• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ ሁለት የመዝናኛ ከተማዎችን ልትገነባ ነው

September 21, 2020 02:16 pm by Editor 1 Comment

ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ የመሆን ግቧ አካል የሆኑ ሁለት የመዝናኛ (ሪዞርት) ከተማዎችን ልትገነባ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ።

በሚኒስቴሩ የቱሪዝም እቅድ ዘርፍ መሪ አቶ አህመድ መሐመድ እንደተናገሩት፤ ከመዝናኛ ከተሞቹ አንዱ የሚገነባው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ነው። ግድቡ ሲጠናቀቅ 70 ገደማ ሰው ሰራሽ ደሴቶች ይኖራሉ። ግድቡ ሲጠናቀቅም በሀገሪቱ ዋነኛው የቱሪስት መዳረሻ ይሆናል።

ሁለተኛው የመዝናኛ ከተማ የሚገነባበት ቦታ የአዋጪነት ጥናት ከተካሄደ በኋላ ይወሰናል ያሉት አቶ አህመድ፤ የመዝናኛ ከተማ ግንባታ የሚከናወነው የግሉ ሴክተርን ጨምሮ በብዙ ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ መሆኑንም ተናግረዋል።

ሪዞርቶችን በግል ባለሀብቶች እንደሚገነባ የተናገሩት አቶ አህመድ፤ የመዝናኛ ከተማዎቹ ሀገሪቱ ከቱሪዝም ዘርፍ የምታገኘው ገቢ ከፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

እንደ አቶ አህመድ መሐመድ ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ በ2022 ኢትዮጵያን የቱሪስቶችን ቁጥር 7 ነጥብ 4 ሚሊዮን ለማድረስ እቅድ የያዘች ሲሆን ፣ ከቱሪዝም ዘርፍ ብቻ የሚገኘውን ገቢ 23 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ አቅዳለች።

በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ውስጥ በነባር 40 መዳረሻዎች ላይ እሴት በመጨመር በመላ አገሪቱ 59 አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን ለማልማት እቅድ መያዟን የተናገሩት አቶ አህመድ፤ ሚኒስቴሩ በመጪዎቹ አሥር ዓመታት ውስጥ የፈጠራ ማዕከላት እና የስብሰባ ማዕከላት ግንባታ እንደሚከናወን አብራርተዋል።

እንዲሁም እንደ ፣ሆቴሎች፣ ምግብ ቤቶች፣ ባህላዊ ምግብ እና መጠጥ ቤቶች ያሉ የቱሪስት ለቱሪስት አስፈላጊ የሆኑ ተቋማት ግንባታ በቀጣይ 10 ዓመታት ለማካሄድ በእቅዱ ላይ መያዙን አቶ አህመድ አመልክተዋል።

የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው፤ ከላይ ከተጠቀሱት ተግባራት በተጨማሪ ቅርሶችን እና ታሪካዊ ቦታዎችን ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ ብሎም የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም በመላ አገሪቱ የሚገኙ በርካታ ታሪካዊ ቦታዎችንና ቅርሶችን የማደስ ተግባር በመካሄድ ላይ መሆኑን ገልፀዋል ።

የሰው ኃይልን ፣ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን፣ የመስመር ላይ አገልግሎት አሰጣጥን ፣ ዲጂታል ማድረግን እና የቱሪስት ገበያዎች ብዝሃነትን በማሻሻል በዘርፉ የመዋቅር ሽግግርን ለማምጣት ተጨማሪ ሥራዎች ይሰራሉ ብለዋል።

እንደ ሚኒስትሯ ማብራሪያ፤ ሀገሪቱ በዘርፉ በቀጣይ 10 ዓመታት ለማሳካት ያቀደችውን እቅድ ለማሳካት በአገሪቱ ውስጥም ጥሩ ዕድሎች አሉ። እስካሁን በቱሪስት መዳረሻነት ያልታወቁ የመስህብ ስፍራዎች እና ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ናቸው በማለት መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም የታተመው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News

Reader Interactions

Comments

  1. ራሔል በቀለ says

    September 23, 2020 04:00 pm at 4:00 pm

    ለኦሮሞ ሰፋሪ አመቻችተህ ስራ በመተከል ክልል ያለ ግድብ አማራ ብቻ ሚገደለው ሚስጥሩ ገብቶናል አዎ መጀመሪያ በዚህ 2 አመታት ለመኖር ያብቃን ከዚያ ብናወራ አይሻልም?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule