• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ጉዳይ

July 25, 2016 05:04 am by Editor Leave a Comment

አቶ ዠ፣ ከ Fast Lane ዩኒቨርስቲ በተልዕኮ በአራት ወራት እድሜ የዶክትሬት ድግሪ የተጫነባቸው የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው። በ“ተልዕኮ” ማለት ለ Fast Lane ዩኒቨርሲቲ ደብዳቤ መጻፍና ገንዘብ መላክ ነው ተብሎ ይታማል። ይህን ሃሜት እኔ ጭምጭታ ነው የሰማሁት። ጭምጭምታው  ግን ከሁነኛ (አስተማማኝ) ሰው ነው።

አቶዠ፣ቀድሞ በደርግ ጊዜ መፈክር ጸሃፊ፣ በኋላም በኢሃዲግ ጊዜ ልማታዊ ጸሃፌ ተውኔት፣ቀድሞ የኢሃዲግ ፍቅር ቤት ሥራ አስቀማጭ፣ ይቅርታ ሥራ አስኪያጅ፣ በዩናይትድ ኔሽንስ የኢትዮጵያ ተወካይ፣ ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት በራስ አነሳሽነት ተወዳዳሪ፣ ወዘተርፈ…ወዘተርፈ….ወዘተርፈ….እንዳልኩት የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው።

ሆኖም ችግር ተፈጠረ። “እኔ ነኝ የምጭንባቸው፣ እኔ ነኝ የምጭንባቸው” የሚሉ ዩኒቨርስቲዎች ኢትዮጵያን ሞሏት። አንደኛው ዩኒቨርስቲ አንተ እንኳን ይቅርብህ ቢባልና ሊመከር ቢታሰብ “እኔ የዶክትሬት ዲግሪ ፕሮግራም ስለሌለኝ ነው?” በማለት ኩርፊያ ሁሉ ነካካው። ዋናው ችግር ግን ወዲህ ነው።

እንግዲህ አቶ ዠ መታወቂያቸው ላይ ብሄር በሚለው ሥር “አማራ” የሚል ተጽፏል። ሆኖም ግን አቶ ዠ የአባታቸው አባት አማራ፣ የአባታቸው እናት ደግሞ ኦሮሞ ሲሆኑ፣ የእናታቸው አባት ሲዳማ፣ የእናታቸው እናት ደግሞ ጉራጌ ነበሩ። በዚህ የተነሳ አራት ክልላዊ ዩኒቨርሲቲዎች “እኔ ነኝ የምጭንባቸው፣ እኔ ነኝ የምጭንባቸው” ሲሉ አታካራ ያዙ።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ደግሞ አቶ ዠ ለኔ ነው የሚገቡት ሲል አታካራው ውስጥ ጥልቅ አለ። ምክንያት? “አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ክልላዊ አይደለም፣ ፌደራላዊ ነው፣ ብሄር ብሄረሰብን የሚያንጸባርቅ። አቶ ዠ የዚህ ተምሳሌት ናቸው። ብሄር ብሄረሰብን ያንጸባርቃሉና” ሲል ተሟገተ።

ሌላው ችግር ደግሞ አቶ ዠ በምን መስክ የክብር ዶክትሬት ይሰጣቸው የሚለው ነው። አቶ ዠ አብዛኛውን እድሜያቸውን መፈክር በመጻፍ ነው ያሳለፉት። ለምሳሌ በሥነ ጥበብ በኩል፣ በማህረሰብ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ “Doctor of Letters” የሚባል የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ይሰጣል። ለአቶ ዠ ታዲያ “Doctor of Slogan” የሚባል የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ይሰጥ? የክልልና የፌደራል ዩኒቨርሥቲዎች የአካዳሚክ ጉባኤዎች ራስ ምታት ሆኑ አቶ ዠ።

ይህንን ሲሰሙ የአቶ ዠ ባለቤት ወይዘሮ ዘ “በልጅህ በኩል ደግሞ ኤርትራዊ ነህና አሥመራ ዩኒቨርሲቲም ዶክትሬት ልጫንብህ እንዳይልህ” ሲሉ ተሳለቁ። የባለቤታቸው የወይዘሮ ዘ እናትና አባት ”ኤርትራዊ“ ናቸውና።

የግርጌ ማስታወሻ

ይህንን ሙግት አስመልክቶ አንዳንድ ሰዎች አስተያየታቸውን መሥጠት ያዙ። አዛብኞቹ አሥተያየት ሰጪዎች አስተያየታቸው ተመሳሳይ ቢሆንም አንዱ ግን ከሌሎች በመለየት ”የክብር ዶክትሬትነት ማዕረግ የተሰጠው ሰው ማዕረጉን ከስሙ አስቀድሞ በመለጠፍ ሊጠቀምበት ይችላል” ሲሉ ደመደሙ። መልሱ አጭር ነው። ይህ ድርጊት የተለመደ አይደለም። የክብር ዶክትሬት ዲግሪውን የሰጠው ዩኒቨርስቲ ለሰጠው ሰው “ዶ/ር ዠ” ብሎ ሊጠራ፣ ሊጻጻፍ ይችላል፣ የተሰጣቸው ሰውዬ (ዠ) ግን እንዳይጠቀሙበት ይመከራሉ። ሌሎችም በዚያ እንዲጠሩዋቸው የተለመደና የሚደገፍ ተግባር አይደለም። የክብር ዶክትሬት ብለው የህይወት ታሪካቸው፣ የሥራ ልምዳቸው (CV and Resume) ላይ ሊጠቅሱት ይፈቀዳል።

“Honorary doctorates are listed as an honor or award on a resume, rather than part of education with earned academic degrees.” እንዲሉ። ይህንን መረጃ በመረጃ በሆነው በአሁኑ ዘመን በቀላሉ ማረጋገጥ ይቻላል።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule