• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሶስቱ ቀናት ፈታኝ ተጋድሎ በብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አንደበት

November 12, 2020 01:30 am by Editor 2 Comments

ዳንሻ ከተማ በሚገኘው የሰሜን ዕዝ አምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር ካምፕ ጊቢ ውስጥ የመከላከያ መኪናዎች በጥይት ተበሳስተው ይታያሉ። መስታወታቸው ረግፏል፤ ዛፎቹም የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል፤ መጥረቢያ እንጂ የጥይት ውርጅብኝ የቆረጣቸው አይመስሉም። የግንብና ቆርቆሮ ቤቶች እንደ ወንፊት ተበሳስተዋል። የጥይቶች ቀላሃ እንደ ጠጠር ተብትኗል።

ዕለተ ማክሰኞ ጥቅምት 25 ቀን 2013ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ሰዓት አካባቢ በዳንሻ ከተማ ያልተጠበቀ፣ አሳዛኝ፣ አስደጋጭ ድርጊት ነው የተፈጸመው። በከተማዋ የሚገኘው የሰሜን ዕዝ የአምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር የተደገሰለትን ጥቃት አያውቅም። በመካናይዝድ ክፍለ ጦሩ ስታፍ ውስጥ የሚሰሩት መደበኛ ስራቸውን ከውነው እንቅልፍ ላይ ናቸው።

በዚህ ምሽት ግን የትግራይ ልዩ ኃይል አባላት ወደ ካምፑ ዘለቁ፤ ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አድማሱን እንደሚፈልጉትና እንዲጠራላችሁ የበር ጥበቃዎችን ይጠይቃሉ።

ጀኔራሉም እንደማይመጡ ሲነገራቸው ተመልሰው ይሄዱና ተጨማሪ ኃይል ይዘው መጥተው በካምፑ ላይ የጥይት መአት ማውረድ ይጀምራሉ። ውስጥ የነበሩ የመከላከያ ሠራዊት አባላትም በጽናት የመመከት ስራ ውስጥ ገቡ፤ ለሶስት ቀንና ሌሊት በጽናት ታገሉ።

አንድ የመከላከያ ሠራዊት የመረጃ ሰራተኛ ወደ ጀነራሉ ጆሮ ተጠግቶ አካባቢውን የትግራይ ልዩ ሀይሎች ከቦታል። ፍላጎት ካለህ ሽማግሌዎቹ ከአካባቢው እናስወጣው ብለው ነግረውኛል፤ ውሳኔህ ምንድነው ሲል ጠየቀኝ ያሉት ብርጋዴር ጀነራሉ፣ የእነሱ ፍላጎት እኔም ወኔዬን ተሰልቤ የሲቪል ልብስ ለብሼ ተደብቄ ወደ አማራ ክልል እንድወጣ፤ አልያም እኔን አታለው እንድያዝ በማድረግ ካምፕ ውስጥና በአቅራቢያው ባለው የመከላከያ ሠራዊት ላይ ለመሰንዘር ያቀዱትን ጥቃት የመከላከልና የመመከት ስራ ለማሰናከል ነው።

በዚህም በቀላሉ ሰራዊቱንና መሳሪያውን በቁጥጥር ስር ለማዋል አስበው መሆኑን ገለጹልን።

እኔም ምላሼ ሽምግልናውን አለመቀበል ብቻ ሳይሆን የመረጃ ሰራተኛው ከሽማግሌዎቹ ጋር ለጥሩም ይሁን ለመጥፎ መገናኘት እንደሌለበት አስጠንቅቄ ነገርኩት። አሁን ይህን ያለኝ ልጅ ቆስሎ ለህክምና ወደ ጎንደር ሄዷል። ሲመጣ ጠይቄ ዓላማቸው ምን እንደነበር የምረዳው ይሆናል። ተመትቶ ስለነበረ እኔም እንዳልሞት አስቦ ይሆናል የሚል ግምት አለኝ ብለውናል።

የሶስት ቀን ከበባው በጣም አስቸጋሪ ነበር። 24 ሰዓት ተኩስ ነው። ያጠቃሉ እኛ እንከላከላለን፤ ይሄዱና ምግብ በልተው ኃይል ጨምረው ያጠቃሉ፤ ሲታኮሱ የነበሩት ልዩ ሀይሎች ወደ ካምፓቸው ሄደው አርፈውና ጥይት ጭነው ይመጣሉ። እኛ ካለንበት ቦታ ውጭ መፈናፈኛ ስፍራ የለንም።

እንደ ቀለበት ዙሪያውን ከበውና ውሃ፣ ምግብ፣ ጥይት የለም። ያለችንን ነው በቁጠባ የምንጠቀመው ሲሉ ያብራሩት ጀነራሉ፣ እኔም አልፎ አልፎ እንደ ምሽግ ከተጠቀምኩበት ግንብ ቤት እየወጣሁ ለወታደሮቼ ጥይት በቁጠባ ተጠቀሙ እያልኩ አሳስብ ነበር ሲሉ ይገልጻሉ። እነሱም አላሳፈሩኝም በጽናት ተዋደቁ።

የሰራዊታችን በጽናት የመከላከል ሞራል የሚገርም፣ የሚደነቅና ታምር የሚያስብል ነው ይላሉ።

አርፒጂ፣ ቦንብ፣ መትረየስ፣ ክላሽ እንደ ዝናብ ቢያርከፈክፉብንም ለሶስት ቀናት ቀንና ሌሊት መክተናል።በፍጹም እንተርፋለን ብለን አላሰብነም፤ ከቻልን እስከ መጨረሻው እንከላከላለን፤ ካልቻልን ደግሞ በመጨረሻ ላይ ራሳችንን እናጠፋለን የሚል አቋም ነበርን።

ግን በእግዚአብሔር ቸርነት፤ በመከላከያ ሠራዊት ፈጥኖ ደራሽነት ቀለበቱ ተሰብሮ ከመከላከል ወደ ማጥቃት ተሸጋግረናል ብለውናል ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም።

ድርጊቱ የሚያሳዝን ነው፤ በህወሓት ከሀዲ ቡድን እንዲህ አይነት ጥቃት ይፈጸምብናል ብለን አስበን፤አልመንም አናውቅም የሚሉት በሰሜን ዕዝ የአምስተኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ሙሉዓለም አድማሱ፤ ምክንያቱም ከኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ጀምሮ እዚሁ ነው እየኖርን ያለው። ህዝቡን መሪዎቹንም በደንብ እናውቃቸዋለን ብለዋል።

“አብረህ እየበላህ እየጠጣህ፣ ተዋልደህ ተጋምደህ፤ ትዳር መስርተህ፣ ልጆች ወልደህ፤ ቤተሰብ ሆነህ በፍጹም ጥቃት ሊሰነዝሩብኝ ይችላሉ ብለህ አታስብም፤ ሆኖም ያልታሰበው ተፈጸመ፤ ያልተጠበቀው ሆነ” ሲሉ በትግራይ ክልል ልዩ ኃይል የተሰነዘረባቸውን ጥቃት አሳዛኝ ሲሉ ይገልጹታል።

ኩርፊያና የተለያዩ መገለጫዎች ይታያሉ። ይህን ተከትሎ ጥርጣሬዎች ቢኖሩም ደፍረው መከላከያ ሠራዊት ካምፕ ውስጥ ገብተው ያጠቃሉ ብለን አላሰብንም።

ምክንያቱም ወንድምህ ሊያኮርፍ ይችላል እንጂ ያጠቃኛል፤ ይገለኛል ብለህ ፈጸሞ አትገምትም። የሚሉት ብርጋዴር ጀኔራሉ፤ ግን የትግራይ ልዩ ሀይሎች ዕለተ ማክሰኞ 25ቀን 2013ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ያለምንም ርህራሄ ዙሪያውን እንደ ቀለበት ከበውን አጠቁን፣ አጠቁን እኛም በጽናት ተከላከልን፤ መከትን ብለዋል።

የህወሓት ቡድን ዓላማ የመከላከያ ሠራዊትን መድፎች፣ ታንኮች፣ ብረት ለበሶችን መንጠቅና መከላከያን ማፍረስ ነው። በዚህ ብቻ የተወሰነ አይደለም፤ በራሳችን መሳሪያ ተመልሰው እኛን ለመውጋት ነበር ዕቅዳቸው። ይህ አልተሳካላቸውም። እኛም በያለንበት በጽናት ተዋግተን መክተናል።

አሁን እነሱ ባሰቡት ሳይሆን እኛ ባሰብነው መንገድ እየሄደ ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥ ጦርነቱ ይቋጫል ብለን እናስባለን ሲሉ ገልጸውልናል።

ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አንድ የሚገርማቸው የሚደንቃቸው ነገር አለ። “እኔ አንድ ተራ ኢትዮጵያዊና ተራ ጄነራል ነኝ፣ በአንድ ክላሽ ጥይት ግፋ ቢል ደግሞ በስናይፐር መግደል ይችላሉ፤ ግን የጭካኔያቸው ጭካኔ አርፒጂ ነው የተኮሱብን”።

አርፒጂ የሚባለው መሳሪያ ደግሞ ለታንክ ወይም ለጠንካራ ምሽግ ነው የሚተኮሰው፤ የእኔን ቤት ለማፍረስ ግን አርፒጂ ነው የተኮሱት ሲሉ የከሀዲው ቡድን የጭካኔ ጥግ ምን ያህል እንደሆነ ይናገራሉ ።

እኔ ብሞትም ቤቱ የእነሱና የህዝቡ ንብረት ነው። ለትግራይ ህዝብ ሰላምና ጸጥታ ለቆምኩ፣ ለአገር ሉዓላዊነትና ለህዝብ ሰላም ውድ ህይወቴን ለመስጠት በተሰለፍኩ የክህደታቸው፣ የክፋታቸው ጥልቀት እኔን በአርፒጂና በቦንብ ነው ያጠቁት ሲሉ የድርጊቱን ክፋት ገልጸውታል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከትግራይ ህዝብ ጋር አብሮ እየኖረ ያለ፣ ለህዝቡ የልማት ሥራዎች ወደ ኋላ የማይል፣ በማህበራዊ ድጋፎች የሚሳተፍ፣ ሁልጊዜ በየዓመቱ ለአቅመ ደካሞች የሚያርስ፣ የሚያርም፣ የሚያጭድና አንበጣ የሚከላከል ነው። 

በትምህርት ቤቶች፣ በጤና ጣቢያዎች፣ በመንገድ ግንባታዎች በሚሳተፍ ሠራዊት ላይ ጥቃት መፈጸም የህወሓት ቡድን እወክለዋለሁ ቆሜለታለሁ ለሚለው ህዝብ ደንታ እንደሌለው ያሳያል ይላሉ።

የአገሩን ዳር ድንበር የሚጠብቀውን፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ስብስብ የሆነውን የመከላከያ ሠራዊት ለማውድምና ለማጥፋት ነው ጥቃቱን የሰነዘሩት። እነዚህ ሰዎች ከዚህ በኋላ ስለኢትዮጵያዊነት፣ስለብሄረሰቦችና ባጠቃላይ ስለኢትዮጵያውያን ቢሰብኩ፣ ቢለፈልፉ፣ ቢቀሰቅሱ ማን ጀሮ ይሰጣቸዋል።ምክንያቱም ጥቃቱን በጽናት ለመመከት የተዋደቁት ከኢትዮጵያ ሕዝብ የተወጣጡ ወታደሮች ናቸው ብለዋል።

ጀኔራሉ በ1980ዓ.ም በወቅቱ ኢህዲን ተብሎ የሚጠራውን ትግል የተቀላቀሉ ናቸው። ከዚሁ ዓመት ጀምሮ ደርግ እስኪደመሰስ ድረስ በተደረጉ ውጊያዎች ተሳትፈዋል። ቆቦ አካባቢ በተካሄደው ሰላም በትግል ኦፕሬሽን፤ ሰሜን ሸዋ መራኛ፣ ጁሁርና መራቤቴ አውድ ውጊያዎች ተሳትፈዋል።

በጎጃም ደጀን፣ አምቦ፣ ነቀምት፣ ጅማ፣ ቡሌሆራ (አገረ ማርያም) ሞያሌ ድረስ በዘለቀው አውድ ውጊያ ተሳትፈዋል። በሀረርም ጸረ ሰላም ሀይሎችን በመከላከልና በማጥቃት ዘመቻ ተሳትፈዋል። በሩዋንዳ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ በ1986ዓ.ም ግድጃቸውን በስኬት አጠናቀው ተመልሰዋል።

የሀገር መከላከያ ሠራዊት ሲቋቋምም 20ኛ ክፍለ ጦር መድፈኛ ብርጌድ አንደኛ ሻለቃ አዛዥ ሆነው አገልግለዋል። በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነትም ትምህርታቸውን አቋርጠው በመሄድ ብርጌድ አዛዥ በመሆን በጾረና፣ በባድመ፣ በሽራሮ አዲኋላ ግንባር ተሳትፈዋል።

አሁንም በዳንሻ ከተማ በትግራይ ልዩ ኃይል የተካሄደውን ከበባና ሶስት ቀናት የዘለቀ ጥቃት ወስን ወታደሮችን መርተውና አዋግተው በተጨማሪ የመከላከያ ሠራዊት ዕገዛ መከላከሉን በድል አጠናቀው የማጥቃቱን ተልዕኮ በድል እየተወጡ ይገኛሉ። ©ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የተወሰደ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics

Reader Interactions

Comments

  1. TAYE says

    November 12, 2020 05:19 am at 5:19 am

    I AM PROUD OF B. GENERAL MULUALEM HE MAKE HISTORY !!!! BUT EVEN IF THE WAR WILL OVER THERE IS TPLF TERRORIST ALL THROUGH ETHIOPIAN REGIONS WAITING TO CREATE CIVIL WAR.
    TO MINIMIZE DEATH RATE GOVERNMENT MUST HAVE SEARCH ALL BALK LIST HOMES OUT OF HIDDEN,OPERATION THAT ORGANIZED BY THIS TPLF TERRORIST GROUPS.
    FOREVER VICTORY TO ETHIOPIA DEATH TO HER ENEMY

    Reply
  2. Abraham says

    November 13, 2020 03:58 pm at 3:58 pm

    I salute you my guy , you are my hero and your country is proud of you love you from my soul

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule