• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ጉዳይ

July 25, 2016 05:04 am by Editor Leave a Comment

አቶ ዠ፣ ከ Fast Lane ዩኒቨርስቲ በተልዕኮ በአራት ወራት እድሜ የዶክትሬት ድግሪ የተጫነባቸው የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው። በ“ተልዕኮ” ማለት ለ Fast Lane ዩኒቨርሲቲ ደብዳቤ መጻፍና ገንዘብ መላክ ነው ተብሎ ይታማል። ይህን ሃሜት እኔ ጭምጭታ ነው የሰማሁት። ጭምጭምታው  ግን ከሁነኛ (አስተማማኝ) ሰው ነው።

አቶዠ፣ቀድሞ በደርግ ጊዜ መፈክር ጸሃፊ፣ በኋላም በኢሃዲግ ጊዜ ልማታዊ ጸሃፌ ተውኔት፣ቀድሞ የኢሃዲግ ፍቅር ቤት ሥራ አስቀማጭ፣ ይቅርታ ሥራ አስኪያጅ፣ በዩናይትድ ኔሽንስ የኢትዮጵያ ተወካይ፣ ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት በራስ አነሳሽነት ተወዳዳሪ፣ ወዘተርፈ…ወዘተርፈ….ወዘተርፈ….እንዳልኩት የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው።

ሆኖም ችግር ተፈጠረ። “እኔ ነኝ የምጭንባቸው፣ እኔ ነኝ የምጭንባቸው” የሚሉ ዩኒቨርስቲዎች ኢትዮጵያን ሞሏት። አንደኛው ዩኒቨርስቲ አንተ እንኳን ይቅርብህ ቢባልና ሊመከር ቢታሰብ “እኔ የዶክትሬት ዲግሪ ፕሮግራም ስለሌለኝ ነው?” በማለት ኩርፊያ ሁሉ ነካካው። ዋናው ችግር ግን ወዲህ ነው።

እንግዲህ አቶ ዠ መታወቂያቸው ላይ ብሄር በሚለው ሥር “አማራ” የሚል ተጽፏል። ሆኖም ግን አቶ ዠ የአባታቸው አባት አማራ፣ የአባታቸው እናት ደግሞ ኦሮሞ ሲሆኑ፣ የእናታቸው አባት ሲዳማ፣ የእናታቸው እናት ደግሞ ጉራጌ ነበሩ። በዚህ የተነሳ አራት ክልላዊ ዩኒቨርሲቲዎች “እኔ ነኝ የምጭንባቸው፣ እኔ ነኝ የምጭንባቸው” ሲሉ አታካራ ያዙ።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ደግሞ አቶ ዠ ለኔ ነው የሚገቡት ሲል አታካራው ውስጥ ጥልቅ አለ። ምክንያት? “አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ክልላዊ አይደለም፣ ፌደራላዊ ነው፣ ብሄር ብሄረሰብን የሚያንጸባርቅ። አቶ ዠ የዚህ ተምሳሌት ናቸው። ብሄር ብሄረሰብን ያንጸባርቃሉና” ሲል ተሟገተ።

ሌላው ችግር ደግሞ አቶ ዠ በምን መስክ የክብር ዶክትሬት ይሰጣቸው የሚለው ነው። አቶ ዠ አብዛኛውን እድሜያቸውን መፈክር በመጻፍ ነው ያሳለፉት። ለምሳሌ በሥነ ጥበብ በኩል፣ በማህረሰብ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ “Doctor of Letters” የሚባል የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ይሰጣል። ለአቶ ዠ ታዲያ “Doctor of Slogan” የሚባል የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ይሰጥ? የክልልና የፌደራል ዩኒቨርሥቲዎች የአካዳሚክ ጉባኤዎች ራስ ምታት ሆኑ አቶ ዠ።

ይህንን ሲሰሙ የአቶ ዠ ባለቤት ወይዘሮ ዘ “በልጅህ በኩል ደግሞ ኤርትራዊ ነህና አሥመራ ዩኒቨርሲቲም ዶክትሬት ልጫንብህ እንዳይልህ” ሲሉ ተሳለቁ። የባለቤታቸው የወይዘሮ ዘ እናትና አባት ”ኤርትራዊ“ ናቸውና።

የግርጌ ማስታወሻ

ይህንን ሙግት አስመልክቶ አንዳንድ ሰዎች አስተያየታቸውን መሥጠት ያዙ። አዛብኞቹ አሥተያየት ሰጪዎች አስተያየታቸው ተመሳሳይ ቢሆንም አንዱ ግን ከሌሎች በመለየት ”የክብር ዶክትሬትነት ማዕረግ የተሰጠው ሰው ማዕረጉን ከስሙ አስቀድሞ በመለጠፍ ሊጠቀምበት ይችላል” ሲሉ ደመደሙ። መልሱ አጭር ነው። ይህ ድርጊት የተለመደ አይደለም። የክብር ዶክትሬት ዲግሪውን የሰጠው ዩኒቨርስቲ ለሰጠው ሰው “ዶ/ር ዠ” ብሎ ሊጠራ፣ ሊጻጻፍ ይችላል፣ የተሰጣቸው ሰውዬ (ዠ) ግን እንዳይጠቀሙበት ይመከራሉ። ሌሎችም በዚያ እንዲጠሩዋቸው የተለመደና የሚደገፍ ተግባር አይደለም። የክብር ዶክትሬት ብለው የህይወት ታሪካቸው፣ የሥራ ልምዳቸው (CV and Resume) ላይ ሊጠቅሱት ይፈቀዳል።

“Honorary doctorates are listed as an honor or award on a resume, rather than part of education with earned academic degrees.” እንዲሉ። ይህንን መረጃ በመረጃ በሆነው በአሁኑ ዘመን በቀላሉ ማረጋገጥ ይቻላል።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule