• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ ሁለት የመዝናኛ ከተማዎችን ልትገነባ ነው

September 21, 2020 02:16 pm by Editor 1 Comment

ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ የመሆን ግቧ አካል የሆኑ ሁለት የመዝናኛ (ሪዞርት) ከተማዎችን ልትገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ።

በሚኒስቴሩ የቱሪዝም እቅድ ዘርፍ መሪ አቶ አህመድ መሐመድ እንደተናገሩት፤ ከመዝናኛ ከተሞቹ አንዱ የሚገነባው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ነው። ግድቡ ሲጠናቀቅ 70 ገደማ ሰው ሰራሽ ደሴቶች ይኖራሉ። ግድቡ ሲጠናቀቅም በሀገሪቱ ዋነኛው የቱሪስት መዳረሻ ይሆናል።

ሁለተኛው የመዝናኛ ከተማ የሚገነባበት ቦታ የአዋጪነት ጥናት ከተካሄደ በኋላ ይወሰናል ያሉት አቶ አህመድ፤ የመዝናኛ ከተማ ግንባታ የሚከናወነው የግሉ ሴክተርን ጨምሮ በብዙ ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ መሆኑንም ተናግረዋል።

ሪዞርቶችን በግል ባለሀብቶች እንደሚገነባ የተናገሩት አቶ አህመድ፤ የመዝናኛ ከተማዎቹ ሀገሪቱ ከቱሪዝም ዘርፍ የምታገኘው ገቢ ከፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

እንደ አቶ አህመድ መሐመድ ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ በ2022 ኢትዮጵያን የቱሪስቶችን ቁጥር 7 ነጥብ 4 ሚሊዮን ለማድረስ እቅድ የያዘች ሲሆን ፣ ከቱሪዝም ዘርፍ ብቻ የሚገኘውን ገቢ 23 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ አቅዳለች።

በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ውስጥ በነባር 40 መዳረሻዎች ላይ እሴት በመጨመር በመላ አገሪቱ 59 አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን ለማልማት እቅድ መያዟን የተናገሩት አቶ አህመድ፤ ሚኒስቴሩ በመጪዎቹ አሥር ዓመታት ውስጥ የፈጠራ ማዕከላት እና የስብሰባ ማዕከላት ግንባታ እንደሚከናወን አብራርተዋል።

እንዲሁም እንደ ፣ሆቴሎች፣ ምግብ ቤቶች፣ ባህላዊ ምግብ እና መጠጥ ቤቶች ያሉ የቱሪስት ለቱሪስት አስፈላጊ የሆኑ ተቋማት ግንባታ በቀጣይ 10 ዓመታት ለማካሄድ በእቅዱ ላይ መያዙን አቶ አህመድ አመልክተዋል።

የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው፤ ከላይ ከተጠቀሱት ተግባራት በተጨማሪ ቅርሶችን እና ታሪካዊ ቦታዎችን ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ ብሎም የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም በመላ አገሪቱ የሚገኙ በርካታ ታሪካዊ ቦታዎችንና ቅርሶችን የማደስ ተግባር በመካሄድ ላይ መሆኑን ገልፀዋል ።

የሰው ኃይልን ፣ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን፣ የመስመር ላይ አገልግሎት አሰጣጥን ፣ ዲጂታል ማድረግን እና የቱሪስት ገበያዎች ብዝሃነትን በማሻሻል በዘርፉ የመዋቅር ሽግግርን ለማምጣት ተጨማሪ ሥራዎች ይሰራሉ ብለዋል።

እንደ ሚኒስትሯ ማብራሪያ፤ ሀገሪቱ በዘርፉ በቀጣይ 10 ዓመታት ለማሳካት ያቀደችውን እቅድ ለማሳካት በአገሪቱ ውስጥም ጥሩ ዕድሎች አሉ። እስካሁን በቱሪስት መዳረሻነት ያልታወቁ የመስህብ ስፍራዎች እና ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ናቸው በማለት መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም የታተመው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News

Reader Interactions

Comments

  1. ራሔል በቀለ says

    September 23, 2020 04:00 pm at 4:00 pm

    ለኦሮሞ ሰፋሪ አመቻችተህ ስራ በመተከል ክልል ያለ ግድብ አማራ ብቻ ሚገደለው ሚስጥሩ ገብቶናል አዎ መጀመሪያ በዚህ 2 አመታት ለመኖር ያብቃን ከዚያ ብናወራ አይሻልም?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule