• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እስራኤል ተጨማሪ ታዳጊዎች ለቀቀች

January 11, 2013 07:54 am by Editor 2 Comments

በእስራኤል አገር ታስረው ከሚገኙት ታዳጊዎች መካከል አራቱ መፈታታቸውን አቶ ሳሙኤል አለባቸው የኢትዮጵያ እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል ሊቀመንበር በተለይ ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ አስታውቀዋል። አሁንም እስር ላይ የሚገኙት ዕድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ አስር ታዳጊዎችን ለማስፈታት አስፈላጊው ሁሉ እየተደረገ መሆኑንንም አስታውቀዋል።

አቶ ሳሙኤል በጽሁፍ በላኩት መልዕክት እንዳስታወቁት ከጎንደር አስኮብላዮች ወደ ሲና በረሃ በመውሰድ ለከፍተኛ እንግልትና ህሊናን የሚፈታተን ስቃይ ከዳረጓቸው ታዳጊዎች መካከል እስራኤል መድረስ የቻሉት እዚያ ሲደርሱ የገጠማቸው እስር ነበር። በተለይም እድሜያቸው ከአስራስምንት ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች በእስር ላይ እንደሚገኙ ከታወቀ በኋላ እርሳቸው የሚመሩት ድርጅትና የወገኖቻቸው ስቃይ እረፍት የነሳቸው አገር ወዳዶች ባደረጉት ትብብር ቀደም ሲል ስድስት ታዳጊዎች ከእስር ተለቅቀው ነበር።

ተጨማሪ አራት ታዳጊዎች መፈታታቸውን ያስታወቁት አቶ ሳሙኤል፣ ቀደም ሲል ከእስር ከተለቀቁት ስድስት ታዳጊዎች ጋር በመሆን በ29/12/2012 የመጀመሪያውን ሰንበት (ቅዳሜ) ከወገኖቻቸው ጋር በጋር ለማሳለፍ ችለዋል። በማያያዝም በእስር ላይ የሚገኙ አስር የሚደርሱ ታዳጊዎች በተመለከተ “… ከእስር ቤት እንደሚገኙ የተነገሩን እድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑና ቁጥራቸው ከአስር የማያንሱ ታዳጊዎች በተመለከተ ከእስር የሚፈቱበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ተገቢው ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።

የሲና በረሃን በሚያቋርጡበት ወቅት የሰውነት ክፍላቸውን በመዘረፍ፣ በመደፈር፣ በድብደባና አሰቃቂ ስቃይ በኋላ ከሞት ተርፈው እስራኤል የገቡት ወገኖች ለእስር መዳረጋቸው፣ በበረሃ ውስጥ የታሰሩበት ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑና በታሰሩበት የሚደረግላቸው እንክብካቤ አስመልክቶ መረጃው ይፋ መሆኑን ተከትሎ ጉዳዩ ዓለም አቀፍ ይዘት እንዲይዝ በማድረግ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዝ ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል።

በ11/01/2013 ዓም አቶ ሳሙኤል አለባቸው የሚመሩት ድርጅት ይፋ ያደረጋቸው ታዳጊዎች ስም ዝርዝር በእድሜና በትውልድ ስፍራ በመለየት ከዚህ እንደሚከተለው  ቀርቧል።

ቀደም ሲል ኮሚቴው ያገኛቸው

ተቁ

ስም

እድሜ

የመጣችበት ክ/ሀገርና ልዩ ቦታ

መግለጫ

1

ዘርፌ ጌዴ እንደሻው

14

ጎንደር /ደባርቅ/

2

ለቄ ደጀን መለሰ

15

ጎንደር /ደባርቅ/

3

ባንቺ ባዜ በላይ

15

ጎንደር /ማክሰኝት ወረዳ/

ልዩ ለፍሬው ባህር ግንብ

4

ወደር ገብሬ ጫኔ

16

ጎንደር /ባሪ ግንድ/

5

ገበያነሽ ተስፋ አማረ

14

ጎንደር /ማክሰኝት ወረዳ/

ልዩ ቦታ 50 ፍጭ

6

አለምወርቅ ሲሳይ የኔነህ

14

ጎንደር /አጅሬ/

ቀሪዎቹ 4 ታዳጊዎች ማለትም በሁለተኛው ዙር ፍለጋ የተገኙና መረጃቸው ተሟልቶ የተላከ የሚከተሉት ናቸው።

ተቁ

ስም

እድሜ

የመጣችበት ክ/ሀገርና ልዩ ቦታ

መግለጫ

7

ሸዋዬ ሹመት አድባያቸው

15

ደባርቅ

8

ድንቄ መብራት አድባያቸው

14

ደባርቅ

9

ወርቅዬ ማሞ ጌጤ

14

ደባርቅ

10

ስለእናት ጥላዬ ቦጋለ

16

ደባርቅ

(ፎቶ: አቶ ሳሙኤል አለባቸው አድማሱ የኢትዮጵያ እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል ሊቀመንበር)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfay fetewi says

    July 9, 2013 06:40 pm at 6:40 pm

    Brother Samuel I have been following your meeting in Israel, but I am really shocked by your statement, as you blamed, meles Zenawi for sailing Eritrea that is totally wrong just you privileged him which he did not deserve and by saying that you disrespected the brave over 400000 fallen Ethiopian soldiers who fought selflessly for their flag in Eritrea .Those who “sold Eritrea” are those who run Eritrean before Meles but either you are sided or know nothing . We Eritrean did not get our freedom as gift coupons from any one it is the result of hard and long fighting it is well known that we paid for our freedom highly price. However,what to the Amhra people happened is really sad but you wake up now but it happened to Eritrean exactly before 40 years and we got the nickname wenbede tegentay yareb kitrejna nevertheless It was not a willing of Meles or Isyas Afewerq that Eritrea is apart from Ethiopia, but the democratically freely decision of Eritrean people 98,9% and this was happening under the monitoring of the entire world if you stand for democracy human right you should aware of it!!!…the old slogan “eritrea mertwa enji sewa anflgm”” people assumed Eritrean soil but no Eritrean people, but how could this work?? How can you have Eritrea asab if the Eritrean people do not accept you???. Should we expect another war, if you being a leader of Ethiopia?? Wendme Alebachew , brother let me tell you!!you are young we live in 2013 a globalization, forget the song of hate and war just try to talk for peace mutual respect “Peace is a journey of a thousand miles and it must be taken one step at a time” if peace is occurred the border would disappear within and your dream could be realize and you can have Assab, you I will spend you a villa in DAHLAk in the middle of the sea…. We had wars for 60 years …there was no winner but ONLY looser!!! I was fighter I know what war is so be smart we are habesha and we should make peace among us ….thank you

    Reply
  2. Desalegne says

    November 3, 2013 05:57 pm at 5:57 pm

    Iam have been given god’s will and opportunity to witness the works and struggles of that a true warrior for peace and equality for ethiopian people such as Mr. Samuel Alenachew. Iam a person of ethiopian origin who left ethiopia at beginning of Mengistu’s reign. At age ten I fought to bring democracy to ethiopia, but we failed to accomplish that. That was because we did not have people who care for our country like. Mr. Samuel I grantee you today if we have ten people like you, the fascist junta will be out of its misery. Ask The Italians, only a hand-full Ethiopians started the struggle to eliminate unjust occupation of ethiopia by Italy.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule