• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ጉዳይ

July 25, 2016 05:04 am by Editor Leave a Comment

አቶ ዠ፣ ከ Fast Lane ዩኒቨርስቲ በተልዕኮ በአራት ወራት እድሜ የዶክትሬት ድግሪ የተጫነባቸው የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው። በ“ተልዕኮ” ማለት ለ Fast Lane ዩኒቨርሲቲ ደብዳቤ መጻፍና ገንዘብ መላክ ነው ተብሎ ይታማል። ይህን ሃሜት እኔ ጭምጭታ ነው የሰማሁት። ጭምጭምታው  ግን ከሁነኛ (አስተማማኝ) ሰው ነው።

አቶዠ፣ቀድሞ በደርግ ጊዜ መፈክር ጸሃፊ፣ በኋላም በኢሃዲግ ጊዜ ልማታዊ ጸሃፌ ተውኔት፣ቀድሞ የኢሃዲግ ፍቅር ቤት ሥራ አስቀማጭ፣ ይቅርታ ሥራ አስኪያጅ፣ በዩናይትድ ኔሽንስ የኢትዮጵያ ተወካይ፣ ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት በራስ አነሳሽነት ተወዳዳሪ፣ ወዘተርፈ…ወዘተርፈ….ወዘተርፈ….እንዳልኩት የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው።

ሆኖም ችግር ተፈጠረ። “እኔ ነኝ የምጭንባቸው፣ እኔ ነኝ የምጭንባቸው” የሚሉ ዩኒቨርስቲዎች ኢትዮጵያን ሞሏት። አንደኛው ዩኒቨርስቲ አንተ እንኳን ይቅርብህ ቢባልና ሊመከር ቢታሰብ “እኔ የዶክትሬት ዲግሪ ፕሮግራም ስለሌለኝ ነው?” በማለት ኩርፊያ ሁሉ ነካካው። ዋናው ችግር ግን ወዲህ ነው።

እንግዲህ አቶ ዠ መታወቂያቸው ላይ ብሄር በሚለው ሥር “አማራ” የሚል ተጽፏል። ሆኖም ግን አቶ ዠ የአባታቸው አባት አማራ፣ የአባታቸው እናት ደግሞ ኦሮሞ ሲሆኑ፣ የእናታቸው አባት ሲዳማ፣ የእናታቸው እናት ደግሞ ጉራጌ ነበሩ። በዚህ የተነሳ አራት ክልላዊ ዩኒቨርሲቲዎች “እኔ ነኝ የምጭንባቸው፣ እኔ ነኝ የምጭንባቸው” ሲሉ አታካራ ያዙ።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ደግሞ አቶ ዠ ለኔ ነው የሚገቡት ሲል አታካራው ውስጥ ጥልቅ አለ። ምክንያት? “አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ክልላዊ አይደለም፣ ፌደራላዊ ነው፣ ብሄር ብሄረሰብን የሚያንጸባርቅ። አቶ ዠ የዚህ ተምሳሌት ናቸው። ብሄር ብሄረሰብን ያንጸባርቃሉና” ሲል ተሟገተ።

ሌላው ችግር ደግሞ አቶ ዠ በምን መስክ የክብር ዶክትሬት ይሰጣቸው የሚለው ነው። አቶ ዠ አብዛኛውን እድሜያቸውን መፈክር በመጻፍ ነው ያሳለፉት። ለምሳሌ በሥነ ጥበብ በኩል፣ በማህረሰብ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ “Doctor of Letters” የሚባል የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ይሰጣል። ለአቶ ዠ ታዲያ “Doctor of Slogan” የሚባል የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ይሰጥ? የክልልና የፌደራል ዩኒቨርሥቲዎች የአካዳሚክ ጉባኤዎች ራስ ምታት ሆኑ አቶ ዠ።

ይህንን ሲሰሙ የአቶ ዠ ባለቤት ወይዘሮ ዘ “በልጅህ በኩል ደግሞ ኤርትራዊ ነህና አሥመራ ዩኒቨርሲቲም ዶክትሬት ልጫንብህ እንዳይልህ” ሲሉ ተሳለቁ። የባለቤታቸው የወይዘሮ ዘ እናትና አባት ”ኤርትራዊ“ ናቸውና።

የግርጌ ማስታወሻ

ይህንን ሙግት አስመልክቶ አንዳንድ ሰዎች አስተያየታቸውን መሥጠት ያዙ። አዛብኞቹ አሥተያየት ሰጪዎች አስተያየታቸው ተመሳሳይ ቢሆንም አንዱ ግን ከሌሎች በመለየት ”የክብር ዶክትሬትነት ማዕረግ የተሰጠው ሰው ማዕረጉን ከስሙ አስቀድሞ በመለጠፍ ሊጠቀምበት ይችላል” ሲሉ ደመደሙ። መልሱ አጭር ነው። ይህ ድርጊት የተለመደ አይደለም። የክብር ዶክትሬት ዲግሪውን የሰጠው ዩኒቨርስቲ ለሰጠው ሰው “ዶ/ር ዠ” ብሎ ሊጠራ፣ ሊጻጻፍ ይችላል፣ የተሰጣቸው ሰውዬ (ዠ) ግን እንዳይጠቀሙበት ይመከራሉ። ሌሎችም በዚያ እንዲጠሩዋቸው የተለመደና የሚደገፍ ተግባር አይደለም። የክብር ዶክትሬት ብለው የህይወት ታሪካቸው፣ የሥራ ልምዳቸው (CV and Resume) ላይ ሊጠቅሱት ይፈቀዳል።

“Honorary doctorates are listed as an honor or award on a resume, rather than part of education with earned academic degrees.” እንዲሉ። ይህንን መረጃ በመረጃ በሆነው በአሁኑ ዘመን በቀላሉ ማረጋገጥ ይቻላል።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule