ ወዳጀ ወደ መልዕክታቸው  ገቡ …

“አንተ ነብዩ የት ጠፋህ?” ሲሉ ደገሙና ስመለጥፋቴ ጠይቀውኝ ሲቀጥሉ “ናና አንድ እህት ከጅዳ ቆንስል በር ወድቃለች፣ ጸሀይ እየደበደበ አድክሟታል! እነሱ (የቆንስል ሰዎች ማለታቸው ነው) ቢነግሯቸው አይሰሙም። ሌላም ሶስት እህቶች ከቆንስሉ አጠገብ ካለው ንጉድ ፉአድ ሆስፒታል ያለ ጠያቂ ተኝተዋል። ጎብኟቸውና ችግራቸውን ተረዱ ወይ መፍትሄ ፈልጉ ወይ ወደ ሀገር  ስደዷቸው ብል የሚሰማ የለም! አንተን ከሰሙህ ናና እያቸው!” ብለው ቁጣ የተቀላቀለበት መልዕክት አስተላለፈውልኝ ተጣድፈው ስልኩን ዘጉት … ! የእኒህ ወንድም መረጃ ሲያቀብሉኝ በስጨት ማለት ምክንያቱ ገብቶኛልና አልተከፋሁም፣ ይልቁንም ስለሰጡኝ መረጃ አመሰገንኳቸው። …

አሁን አሁን በኮንትራት መጥተው ጠፍተው ሲሰሩ የነበሩት፣ በባህርም ሆነ በቀድሞው ሃጅና ኡምራ  መጥተው በአሰሪዎቻቸው መደፈር መደብደብን ጨምሮ ፈርጀ ብዙ በሆነ ምክንያት  የተለያየ ጥቃትም ሆነ ህመም ሲያጠቃቸው መጥተው የሚወድቁት በዚሁ በጅዳ ቆንሰል በር ነው። ለምን ቢባል ዘንድሮ  ህጋዊ መኖሪያ ፍቃድ የሌላቸውን ማስጠጋት አደጋ አለውና ነው፣ አደጋው ደግሞ ቤተሰብን ጠቅልሎ ከሀገር መባረር ነውና ያስፈራል። ይህ የከፋ ችግር የተጋረጠበት የጨነቀው ነዋሪ እየፈራ እየተባ ያስጠጋው ነዋሪ ወደ ሀገር ይገባ ዘንድ ከቆንሰል መስሪያ ቤቱ ጋር ሞግቶ አልሳካለት ሲል ከቀጣዩ አደጋ ራሱን ለመከላከል የስጋ ዘመዱን ሳይቀር በጠራራው ጸሀይ ጨክኖ አምጥቶ የሚጥለው በቆንስሉ በር ላይ ነው!eth

ያን ሰሞን አንድ ወዳጀ “በቆንስሉ በር የወደቀች ልጅ አለች እያት ታሳዝናለች!” የሚል መረጃ አደረሰኝና ወደ ዚያው አቀናሁ፣ ሙቀት ያደከማት፣ ውሃ ጥም ያደረቃትን እህት አገኘኋት፣ ከመኪናየ ውስጥ የነበረውን ውሃ ስሰጣት ተንሰፍስፋ ስትጠታው የተሰማኝን ህመም ሳስበው እታመማለሁ … ልጅቱ በዥጉርጉሩ ፎቴ ተዘርራ የምታዮዋትን ናት፣ ውሃው ድካሟን አልመለሰውም፣ ተንፈስ ማለት ችላለች … ያም ቢሆን የዋለባት ሙቀቱ አድክሟት ያዝ ለቀቅ እያደረገች ያጫወተችኝ የቅርብ ዘመዶችዋ በቆንስል መስሪያ ቤቱ በኩል ወደ ሀገር የመጓጓዣ ሰነድ አውጥተው ለመስደድ ሞክረው አልሆን ሲላቸው አምጥተው እንደጣሏት ነበር  … ስሜቴ በጣሙን ተነክቶ ወደ አምባሳደር ውብሸት በላኩት መልዕክት ቦታውን ሳልለቅ ወደ መጠለያው ለመግባት ፈቃድ በማግኘቷ ቆንስሉ ልትሞት የነበረቸውን እህትን የታደጋትን ያህል ተደሰትኩ …

ዛሬ ከሰዓታት በፊት ያየኋት እህት በጠራራው ጸሃይ በቆንስሉ በር ተዘርራ ተኝታ ነበር፣ አትሰማም አትናገር ። ብዙዎቻችን ከንፈራችን እየመጠጥን ስናልፋት በመኪና የሚተላለፉት አረቦች ሲያዩዋት መኪናቸውን አቁመው “ለምን ወደ ግቢ  አታስገቧትም? ለምን አንቡላንስ አትጠሩም?” እያለ እያዘኑ “ፈጣሪ ይድረስልሽ ፣ ምስኪን!” እያሉ  ይሄዳሉ … እያየን ወደ ሀላፊዎች ስልክ ደውለን ለማሳወቅ እንኳ “ተቃዋሚ ምንቴስ ” እንባላለን ብለን ከምንፈራው ብዙዎች የተሻሉ የምላቸው የሳውዲ መንግስት የቆንስሉ ጠባቂዎች ደጋግመው ወደ ቀይ ጨረቃ ደውለው አምቡላንስ አልመጣ ቢልም ጉዳዩን ወደ አንድ ጉምቱ ባለስልጣን በመድረሱ አምቡላንሱ ፈጥኖ ሳይመጣ አይቀርም! እኔም እንደ አልፎ ሂያጁ አረብ “ምስኪን! ፈጣሪ ይድረስልሽ!” ከማለት ውጭ የምለው የለም… !

እኛ ቅንጡዎች “ራሳችን፣ ሆድ እቃ፣ እግር እጅ፣ አይናችን አመመን!” ብለን አገር ይያዝ ብለን በምንቀውጥበት ሰማይ ስር ያየሁት የማይታመን አይደለም፣ ይህችና ይህችን መሰል እህቶች በሀገራችን የመንግስት ተወካይ፣ የማህበረሰብና የፖለቲካ ድርጅት ተወካዮችና የደላ የሞላልን ሳይሆን ሳይደላን በሽፍንፍን ህይዎት አሸሸ ገዳሜ በምንልበት አዳራሽና ቆንስል በር በተደጋጋሚ ይጣላሉ፣ ያለላቸው ተርፈው ያላለላቸው “ሰርታ ታሻሽለኛለች!” ብሎ ለላከላቸው ወላጅ የህይዎት እንቆቅልሽ ይሆኑ ዘንድ  ማንነታቸው ሳይታወቅ ወደ ማይቀረው አለም ይሸኛሉ (… የሳውዲ መንግስት በነጻ የሚሰጠው  ህክምና አይደለም ቀዝቃዛ ውሃ ናፍቋቸው፣ ይህችን አለም ሲሰናበቱ ማየት በእርግጥ ያማል … (ይህን አይቶ ዝም ማለቱም ለእኔ ሌላ እዳ ነውና ያማችሁ ዘንድ ብቻ ሳይሆን የሚመለከታቸው መፍትሄ ይፈልጉለት ዘንድ እነግራችኋለሁ!

ደረቁ እውነት ይህ ነው … እኒህ በየሜዳው ተጥለው የሚጠፉት እህቶች ከወላጅ ጀምሮ፣ የመንግስት፣ የነዋሪው፣  የማህበረሰብ ተወካዮች፣ ይህ መከራ መቋጫ እንዲመጣ ያልተጉት ፖለቲከኞችን  ጨምሮ በግል የእኔ፣ ያንተ፣ ያንችም የሁላችንም ተጠቂዎች ናቸው! በጅዳ ቆንስልና በሪያ ኢምባሲ በር የሚጣሉ ወገኖች … ተጠቂዎች ናቸው!

ቸር ያሰማን ስል ለብላቴናው መሀመድ እናት ለእናት ሀሊማ የምታደርጉትን እርዳታ እንዳትረሱ በማስታወስ ነው! የመሀመድ ቤተሰብ ፍትህ እስኪያገኙ ከንፈር ከመምጠጥ ባለፈ የከበደውን አንግልትና ወጫቸው ለመሸፈን ቢገድ ለቤት ኪራይና ትራንስፖርት የቻልነውን በማድረግ መከራውን ልንጋራ ይገባል። አነሰ በዛ አትበሉ፣ ብርቱዋን እናት ሃሊማን ቢያንስ ለማረፊያና ለትራንስፖርት ለመርዳት ፈቃደኛ የሆናችሁ በስልክ ቁጥር 0505682531 ደውሉ ካላችሁበት ድረስ መጥቸ እርዳታውን እቀበላለሁ!

ሰላም!

ነቢዩ ሲራክ
ጥቅምት 20 ቀን 2008 ዓም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule