• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እስራኤል ተጨማሪ ታዳጊዎች ለቀቀች

January 11, 2013 07:54 am by Editor 2 Comments

በእስራኤል አገር ታስረው ከሚገኙት ታዳጊዎች መካከል አራቱ መፈታታቸውን አቶ ሳሙኤል አለባቸው የኢትዮጵያ እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል ሊቀመንበር በተለይ ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ አስታውቀዋል። አሁንም እስር ላይ የሚገኙት ዕድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ አስር ታዳጊዎችን ለማስፈታት አስፈላጊው ሁሉ እየተደረገ መሆኑንንም አስታውቀዋል።

አቶ ሳሙኤል በጽሁፍ በላኩት መልዕክት እንዳስታወቁት ከጎንደር አስኮብላዮች ወደ ሲና በረሃ በመውሰድ ለከፍተኛ እንግልትና ህሊናን የሚፈታተን ስቃይ ከዳረጓቸው ታዳጊዎች መካከል እስራኤል መድረስ የቻሉት እዚያ ሲደርሱ የገጠማቸው እስር ነበር። በተለይም እድሜያቸው ከአስራስምንት ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች በእስር ላይ እንደሚገኙ ከታወቀ በኋላ እርሳቸው የሚመሩት ድርጅትና የወገኖቻቸው ስቃይ እረፍት የነሳቸው አገር ወዳዶች ባደረጉት ትብብር ቀደም ሲል ስድስት ታዳጊዎች ከእስር ተለቅቀው ነበር።

ተጨማሪ አራት ታዳጊዎች መፈታታቸውን ያስታወቁት አቶ ሳሙኤል፣ ቀደም ሲል ከእስር ከተለቀቁት ስድስት ታዳጊዎች ጋር በመሆን በ29/12/2012 የመጀመሪያውን ሰንበት (ቅዳሜ) ከወገኖቻቸው ጋር በጋር ለማሳለፍ ችለዋል። በማያያዝም በእስር ላይ የሚገኙ አስር የሚደርሱ ታዳጊዎች በተመለከተ “… ከእስር ቤት እንደሚገኙ የተነገሩን እድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑና ቁጥራቸው ከአስር የማያንሱ ታዳጊዎች በተመለከተ ከእስር የሚፈቱበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ተገቢው ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።

የሲና በረሃን በሚያቋርጡበት ወቅት የሰውነት ክፍላቸውን በመዘረፍ፣ በመደፈር፣ በድብደባና አሰቃቂ ስቃይ በኋላ ከሞት ተርፈው እስራኤል የገቡት ወገኖች ለእስር መዳረጋቸው፣ በበረሃ ውስጥ የታሰሩበት ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑና በታሰሩበት የሚደረግላቸው እንክብካቤ አስመልክቶ መረጃው ይፋ መሆኑን ተከትሎ ጉዳዩ ዓለም አቀፍ ይዘት እንዲይዝ በማድረግ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዝ ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል።

በ11/01/2013 ዓም አቶ ሳሙኤል አለባቸው የሚመሩት ድርጅት ይፋ ያደረጋቸው ታዳጊዎች ስም ዝርዝር በእድሜና በትውልድ ስፍራ በመለየት ከዚህ እንደሚከተለው  ቀርቧል።

ቀደም ሲል ኮሚቴው ያገኛቸው

ተቁ

ስም

እድሜ

የመጣችበት ክ/ሀገርና ልዩ ቦታ

መግለጫ

1

ዘርፌ ጌዴ እንደሻው

14

ጎንደር /ደባርቅ/

2

ለቄ ደጀን መለሰ

15

ጎንደር /ደባርቅ/

3

ባንቺ ባዜ በላይ

15

ጎንደር /ማክሰኝት ወረዳ/

ልዩ ለፍሬው ባህር ግንብ

4

ወደር ገብሬ ጫኔ

16

ጎንደር /ባሪ ግንድ/

5

ገበያነሽ ተስፋ አማረ

14

ጎንደር /ማክሰኝት ወረዳ/

ልዩ ቦታ 50 ፍጭ

6

አለምወርቅ ሲሳይ የኔነህ

14

ጎንደር /አጅሬ/

ቀሪዎቹ 4 ታዳጊዎች ማለትም በሁለተኛው ዙር ፍለጋ የተገኙና መረጃቸው ተሟልቶ የተላከ የሚከተሉት ናቸው።

ተቁ

ስም

እድሜ

የመጣችበት ክ/ሀገርና ልዩ ቦታ

መግለጫ

7

ሸዋዬ ሹመት አድባያቸው

15

ደባርቅ

8

ድንቄ መብራት አድባያቸው

14

ደባርቅ

9

ወርቅዬ ማሞ ጌጤ

14

ደባርቅ

10

ስለእናት ጥላዬ ቦጋለ

16

ደባርቅ

(ፎቶ: አቶ ሳሙኤል አለባቸው አድማሱ የኢትዮጵያ እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል ሊቀመንበር)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfay fetewi says

    July 9, 2013 06:40 pm at 6:40 pm

    Brother Samuel I have been following your meeting in Israel, but I am really shocked by your statement, as you blamed, meles Zenawi for sailing Eritrea that is totally wrong just you privileged him which he did not deserve and by saying that you disrespected the brave over 400000 fallen Ethiopian soldiers who fought selflessly for their flag in Eritrea .Those who “sold Eritrea” are those who run Eritrean before Meles but either you are sided or know nothing . We Eritrean did not get our freedom as gift coupons from any one it is the result of hard and long fighting it is well known that we paid for our freedom highly price. However,what to the Amhra people happened is really sad but you wake up now but it happened to Eritrean exactly before 40 years and we got the nickname wenbede tegentay yareb kitrejna nevertheless It was not a willing of Meles or Isyas Afewerq that Eritrea is apart from Ethiopia, but the democratically freely decision of Eritrean people 98,9% and this was happening under the monitoring of the entire world if you stand for democracy human right you should aware of it!!!…the old slogan “eritrea mertwa enji sewa anflgm”” people assumed Eritrean soil but no Eritrean people, but how could this work?? How can you have Eritrea asab if the Eritrean people do not accept you???. Should we expect another war, if you being a leader of Ethiopia?? Wendme Alebachew , brother let me tell you!!you are young we live in 2013 a globalization, forget the song of hate and war just try to talk for peace mutual respect “Peace is a journey of a thousand miles and it must be taken one step at a time” if peace is occurred the border would disappear within and your dream could be realize and you can have Assab, you I will spend you a villa in DAHLAk in the middle of the sea…. We had wars for 60 years …there was no winner but ONLY looser!!! I was fighter I know what war is so be smart we are habesha and we should make peace among us ….thank you

    Reply
  2. Desalegne says

    November 3, 2013 05:57 pm at 5:57 pm

    Iam have been given god’s will and opportunity to witness the works and struggles of that a true warrior for peace and equality for ethiopian people such as Mr. Samuel Alenachew. Iam a person of ethiopian origin who left ethiopia at beginning of Mengistu’s reign. At age ten I fought to bring democracy to ethiopia, but we failed to accomplish that. That was because we did not have people who care for our country like. Mr. Samuel I grantee you today if we have ten people like you, the fascist junta will be out of its misery. Ask The Italians, only a hand-full Ethiopians started the struggle to eliminate unjust occupation of ethiopia by Italy.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule