• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ጉዳይ

July 25, 2016 05:04 am by Editor Leave a Comment

አቶ ዠ፣ ከ Fast Lane ዩኒቨርስቲ በተልዕኮ በአራት ወራት እድሜ የዶክትሬት ድግሪ የተጫነባቸው የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው። በ“ተልዕኮ” ማለት ለ Fast Lane ዩኒቨርሲቲ ደብዳቤ መጻፍና ገንዘብ መላክ ነው ተብሎ ይታማል። ይህን ሃሜት እኔ ጭምጭታ ነው የሰማሁት። ጭምጭምታው  ግን ከሁነኛ (አስተማማኝ) ሰው ነው።

አቶዠ፣ቀድሞ በደርግ ጊዜ መፈክር ጸሃፊ፣ በኋላም በኢሃዲግ ጊዜ ልማታዊ ጸሃፌ ተውኔት፣ቀድሞ የኢሃዲግ ፍቅር ቤት ሥራ አስቀማጭ፣ ይቅርታ ሥራ አስኪያጅ፣ በዩናይትድ ኔሽንስ የኢትዮጵያ ተወካይ፣ ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት በራስ አነሳሽነት ተወዳዳሪ፣ ወዘተርፈ…ወዘተርፈ….ወዘተርፈ….እንዳልኩት የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው።

ሆኖም ችግር ተፈጠረ። “እኔ ነኝ የምጭንባቸው፣ እኔ ነኝ የምጭንባቸው” የሚሉ ዩኒቨርስቲዎች ኢትዮጵያን ሞሏት። አንደኛው ዩኒቨርስቲ አንተ እንኳን ይቅርብህ ቢባልና ሊመከር ቢታሰብ “እኔ የዶክትሬት ዲግሪ ፕሮግራም ስለሌለኝ ነው?” በማለት ኩርፊያ ሁሉ ነካካው። ዋናው ችግር ግን ወዲህ ነው።

እንግዲህ አቶ ዠ መታወቂያቸው ላይ ብሄር በሚለው ሥር “አማራ” የሚል ተጽፏል። ሆኖም ግን አቶ ዠ የአባታቸው አባት አማራ፣ የአባታቸው እናት ደግሞ ኦሮሞ ሲሆኑ፣ የእናታቸው አባት ሲዳማ፣ የእናታቸው እናት ደግሞ ጉራጌ ነበሩ። በዚህ የተነሳ አራት ክልላዊ ዩኒቨርሲቲዎች “እኔ ነኝ የምጭንባቸው፣ እኔ ነኝ የምጭንባቸው” ሲሉ አታካራ ያዙ።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ደግሞ አቶ ዠ ለኔ ነው የሚገቡት ሲል አታካራው ውስጥ ጥልቅ አለ። ምክንያት? “አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ክልላዊ አይደለም፣ ፌደራላዊ ነው፣ ብሄር ብሄረሰብን የሚያንጸባርቅ። አቶ ዠ የዚህ ተምሳሌት ናቸው። ብሄር ብሄረሰብን ያንጸባርቃሉና” ሲል ተሟገተ።

ሌላው ችግር ደግሞ አቶ ዠ በምን መስክ የክብር ዶክትሬት ይሰጣቸው የሚለው ነው። አቶ ዠ አብዛኛውን እድሜያቸውን መፈክር በመጻፍ ነው ያሳለፉት። ለምሳሌ በሥነ ጥበብ በኩል፣ በማህረሰብ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ “Doctor of Letters” የሚባል የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ይሰጣል። ለአቶ ዠ ታዲያ “Doctor of Slogan” የሚባል የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ይሰጥ? የክልልና የፌደራል ዩኒቨርሥቲዎች የአካዳሚክ ጉባኤዎች ራስ ምታት ሆኑ አቶ ዠ።

ይህንን ሲሰሙ የአቶ ዠ ባለቤት ወይዘሮ ዘ “በልጅህ በኩል ደግሞ ኤርትራዊ ነህና አሥመራ ዩኒቨርሲቲም ዶክትሬት ልጫንብህ እንዳይልህ” ሲሉ ተሳለቁ። የባለቤታቸው የወይዘሮ ዘ እናትና አባት ”ኤርትራዊ“ ናቸውና።

የግርጌ ማስታወሻ

ይህንን ሙግት አስመልክቶ አንዳንድ ሰዎች አስተያየታቸውን መሥጠት ያዙ። አዛብኞቹ አሥተያየት ሰጪዎች አስተያየታቸው ተመሳሳይ ቢሆንም አንዱ ግን ከሌሎች በመለየት ”የክብር ዶክትሬትነት ማዕረግ የተሰጠው ሰው ማዕረጉን ከስሙ አስቀድሞ በመለጠፍ ሊጠቀምበት ይችላል” ሲሉ ደመደሙ። መልሱ አጭር ነው። ይህ ድርጊት የተለመደ አይደለም። የክብር ዶክትሬት ዲግሪውን የሰጠው ዩኒቨርስቲ ለሰጠው ሰው “ዶ/ር ዠ” ብሎ ሊጠራ፣ ሊጻጻፍ ይችላል፣ የተሰጣቸው ሰውዬ (ዠ) ግን እንዳይጠቀሙበት ይመከራሉ። ሌሎችም በዚያ እንዲጠሩዋቸው የተለመደና የሚደገፍ ተግባር አይደለም። የክብር ዶክትሬት ብለው የህይወት ታሪካቸው፣ የሥራ ልምዳቸው (CV and Resume) ላይ ሊጠቅሱት ይፈቀዳል።

“Honorary doctorates are listed as an honor or award on a resume, rather than part of education with earned academic degrees.” እንዲሉ። ይህንን መረጃ በመረጃ በሆነው በአሁኑ ዘመን በቀላሉ ማረጋገጥ ይቻላል።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule