• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እንዴት እንኑር!

August 10, 2013 11:48 pm by Editor Leave a Comment

… ለመሆኑ ከየት መጣን?…. ወዴት እንሄዳለን? …እንዴትስ እንኑር? የሚሉትን የፈላስፋውን ጥያቄ ስናነሳ፣ ግሪክ አገር አቴን ከተማ የዓለም ፈላስፋዎች ሰሞኑን ተሰብስበው “ስለ ዓለም ሁኔታ ይነጋገራሉ” ብለን አልገመትንም ነበር።

እኛ በዚህ እትማችን ሰለ ዓለም ሳይሆን ስለ እኛው ስለ ራሳችን ችግር ነው አንዳንድ ነገሮቸን አንስተን ከግንዛቤ ውስጥ አስገብትን መለስ ብለን ለመመልከት የተነሳነው።

“…እንዴት እንኑር? ” የሚለው ጥያቄ ሲሰነዘር የሚያስቆጣቸው ሰዎች እንደሌሉ ተስፋ እናደርጋለን።

አንደንድ ጊዜ ከረጅም መላ-ምትና ግራ ከሚያጋቡ ጠማማ ጽንሰ-ሓሳቦች፣ ከቲዎሪ ዎች ይልቅ ቀላልና ጥሩ ጥያቄ ማቅረብ ፣ሌላውም ጎረቤት አገር ሆነ ራቅ ያሉ ሰዎች “እነሱስ እንዴት ይኖራሉ ?”ብሎ እራስን መጠየቅ ከብዙ ድካምና መነከራተት ያድናል።

ግን ደግሞ ወደፊት ዘልቃችሁ እንደምታነቡት ፣ እንደዚህ ዓይነቱ አካሄድ ደግሞ ሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት በደንብ ከአልተወያዩበት የአርባና የሃምሳ አመት መከራ ውስጥ አንድን ሕዝብ ከቶ አገሪቱን ያተረማምሳል። እንኳን እኛ “እንዴት እንኑር ?” ብለን ከሩሲያ በተዋስነው ትምህርት “በቀላሉ ነጻ ልንወጣ” ቀርቶ ራሺያ እራሱዋ ከገባችበት ማጥ ለመውጣት ከሰባ አመት በላይ ፈጅቶበታል ።

“…እንዴት እንኑር? ወዴት እንሄዳለን? ከየት መጣን ” የሚለው ጥያቄ የፈላስፋዎች ጥያቄ -ወረድ ብለችሁ እንደምታዩት- ብቻ አይደለም። ግን አንድ ክፍል ከሌላው በልጦ፣ የግንባር ቀደምነት ቦታውን ይዞ “…እኔ ያልኩት ከአልሆነ፣ ሞቼ እገኛለሁ፣ አለበለዚያ ዋ! አንተ ከአልተቀበልክ፣ እኔ አንተን እገደልሃለሁ…” የሚል የምሁር ክፍል አለ። እሱ ነው እንግዲህ የእኛ የዛሬው እትማችን አርዕስት።

ምሁሩ በጅምላ ሲታይ በሕብረተሰቡ ውስጥ ጥቂት አይደለም። እነሱም በተለያዩ መስኮች ውስጥ ተሰማርተው እራሳቸውንም ሕብረተሰቡንም፣ አገሪቱንም ቤተሰቦቻቸውን በአእምሮ ሥራቸውና ችሎታቸው ይረዳሉ ። ግን ከእነሱ አንዱ ክፍል -ቀጥሩ ትንሽ ቢሆነም- በጩኸቱ፣ በክርክሩ፣ በጽሑፉ፣ ግርግር በመፍጠሩ፣ በክሱ፣ በብዕሩና በምላሱ፣ በመቀስቀስና በማደረጀት ችሎታው፣ በአፍዝ አደንግዝነቱ…ጠቅላላውን መድረክ በመያዝ ችሎታው ማንም የሚደርስበት የለም። እሱም “አቫንጋርዱ የሙያ አብዮተኛ ” የሚባለው ትንሽ ክፍል ነው።

ይህ ክፍል (ፖለቲካ ምንድነው ? በሚለው መጣጥፍ ላይ አንሰተናል) ለሠራውና ለሚሰራው ሥራ ኃላፊነትና ተጠያቂነት እማይሳማው ነው። በዚህም ከሌሎች ሕግ አክባሪ ፖለቲከኞች ፍጹም ይለያል።

ኃላፊነት መቀበል ምንድነው? በአጭሩ “ሁሉን ነገር ማድረግ ስችል ለምን አላደርገውም “ብሎ መነሳት ነው። ሃምሳ ሚሊዮን፣ ሰባ ና ሰማኒያና ከዚያም አልፎ ዘጠና ሚሊዮን በሚኖርበት አገር፣ አምስትም ሚሊዮን ይሁኑ “….ጥቂት ሰወች ተሰባስበው እኛ ለአንተና ለአንቺ፣ እንዲያውም ለሁላችሁም የአሰብነው የአኗኗር ዘይቤ ወይም ሥርዕት ይህ ነው፣ ወደዳችሁት ጠላችሁት ተቀበሉት፣ ከዚያ ወጭ ትንሽ ትንፍሽ ብትሉ…” ተብሎ ፖለቲካ የሚሰራበት ዘመን ከምሥራቁ ዲክታተሮች ጋር አብሮ አልፎአል። ይህ ጊዜም አክትሞአል።

የአሁኑ እትም አተኩሮ በአገራችን ብቻ ሳይሆን በአፍሪካና በእሲያ በሥራቅ አውሮፓም ጭምር ፣አንድ የቶታሊቴሪያን አስተሳሰብ እንዴት በጥቂት ምሁሮች አመካኚነት እንዴት ተስፋፍቶ እንደመጣና “የሰውን” ልብና አእምሮ ፣የእራሳቸውንም “የፈጣሪዎቹና የተከታዮቸንም ” መንፈስ ይዞ እነሱን እንዴት “አገልጋይ ባሪያቸው” እንዳደረጋቸው ከብዙ በጥቂቱ ለማሰየት ነው።

እገረ መንገዳችንን “እኛ ማነን!” የሚለውን ስለ አሜሪካን ክሬዶ ፣…አሜሪካንን አሜሪካ ስለ አደረገው ፣ መንፈስ፣ እሱ ጸሓፊው ሳሙኤል ሐንቲንግተን “እስፐሪት” ቀደም ሲል የጻፈውን መጽሓፍ ተመልክትን አጠር ያለ ግርፋትና ክትበት ሰጥተናል።

እንዴት እንኖራለን? እንዴት አብረን እንኑር ? እናውቃለን አወዛጋቢ ጥያቄ ነው። ግን በዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ መካከል “ኢሚንት የማይሞሉ የፖለቲካ ሰዎችም አጉል ቲዎሪ አንግበው፣ እኛ ያለነው ብቻ…” እያሉ መከራ ከሚያሳዩ ጠለቅ ያለ፣ ከዘመኑ ጋር አብሮ የሚሄድ ነገር በያቀርቡልን ደግ ነው። ያ ቲዎሪ እኮ የ19ኛው ክፍለ-ዘመን ትምህርት ነው። ከእዚያ በላይ ይህን ቲዎሪ የሚያራምዱት ከጠቅላላው የአገሪቱ ምሁሮች፣ በሌላ መስክ ላይ ከተሰማሩት ከእነሱ ጋር ሲነጻጸሩ፣ እንደዚሁ ትንሽ ናቸው።ይህንንም ማወቅ ያስፈልጋል።

ተሽከርካሪ ጎማ ገና ዱሮ ጥንት በተፈጠረበት ዓለም –አውሮፓያኖች፣ ወርቅማ ጊዜህን አዲስ ታይቶና ተሰምቶ ተሞክሮ ፣ የማይታወቅ አዲስ ተሽከርካሪ ጎማ እፈጥራለሁ ብለህ ጊዜህንም ጉልበትህንም አትጨርሰው ይላሉ። ይህም ማለት በአጭሩ አዲስ የሕብረተስብ ሞዴል፣ በዓለም ላይ ታይቶም ተሰምቶም የማይታውቅ እፈጥራለሁ ብሎ መድከም ከንቱ ነው። ያው የምናውቀው የዲምክራሲና የታወቀው የፓርላማ ሥርዓት፣ ነጻው ሕብረተሰብ ይሻለናል።

የነገሮች ሁሉ እምብርት ደግሞ፣ ወዳጄ ! ነጻ ሐሳብ፣ በነጻ-ፕሬስ ላይ ማራመድ ነው። ከሁሉም አቅጣጫ ነገሮችን ሰርስረን “እንዴት እንኑር?” ለሚለው ጥያቄ በየጊዜው መልስ እንሰጣለን።

(የ”ለአእምሮ መጽሔት” ዋና አዘጋጁ ይልማ ኃይለ ሚካኤል)

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule