• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች

October 10, 2023 09:07 am by Editor Leave a Comment

“አቋጥሬ አይጫረሰ ነው” አሉ አንድ አዛውንት መላው እንደጠፋቸው በመግለጽ። “አቋጥሬ ምንድን ነው?” ሲባሉ፣ በአጭሩ ደምን መበቀለ ወይም ነብስን በነብስ ማካካስ የሚባለው የቆየ ልማድ ነው።

“ጎበዝ ተጫረሰ” ያሉት የጎጃም ብቸና ከተማ አቅራቢያ ነዋሪ አዛውንት “እንደው መላም የለው” በማለት ብዙም ማብራራት አይፈልጉም። ዜናውን ያጋራን የአዲስ አበባ ተባባሪያችን ቤተሰቦቻቸው ጋር መጥተው ያገኛቸው አዛውንት ክፉኛ ሃዘን ገብቷቸዋል።

አማራ ክልል እየተንቀሳቀሱ ያሉ የፋኖ ሃይሎች ወደ ከተማ ሲገቡ እስር ቤት ተከፍቶላቸው የወጡ ታራማሚዎች ቀደም ሲል የከሰሷቸውን ሰዎች መበቀላቸውን አዛውንቱን ጠቅሶ የዘገበው ተባባሪያችን፣ አንዱ ሌላውን እያደፈጠ ምላሽ በመስጠት በቀሉ ሳይታሰብ ተስፋፍቷል። የማቆሚያው መላም ቀላል አይመስልም።

እሁድ ተለቅልቆ ሰኞ ተበራዬ፥

ተሰው ሚስት አይሄድም ወረታውን ያዬ!

ኧረ አንቺው ነይልኝ እኔስ አልመጣም፥

እንደ ወረታው በጉዴ አልወጣም፡፡

ወረታው ተበጀ ምን ወንድም አለው፣

እንደ አህያ እሬሳ ወድቆ የቀረው!

ይልሃል የአገር ሰው ለጥቁር ደም ሲያመቻችህ።

ምስጋና – ጥቁር ደም ይህን የአንዳርጌ መስፈን ልብ ወለድ ድርሰት

በዚሁ መነሻ በተለያዩ የጎጃም መንደሮችና ከተሞች ተመሳሳይ ችግር ስለመኖሩ ለማጣራት በተደረገ ሙከራ ነገሩ ቀጣዩ የማህበራዊ ቀውስ ሊሆን እንደሚችል ፍርሃቻ ያላቸውን ተባባሪያችን አመልክቷል። ያነጋገራቸው የብቸና አቅራቢያ ነዋሪ በቀን የሚገዳደሉትን ሰዎች አማካይ ቁጥር ጠቅሰው ”አይ አገር ደም እየቋጠረ ነው። ነገሩ ሁሉ ግምኛ ነው” ሲሉ ባንድ ወገን ከጎንደር የሚወለዱት አዛውንት ሁኔታውን ገልጸውታል። ክፉኛ ማዘናቸውን በሚያሳይ መልኩ ቁና ተንፍሰው ”ተወኝ እስኪ” በማለት ዝምታን መርጠዋል።

ከአማራ ክልል የድርቅ፣ የረሃብና የማህበራዊ ቀውስ ዜናዎች እየበረከቱ ነው። ፋታ የማይሰጡ የድርቅ አሳሳቢ ችግሮች ከአስድንጋጭ የሞት መረጃ ጋር እየተሰሙበት ያለው አማራ ክልል ከጦርነት ያለገገመ ከመሆኑ ጋር ተዳምሮ የከፋ ቀውስ እንዳይከሰት ስጋቱ ከፍተኛ ነውልል በዚህ ሁሉ ስጋት ላይ “ለአማራ ህዝብ እንታገላለን” ከሚሉት ጎን ለጎን ታጠቀው የሚዘርፉ፣ ህዝብ ላይ መዋጮ እየጣሉ የሚያሰቃዩ እንዳሉም ህዝብ እየገለጸ ነው።

ቲክቨሃ የአሜሪካንን ድምጽ ጠቅሶ “በአማራ ክልል ባህር ዳር እና ጎንደር ጨምሮ በሌሎች ከተሞች ነዋሪው የዋጋ ንረቱን መቋቋም አልቻለም” በሚል ርዕስ ከስር ያለውን ዜና አስፍሯል።

የባህር ዳር ነዋሪው አቶ አለሙ ይርዳው ባለፈው ሳምንት ጤፍ ለመግዛት ወደ ገቢያ በወጡበት ወቅት ከወር በፊት በ10 ሺህ ብር የገዙት ጤፍ በሺዎች ብር ጨምሮ እንዳገኙት ገልጸዋል።

እኚሁ ነዋሪ ከ6 እና 7 ወር በፊት አንድ ኩንታል ጤፍ 6,700 ብር ገደማ መግዛታቸውን አስታውሰው አሁን 13,000 ብር መባሉን ገልጸዋል።

”በጣም ደንግጫለሁ፤ ከእጥፍ በላይ ነው የጨመረው ዝቅተኛው ጤፍ 11 ሺህ 500 እና 12 ሺህ 500 ነው የሚባለው እኔ የገዛሁት 13 ሺህ ብር ነው” ብለዋል።

ለምን በዚህ ልክ እንደጨመረ ነጋዴዎችን ጠይቀው የተሰጣቸው ምላሽ ”ከትራንስፖርት አንፃር አቅርቦት የለም፣ በየቀኑ መንገድ ይዘጋል” የሚል እንደሆነ ገልጸዋል።

ከጤፍ በተጨማሪ ሽንኩርት አንድ ኪሎ 110 ብር እንደገዙ አመልክተዋል። ቲማቲምን ጨምሮ ሌሎችም የዕለት ዕለት ግዢዎች ላይ ዋጋ ጨምሯል ብለዋል።

”13 ሺህ ብር ጤፍ ተገዝቶ እንዴት መኖር እንደሚቻል አይገባኝም ፤ በተለይ መካከለኛ እና ዝቅተኛ እንደኔ አይነት ገቢ ያላቸው የወር ደሞዝተኞች መኖር የማይቻልበት ሁኔታ ውስጥ ነው ያለነው” ሲሉ አክለዋል።

ይህንን እየፈጠረ ያለው አንደኛው ወቅታዊው የመንገድ መዘጋት ነው፤ በተጨማሪ ስግብግብ ነጋዴዎች ወቅቱን ተጠቅመው ሰው እንደተቸገረ አውቀው በከፍተኛ ዋጋ እየሸጡ በመሆኑ ነው ብለዋል።

አማራ ክልል በተለይ ምዕራብ እና ምስራቅ ጎጃም ጤፍ አምራች ቢሆንም የአካባቢው ነዋሪ በዚህ ዋጋ ለመሸመት መገደዱ አስደንጋጭ ነው ያሉ ሲሆን ለዚህ ምክንያት እየሆነ ያለው ግጭት በፍጥነት ካልቆመ ህዝቡ በኑሮ ይጎዳል ብለዋል።

አንድ ስማቸው እንዲገልፅ ያልፈለጉ ከምዕራብ ጎጃም አዴት እና ጎንጂ ቆለላ ጤፍ አምራች አካባቢዎች ጤፍ እያመጡ የሚሸጡ ነጋዴ ፤ በወቅታዊ ግጭት ምክንያት አርሶ አደሩ ምርቱን ወደገበያ እንደማያወጣ ገልጸዋል።

”አርሶ አደሩ በሰላም ውለን መግባት ስላልቻልን ምርቱን እያወጣ አይደለም። ነጋዴው ደግሞ ያገኘውን ይዞ ይመጣል” ብለዋል። እኚሁ ነጋዴ ጤፍ 12 ሺህ ብር እየሸጡ እንደሆነ ተናግረዋል።

የጎንደር ነዋሪ የሆኑት ይፍቱ ስራማረው፤ የዋጋ ንረቱ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው ብለዋል። ”እውነት ለመናገር እንኳን በሁለት ዓመት ውስጥ በዚህ ወር ውስጥ እንኳን ከፍተኛ ጭማሪ ነው ያለው። 30 እና 20 ብር ስንገዛው የነበረው እቃ አሁን 100 ቤት ውስጥ ነው።

ሽንኩርት ከግርግሩ በፊት ከ50 – 55 ብር ነበር አሁን ሱቅ ውስጥ እስከ 120 ብር ዋና ገበያ እስከ 80-100 ብር ይሸጣል። 

ሞኮሮኒ ፓስታ ከአንድ ወር በፊት ነው የጨመሩት የ20 ብር ጭማሪ አለው ፤ ጤፍ 115 ብር – 120 ብር ይባላል በኪሎ ፤ አቅርቦትም ስለሌለ ይሆናል ” ሲሉ ተናግረዋል።

አዘዞ ከተማ የሚኖሩት የችርቻሮ  ነጋዴዋ ወ/ሮ አለሚቱ ደሴ ፤ ጤፍን ጨምሮ ሌሎች እህሎች ተወዷል ብለዋል።

”የገበያው ሁኔታ በጣም ከባድ ነው ለሻጭም ለገዢም … ቀይ ጤፍ 90 ብር ነው፣ ነጭ ጤፍ  100 ብር አሁን ላይ ነው በጣም የጨመረው 60 እና 70 ብር ነበር፤ ግጭት ከጀመረ አንስቶ እስከ 100 ብር ገብቷል።  ሽንኩርትም እስከ 100 ብር እየተሸጠ ነው። ” ብለዋል።

እህል እየተቀበሉ ያሉት የገጠሩ ማህበረሰብ ይዞ ሲመጣ እንድሆነ የገለፁት ወ/ሮ አለሚቱ ”ባለው ችግር የገጠሩ ነዋሪዎች እንደልባቸው መንቀሳቀስ አልቻሉም” ሲሉ ገልጸዋል። (ethio12)

በዳያስፖራ ያለው ደግሞ በጥቂት ጥቅመኞች እየተነዳ አገር ውስጥ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ከመረዳትና መፍትሔ ከመፈለግ ይልቅ ተነስ፣ ታጠቅ፣ በለው፣ ዝመት፣ ተሰዋ ወዘተ ይላል። ከአገር ውስጥ የሚውጡ መረጃዎች የሚጠቁሙት ግን ጦርነት በቃን፣ ሰላም እንፈልጋለን፣ ማደግና ልጆቻችንን ማሳደግ እንፈልጋለን የሚል ነው። እንዲያውም አንዳንዶች ዳያስፖራ ያለው ለውጊያ ገንዘብ ከሚያዋጣ ተበድሮም ቢሆን ለሰላም ቢሠራ የተሻለ ነው፤ የራሱን ልጆች በሰላም አገር ትምህርት ቤት እየላከ፣ እያስተማረ፣ ከሩቅ ሆኖ ገፋ በለው ከሚል እዚሁ ገብቶ ከኛው ጋር ሥቃዩንም፣ መከራውንም፣ ጦርነቱንም፣ ቢያየው ጥሩ ነበር ይላሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: amhara region, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule