• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እንዴት እንኑር!

August 10, 2013 11:48 pm by Editor Leave a Comment

… ለመሆኑ ከየት መጣን?…. ወዴት እንሄዳለን? …እንዴትስ እንኑር? የሚሉትን የፈላስፋውን ጥያቄ ስናነሳ፣ ግሪክ አገር አቴን ከተማ የዓለም ፈላስፋዎች ሰሞኑን ተሰብስበው “ስለ ዓለም ሁኔታ ይነጋገራሉ” ብለን አልገመትንም ነበር።

እኛ በዚህ እትማችን ሰለ ዓለም ሳይሆን ስለ እኛው ስለ ራሳችን ችግር ነው አንዳንድ ነገሮቸን አንስተን ከግንዛቤ ውስጥ አስገብትን መለስ ብለን ለመመልከት የተነሳነው።

“…እንዴት እንኑር? ” የሚለው ጥያቄ ሲሰነዘር የሚያስቆጣቸው ሰዎች እንደሌሉ ተስፋ እናደርጋለን።

አንደንድ ጊዜ ከረጅም መላ-ምትና ግራ ከሚያጋቡ ጠማማ ጽንሰ-ሓሳቦች፣ ከቲዎሪ ዎች ይልቅ ቀላልና ጥሩ ጥያቄ ማቅረብ ፣ሌላውም ጎረቤት አገር ሆነ ራቅ ያሉ ሰዎች “እነሱስ እንዴት ይኖራሉ ?”ብሎ እራስን መጠየቅ ከብዙ ድካምና መነከራተት ያድናል።

ግን ደግሞ ወደፊት ዘልቃችሁ እንደምታነቡት ፣ እንደዚህ ዓይነቱ አካሄድ ደግሞ ሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት በደንብ ከአልተወያዩበት የአርባና የሃምሳ አመት መከራ ውስጥ አንድን ሕዝብ ከቶ አገሪቱን ያተረማምሳል። እንኳን እኛ “እንዴት እንኑር ?” ብለን ከሩሲያ በተዋስነው ትምህርት “በቀላሉ ነጻ ልንወጣ” ቀርቶ ራሺያ እራሱዋ ከገባችበት ማጥ ለመውጣት ከሰባ አመት በላይ ፈጅቶበታል ።

“…እንዴት እንኑር? ወዴት እንሄዳለን? ከየት መጣን ” የሚለው ጥያቄ የፈላስፋዎች ጥያቄ -ወረድ ብለችሁ እንደምታዩት- ብቻ አይደለም። ግን አንድ ክፍል ከሌላው በልጦ፣ የግንባር ቀደምነት ቦታውን ይዞ “…እኔ ያልኩት ከአልሆነ፣ ሞቼ እገኛለሁ፣ አለበለዚያ ዋ! አንተ ከአልተቀበልክ፣ እኔ አንተን እገደልሃለሁ…” የሚል የምሁር ክፍል አለ። እሱ ነው እንግዲህ የእኛ የዛሬው እትማችን አርዕስት።

ምሁሩ በጅምላ ሲታይ በሕብረተሰቡ ውስጥ ጥቂት አይደለም። እነሱም በተለያዩ መስኮች ውስጥ ተሰማርተው እራሳቸውንም ሕብረተሰቡንም፣ አገሪቱንም ቤተሰቦቻቸውን በአእምሮ ሥራቸውና ችሎታቸው ይረዳሉ ። ግን ከእነሱ አንዱ ክፍል -ቀጥሩ ትንሽ ቢሆነም- በጩኸቱ፣ በክርክሩ፣ በጽሑፉ፣ ግርግር በመፍጠሩ፣ በክሱ፣ በብዕሩና በምላሱ፣ በመቀስቀስና በማደረጀት ችሎታው፣ በአፍዝ አደንግዝነቱ…ጠቅላላውን መድረክ በመያዝ ችሎታው ማንም የሚደርስበት የለም። እሱም “አቫንጋርዱ የሙያ አብዮተኛ ” የሚባለው ትንሽ ክፍል ነው።

ይህ ክፍል (ፖለቲካ ምንድነው ? በሚለው መጣጥፍ ላይ አንሰተናል) ለሠራውና ለሚሰራው ሥራ ኃላፊነትና ተጠያቂነት እማይሳማው ነው። በዚህም ከሌሎች ሕግ አክባሪ ፖለቲከኞች ፍጹም ይለያል።

ኃላፊነት መቀበል ምንድነው? በአጭሩ “ሁሉን ነገር ማድረግ ስችል ለምን አላደርገውም “ብሎ መነሳት ነው። ሃምሳ ሚሊዮን፣ ሰባ ና ሰማኒያና ከዚያም አልፎ ዘጠና ሚሊዮን በሚኖርበት አገር፣ አምስትም ሚሊዮን ይሁኑ “….ጥቂት ሰወች ተሰባስበው እኛ ለአንተና ለአንቺ፣ እንዲያውም ለሁላችሁም የአሰብነው የአኗኗር ዘይቤ ወይም ሥርዕት ይህ ነው፣ ወደዳችሁት ጠላችሁት ተቀበሉት፣ ከዚያ ወጭ ትንሽ ትንፍሽ ብትሉ…” ተብሎ ፖለቲካ የሚሰራበት ዘመን ከምሥራቁ ዲክታተሮች ጋር አብሮ አልፎአል። ይህ ጊዜም አክትሞአል።

የአሁኑ እትም አተኩሮ በአገራችን ብቻ ሳይሆን በአፍሪካና በእሲያ በሥራቅ አውሮፓም ጭምር ፣አንድ የቶታሊቴሪያን አስተሳሰብ እንዴት በጥቂት ምሁሮች አመካኚነት እንዴት ተስፋፍቶ እንደመጣና “የሰውን” ልብና አእምሮ ፣የእራሳቸውንም “የፈጣሪዎቹና የተከታዮቸንም ” መንፈስ ይዞ እነሱን እንዴት “አገልጋይ ባሪያቸው” እንዳደረጋቸው ከብዙ በጥቂቱ ለማሰየት ነው።

እገረ መንገዳችንን “እኛ ማነን!” የሚለውን ስለ አሜሪካን ክሬዶ ፣…አሜሪካንን አሜሪካ ስለ አደረገው ፣ መንፈስ፣ እሱ ጸሓፊው ሳሙኤል ሐንቲንግተን “እስፐሪት” ቀደም ሲል የጻፈውን መጽሓፍ ተመልክትን አጠር ያለ ግርፋትና ክትበት ሰጥተናል።

እንዴት እንኖራለን? እንዴት አብረን እንኑር ? እናውቃለን አወዛጋቢ ጥያቄ ነው። ግን በዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ መካከል “ኢሚንት የማይሞሉ የፖለቲካ ሰዎችም አጉል ቲዎሪ አንግበው፣ እኛ ያለነው ብቻ…” እያሉ መከራ ከሚያሳዩ ጠለቅ ያለ፣ ከዘመኑ ጋር አብሮ የሚሄድ ነገር በያቀርቡልን ደግ ነው። ያ ቲዎሪ እኮ የ19ኛው ክፍለ-ዘመን ትምህርት ነው። ከእዚያ በላይ ይህን ቲዎሪ የሚያራምዱት ከጠቅላላው የአገሪቱ ምሁሮች፣ በሌላ መስክ ላይ ከተሰማሩት ከእነሱ ጋር ሲነጻጸሩ፣ እንደዚሁ ትንሽ ናቸው።ይህንንም ማወቅ ያስፈልጋል።

ተሽከርካሪ ጎማ ገና ዱሮ ጥንት በተፈጠረበት ዓለም –አውሮፓያኖች፣ ወርቅማ ጊዜህን አዲስ ታይቶና ተሰምቶ ተሞክሮ ፣ የማይታወቅ አዲስ ተሽከርካሪ ጎማ እፈጥራለሁ ብለህ ጊዜህንም ጉልበትህንም አትጨርሰው ይላሉ። ይህም ማለት በአጭሩ አዲስ የሕብረተስብ ሞዴል፣ በዓለም ላይ ታይቶም ተሰምቶም የማይታውቅ እፈጥራለሁ ብሎ መድከም ከንቱ ነው። ያው የምናውቀው የዲምክራሲና የታወቀው የፓርላማ ሥርዓት፣ ነጻው ሕብረተሰብ ይሻለናል።

የነገሮች ሁሉ እምብርት ደግሞ፣ ወዳጄ ! ነጻ ሐሳብ፣ በነጻ-ፕሬስ ላይ ማራመድ ነው። ከሁሉም አቅጣጫ ነገሮችን ሰርስረን “እንዴት እንኑር?” ለሚለው ጥያቄ በየጊዜው መልስ እንሰጣለን።

(የ”ለአእምሮ መጽሔት” ዋና አዘጋጁ ይልማ ኃይለ ሚካኤል)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule