• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከኢትዮጵያ ስለመጣችሁ ታሰራችሁ”

December 17, 2012 09:02 am by Editor 1 Comment

አገር ቤት ያሉትን ወገኖች ለጊዜው መታደግ ካልተቻለ ቢያንስ ከማንም ተጽዕኖ ወጪ በስደት የሚኖሩትን ኢትዮጵያዊያኖች ለመርዳት ለሚቀርብ ጥያቄ የሚሰጠው ምላሽ የሚያሳዝን እንደሆነ አቶ ሳሙኤል አለባቸው በእስራኤል የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማህበር ሊቀመንበር ገለጹ። አቶ ኦባንግ ሜቶን ማህበሩ በተለይ መጋበዙን አስታወቁ።

ከሚያሳዝን መከራ ተርፈው እስራኤል ከደረሱ በኋላ እስር ቤት እንዲቆዩ የተደረጉት ታዳጊዎች መፈታታቸውን አስመልክቶ መግለጫ ያሰራጩት አቶ ሳሙኤል በተለይ ለጎልጉል እንደተናገሩት “በተለያዩ አገራት መከራ እየተቀበሉ ያሉትን ወገኖች መታደግ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ተቋማትና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ጠቅሰው፣ በተግባር ግን ይህንን ማየት” እንዳልቻሉ ተናግረዋል።

አቶ ሳሙኤል አለባቸው

በእስራኤል እየደረሰ ያለውን የወገኖች ስቃይ አስመልክቶ ለቀረበ ጥሪ ምላሽ ለመስጠት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ግንባር ቀደም እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሳሙኤል “በየአገሩ የተበተኑ ወገኖች እንደሚሉት በእስራኤል ያሉ ኢትዮጵያዊያን በአቶ ኦባንግና በድርጅታቸው አኢጋን ላይ ታላቅ እምነት አላቸው” ብለዋል።

“አቶ ኦባንግን ብቻ ሳይሆን አብረዋቸው ለሚሰሩት ሁሉ ልዩ ክብርና ፍቅር እንዳለን የምንገልጸው ዝም ብለን አይደለም” ያሉት አቶ ሳሙኤል “በጠላት ላይ ትኩረት አድርጎ በህብረት ከመስራት ይልቅ እርስ በርስ በመጠላለፍና ባለመተማመን በሚፈጥሩት ውዝግብ ጊዜያቸውን ከሚያባክኑት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ይልቅ ኦባንግ የሚመሩት ድርጅት ውጤታማ ስራ ሲሰራ ይስተዋላል። ይህ እውነት በሁሉም ኢትዮጵያዊ ዘንድ በገሃድ የሚታወቅ ነው…” ሲሉ ተናግረዋል። ከህዝብ በቀረበ ጥያቄ አቶ ኦባንግ እስራኤል እንዲገኙ ጥሪ ማቅረባቸውንም አስታውቀዋል። ያስመዘገቡት ስኬት፣ የህይወት ተሞክሯቸውና ትምህርት ሰጪው ልምዳቸው፣ እንዲሁም የሚመሩት ድርጅት የገነባው ስም ለግብዣው ዋና ምክንያት መሆኑን አስታውቀዋል።

ለአንድ አገር ወዳድ የዜጎቹን ህይወት ከመታደግ በላይ ታላቅ ክብር የሚያሰጠው ጉዳይ እንደሌለ ያመለከቱት አቶ ሳሙኤል አድማሱ፣ “በህዝብ መወደድ እንዲሁ የሚገኝ ቀላልና ተራ ጉዳይ አይደለም። ቀናነትና መልካምነት እያደር በሁሉም ዜጎች ልብ ውስጥ የሚነደው በቀስታ ነው። ቀስ ብሎ የሚገነባ ክብር በቀላሉ አይናድም። ይህን የመሰለው ፍቅርና ክብር አቶ ኦባንግ ለሚመሩት ድርጅት አለን። ከተደረገው ነገር አንጻር ብዙ መናገር ቢገባኝም ለጊዜው ከዚህ በላይ የምለው የለም” ብለዋል፡፡

በተቃራኒው “አምላክ ይማርህ/ሽ የማይባልለት በሽታ ይዞናል። ብዙ ስራ አለብን። ብዙ ጉዳዮች ከፊታችን ተቀምጠዋል። አላማችን ኢትዮጵያ ናት ግን አንስማማም። ከመከራ፣ከግድያ፣ ከእስር፣ ልንማር አልቻልንም። ኢትዮጵያን ፊትለፊት በማሳየት ውስጥ ውስጡን ለግል ጥቅም የምንሰራ አለን። እንዲህ ያለው ድርጊት ሊያበቃ ይገባዋል” ብለዋል።

በእስር ላይ የነበሩት ታዳጊዎች ዛሬ ተፈተው ወደ ተለመደው የህይወት እንቅስቃሴ እንዲዛወሩ ኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል የተሳካ ስራ ለመስራቱ ታዳጊዎቹን በመጎብኘትና በማነጋገር ያሰራጨው በምስል የተደገፈ ምስክርነት ያረጋግጣል። (ክፍል አንድ እና ክፍል ሁለት እዚህ ላይ ይገኛል) አሁን ትልቁ ጥያቄ እስር ላይ ያሉትን ተጨማሪ ከ300 በላይ ሰዎች ከእስር የማስለቀቁ ተግባር ነው። እነዚህ ወገኖች ያሉበትን ሁኔታ ለመመልከትና ከአገሪቱ ባለስልጣናት ጋር ለመነጋገር አቶ ኦባንግ ሜቶ ወደ ስፍራው የማምራት እቅድ አላቸው። ማረጋገጫ እንዲሰጡ ለተጠየቁት “ስንቋቋም ለወገን ነው።የምንሰራውም ለወገኖቻችን ነው። በተደረገው ተደስተናል። ለወደፊቱም የምንችለውን እናደርጋለን። አሁንም ውጤቱን መግለጽ ባልችልም ስራዎች እየተሰሩ ነው። እስራኤል ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ቦታዎች” የሚል መልስ ሰጥተዋል። በእስራኤል ከ2500 እስከ 3000 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን ባልተሟላ የስደት ህይወት እንደሚገፉ ለማወቅ ተችሏል።

አቶ ሳሙኤል የሚመሩት ማህበር ይፋ ያደረገው በምስል የተደገፈ ቃለ ምልልስ በታዳጊዎቹ ውጫዊ አካል ላይ የደረሰ ጉዳት የሚታይበት ባይሆንም፤ ስራ እናስገባችኋለን በሚል አፍነው እንዴት እንደወሰዷቸውና ሲና በረሃ አስኪገቡ የደረሰባቸውን መከራ፣ ከዚያም በሲና በረሃ ቆይታቸው፣ እኒህ ህጻናት ይፋ ያላደረጉት ምን ደርሶባቸው ይሆን የሚል ጥያቄ ያስነሳል።

ቀደም ሲል ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ስለ ሲና በረሃ ባወጣው ዘገባ የአካል ክፍልን መሰረቅ፣ መደፈር፣ መሰቃትና ጉሮሮ ለማርጠብ እንኳን አረብኛ አለመናገራቸው ወገኖቻችንን እንዴት እንደሚጎዳቸው ጠቅሰን ነበር። በተመሳሳይ አሁን በተለቀቀው የቪዲዮ መረጃ “የታሰራችሁት ከኢትዮጵያ ስለመጣችሁ ነው” በማለት የእስራኤል ፖሊስ እንደገለጸላቸው የምትናገረዋ ታዳጊና ሌላዋ ጓደኛዋ የሚናገሩትን በጉልጉል ቲዩብ ይመልከቱ። ያቺ ስሟን የሰማናትና አካላዊ ግፍ የተፈጸመባት ታዳጊና ሌሎች ተበዳዮች ወደፊት ሰፊ ዘገባ ለማቅረብ እንሞክራለን።

የኢትዮጵያን እናድን በእስራኤል ማህበር ሊቀ መንበር አቶ ሳሙኤል አድማሱ በማህበሩ ስም ያሰራጩትና ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ በአድራሻ የላኩት ደብዳቤ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል።

ቀን 14/12/2012

የማያባራው የኢትዮጵያውያን ፈተና

ፍትህ ሰላም ዴሞክራሲ ስርአት የራቃት አገራችን ለብሔራዊ ዳር ድንበሯ መከበርና ለዜጎቿ የመኖር ዋስትና የሚሰጥ ወይም የሚታደግ መንግስት በማጣታችን የተነሳ በየጊዜው የሚገጥመን ሰቆቃ ማባሪያ አጥቶ ከዛሬው እለት ላይ ደርሰናል።

ይህ ዘገባ የሚያጠነጥነው ከጎንደር ክፍለ አገር በደላሎች አሳሳችነት ከደባርቅ፣ ከማክሰኝት፣ 50 ፍጭ እና አጅሬ ከተባሉ አካባቢዎች ወደ መተማ በመወሰድ ከመተማም ስራ እንሰጣችኋለን በሚሉ ግለሰቦች አማካኝነት እድሜያቸው ከ14 እስከ 16 የሆኑ ታዳጊዎችን በበረሃ ውስጥ ባዘጋጁት የመጠለያ ስፍራ ቀደም ሲል በተለያየ ጊዜ ያሰባሰቧቸውን 14 ወንዶችንና 46 ሴቶች ከሚገኙበት ቦታ በመውሰድ በጠቅላላው 60 ታጋቾችን ወደ ሲናይ በርሃ በማስተላለፍ “እስራኤል እንልካችኋለን ሰርታችሁ ገንዘብ ታገኛላችሁ” በማለትና ከዚያ በፊት ኢትዮጵያ ያሉ ቤተሰቦቻችሁን ስልክ ቁጥር አምጡ በማለት ወደ ኢትዮጵያ ስልክ በመደወል በእያንዳንዳቸው 60,000 /ስልሳ ሺህ የኢትዮጵያ ብር/ እስካልተከፈለ ድረስ እንደሚገሉን የሚያመለክት የማስገደጃ ትእዛዝ ለቤተሰቦቻችንን በመናገር የተጠየቀውን ገንዘብ ሊቀበሉ ችለዋል። ከዚያም የሲናን በረሃ በተሽከርካሪና በእግር በማቋረጥ ላይ እንዳለን ከመሐከላችን ከወሎ ክፍለ አገር ራያና ቆቦ ከሚባል ስፍራ የተሰደደች ሰሚራ ሲሳይ ወይም ቤተልሄም ሲሳይ እድሜዏ በ20ዎቹ መጀመሪያ ላይ የምትገኝ ወጣት መንገድ በሚመሩ ግለሰቦች በመደፈሯና በመደብደቧ የደረሰባት በደል ፅኑ ስለነበር ህይወቷ ሊያልፍ ችሏል። እኛም በእድሜያችን ልጆች በመሆናችንና አካባቢው ላይ ስርአተ ቀብሯን ለመፈፀም አቅም በማጣታችን ከሜዳ ላይ ጥለናት ልንሄድ ሲሉ ቃላቸውን ከመስጠታቸውም ባሻገር እነሱ ራሳቸውን በረሃ ላይ ታግተው ከቆዩባቸው ቀናትና በጉዞው ላይ ባሳለፉት 14 ቀናት ውስጥ ከመደብደባቸውም ባሻገር በቂ ምግብ የተነፈጉና ለመጠጥ ውሃ በሚጠይቁበት ጊዜ ከቤንዚን ወይም ከናፍጣ ጋር የተቀላቀለበት ስለነበር በጤናቸው ላይ ከፍተኛ የሆነ ችግር ገጥሟቸው ስለነበር ልንጠይቃቸው በሄድንበት ሰአት ገልፀውልናል።

እነዚህ በእድሜአቸው እጅግ በጣም አነስተኛ የሆኑ ታዳጊዎች ከአገራቸው የኑሮ ዋስትና በማጣታቸው በእግዚአብሔር ቸርነትና ከቤተሰቦቻቸው በተከፈለ 60000 ብር በሲናይ በረሀ ከሚፈፀም የተለያየ ወንጀሎች ተርፈው ወደ እስራኤል ብሔራዊ ድንበር በተሻገሩበት ወቅት በእስራኤል የጠረፍ ጠባቂ ፖሊሶች ተይዘው ለ1 ወር ከታሰሩ በኋላ በአገሪቱ መሀል አገር በሚገኝ ራምሌ በሚባል እስር ቤት በተጨማሪ 7 ወራት በጠቅላላው 8 ወራት ከቆዩ በኋላ ከእስር ተለቀው የእስራኤል መንግስት ባዘጋጀላቸው አዳሪ ት/ቤት መደበኛ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ።

ከአዳሪ ት/ቤት ተዘዋውረን እንደተመለከትነው ሞግዚታቸው ወ/ሮ ምካኤል አነጋግረን የልጆቹ ጤንነት በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ ቢሆንም ከመሀከላቸው ያለምወርቅ ሲሳይ የኔነህ የምትባል ታዳጊ ያለባትን የጥርስ ህመም በተመለከተ ተገቢው ተከታታይ ህክምና እየተደረገላት እንደሚገኝ ከመግለፃቸውም ባሻገር ተማሪዎቹ ከእስር እንደተፈቱ ለእያንዳንዳቸው 500 የእስራኤል ሼቅል ተሰጥቷቸው እለታዊ አስፈላጊ ነገር የተሟሉላቸው ሲሆን በቋሚነት በየወሩ ለእያንዳንዳቸው 150 ሼቅል የኪስ ገንዘብ እንደሚሰጣቸው ገልውልን መደበኛ ትምህርታቸውን በተመለከተ በሳምንት 5 ቀናት ከጠዋቱ 8 ሰአት እስከ ቀኑ 1፡30 እንደሚከታተሉና በትምህርት ቤት ቆይታቸው እድሜአቸው 18 አመት እስከሚሞላ መሆኑን ገልፀውልናል። ከ18 አመት በኋላ የታዳጊዎቹ እጣ ፋንታ ምን እደሚሆን አላወቅንም።

የእስራኤል መንግስት የእነዚህን ታዳጊዎች ህይወት በመታደግ ረገድ ላደረገው መልካም ትብብር በታዳጊዎቹ ስም ምስጋናችንን እያቀረብን እስራኤል አገር ታስረው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እስረኞችን በተመለከተ በመላው አለም ለሚገኙ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅቶች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ለችግራች የሚዲያ ሽፋን እንዲሰጡን ጥሪ አቅርበንላቸው ምላሽ ለሰጡን የድህረ ገፅ ባለቤቶች ምሥጋናችንን እያቀረብን በተለይ ለእስራኤል መንግስትና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የተለያዩ ክፍሎች በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የመብት ጥሰት በመግለፅ ኢትዮጵያውያን ታሳሪዎችን ከእስር ነፃ እንዲያደርጋቸው ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ሽግግርና ም/ቤትና ከአዲሲቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ለተፃፉ ደብዳቤዎችና ሁለገብ ድጋፎች በኢትዮጵያ አንድነት ማህበር ስም ምጋናችን ለማቅረብ እንወዳለን።

እነዚህን ታዳጊዎችና አሁን በእስር ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተመለከተ በመላው አለም የምትገኙ ታዋቂ ኢትዮጵያውያን ግለሰቦች የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት መሪዎች የሲቪክ ማህበራት የሀይማኖት መሪዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢሰብአዊ ድርጊት ለእስራኤል መንግስት በማሳዋቅ ረገድ የበኩላችሁን እገዛ ታደርጉልን ዘንድ በታሳሪዎቹ ከእስር ከተፈቱትና ቧልተሟላ የስደተኛ መብት በሚኖሩት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ስም የበኩላችሁን ድጋፍ እንድታደርጉ የኢትዮጵያ አንድነት ማህበር በእስራኤል ወገናዊ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ከእስር ከተፈቱት መሐከል

ተቁ ስም እድሜ የመጣችበት ክ/ሀገርና ልዩ ቦታ መግለጫ
1 ዘርፌ ጌዴ እንደሻው 14 ጎንደር /ደባርቅ/
2 ለቄ ደጀን መለሰ 15 ጎንደር /ደባርቅ/
3 ባንቺ ባዜ በላይ 15 ጎንደር /ማክሰኝት ወረዳ/ ልዩ ለፍሬው ባህር ግንብ
4 ወደር ገብሬ ጫኔ 16 ጎንደር /ባሪ ግንድ/
5 ገበያነሽ ተስፋ አማረ 14 ጎንደር /ማክሰኝት ወረዳ/ ልዩ ቦታ 50 ፍጭ
6 አለምወርቅ ሲሳይ የኔነህ 14 ጎንደር /አጅሬ/

ከዱሪም ከሚባል ስፍራ የእርሻና የወጣቶች መንደር ታዳጊዎቹን በአንድ አዳሪ ት/ቤት አግኝተን ተገቢውን መሰረታዊ ቁሳቁስ እርዳታ ልናደርግላቸው ችለናል። ቀሪዎቹ 4 ታዳጊዎች ማለትም

ተቁ ስም እድሜ የመጣችበት ክ/ሀገርና ልዩ ቦታ መግለጫ
1 ሸዋዬ ሹመት
2 ድንቄ መብራት
3 ወርቅዬ ማሞ
4 ስለእናት ጥላዬ

የተባሉት ከእስር የተለቀቁ ሲሆን የተመደቡበትን አዳሪ ት/ቤት አድራሻ በትክክል እንዳወቅን በተመሳሳይ መልኩ ተገቢውን የአልባሳት ስጦታና ሌሎች መሰረታዊ የሆኑ መጠቀሚያዎችን ለማዳረስ ቅድመ ዝግጅት ያደረግን ሲሆን በዚህ የእርዳታ ማሰባሰብ ስራ ላይ ከማህበሩ አባላት በተጨማሪ የእስራኤል የአካባቢ ም/ቤት አባላትና ሌሎች ግለሰቦችም የበኩላቸውን አስተዋፅኦ አበርክተዋል።

በአጠቃላይ በረሀ ከነበሩት 60 ታጋቾች እስካሁን በህይወት ያገኘናቸው አስር ያህሉን ሲሆን የተቀሩት 50 ኢትዮጵያውያን እጣ ፋንታ ምን እንደሆነ እስካሁን አልታወቀም።

ከእስር የተፈቱት ታዳጊዎች የመደበኛ ትምህርት በተመለከተ ከ3ኛ ክፍል እስከ 6ኛ ክፍል በአገር ቤት የተማሩ ሲሆን አንዷ ግን ምንም አይነት የትምህርት እድል እንዳላገኘች ለማወቅ ችለናል፡፡

የሁሉም አስተያየት ተመሳሳይ ሲሆን ስራ ፍለጋ እንደተሰደዱና የቤተሰቦቻቸው አቅም በሐብት ያልደረጁ በመሆናቸው ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት ከነበራቸው ፍላጎት የተነሳ መሰደዳቸውን ገልፀዋል።

በአንፃሩም በበረሀና በእስር ቤት ያሳለፉትን ስቃይ በማሰብ ሌሎች ወገኖቻችን ስደትን የመፍትሔ አማራጭ አድርገው እንዳይወስዱ የበኩላቸውን አስተያየት በመስጠት የቆይታ ጊዜያችንን በዚህ መልክ ያጠናቀቅን ቢሆንም አሁንም የነዚህን ታዳጊዎች የወደፊት እድል በተመለከተ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊተባበራቸውና አቅሙ በፈቀደ ሁሉ ይረዳቸው ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ከሰላምታ ጋር

ሳሙኤል አለባቸው አድማሱ

የኢትዮጵያ እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል ሊቀመንበር

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Fedlu says

    December 17, 2012 12:17 pm at 12:17 pm

    Ethiopiawi kibrun ata tesekayen…yesew fit gerefen min yishalal?wetatu bechatina beshisha denziual ke eskindirena keandualem yilek sile runey new miawkew ebakih yehagere wetat nika….nika….wegen tesedo 1tiwelid bado lihon new

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule