• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ትልቁ ሽልማታችን የሀገራችን ሰንደቅ ዓላማ በስፍራው ማውለብለብ ነው” ከ190 ሀገራት 2ኛ የወጡት ተሸላሚዎች

October 18, 2024 09:32 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ190 ሀገራት በላይ የተሳተፉበት ዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር በቅርቡ በግሪክ አቴንስ ታካሂዷል፡፡

7 አባላት ያሉት የኢትዮጵያ የፈርስት ግሎባል ቡድን በውድድሩ ተሳትፎ ከዓለም 2ኛ ደረጃ በመያዝ የብር ሜዳልያ ተሸልሟል፤ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ስሟን ማስጠራት ችሏል፡፡

ተማሪዎች የሳይንስ የቴክኖሎጂ የኢንጂነሪንግ እና የሂሳብ እውቀትን በመጠቀም ለአሁናዊ የዓለም ችግሮች ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም መፍትሄ እንዲያመነጩ የተለያዩ እድሎች ይፈጠራሉ፡፡

እድሎችን በመጠቀም የራሳቸውን የቤተሰባቸውን የአከባቢያቸውን የሀገራቸውን እንዲሁም በዓለም ለሚታዩ ችግሮች መፍትሄ ያፈላልጋሉ፡፡

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የሶፎትዌር ኢንጂነሪንግ ተማሪ ዳግማዊ ግሩም የቡድኑ መሪ ሲሆን ስለ ውድድሩ ሲናገር የዘንድሮው ውድድር ትኩረት የወደፊቷን ዓለም መመገብ (Feed The Future) የሚል ቻሌንጅ ነበር፡፡

የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ምግብ ከማምረት እስከ ማጓጓዝ ያለውን ሂደት እንዴት በቴክኖሎጂ መስራት ይቻላል የሚለውን የመፍትሄ ሀሳብ ማስተማሪያ ሮቦቲክስ መስራት ለሁሉም ተወዳዳሪዎች የቀረበ ፈተና እንደነበር ይናገራል፡፡

ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (ሮቦቶችን) በመጠቀም እንዴት ምግብ መማረት እንደሚቻል፤ የተመረተውን ምግብ ወደ ማከማቻ መጋዘን እንዴት ማጓጓዝ ይቻላል? ሮቦቶችን በመጠቀም በግብርን ስራ ላይ የተሻለ ምርታማ መሆን ብቻ ሳይሆን የተመረተውን ምግብ   ወደ መጋዘን በአግባቡ ማጓጓዝ ይቻላል የሚለውን በቴክኖሎጂ አስተማሪ ሮቦት መስራት በመቻላችን 2ኛ ደረጃ መያዝ ችለናል ብሏል፡፡

ከ100 በላይ ኪቶች ያሉት ሮቦት ተበታትኖ ለሁሉም ተወዳዳሪዎች ተላከልን፤ ስራውና ዓላማው አንድ የሆነ ሮቦት ዲዛይን እንድንሰራ ቻሌንጅ ተሰጠን፤ የተላከውን የሮቦት ኪት በመጠቀም በውድድሩ ለማሸነፍ የተሻለና የተለያዩ ዲዛይን በመጠቀም ዓላማውን ማሳካት የሚችል ሮቦት መስራት መቻላቸውን ይናገራል ወጣት ዳግማዊ፡፡

የ18 ዓመቷ ወጣት ፅዮን ፍፁም ከሳፋሪ አካዳሚ የተገኘች የመጀመሪያ ዓመት የዩኒቨርስቲ ተማሪ ናት፡፡ “ውድድሩ አድካሚ ነበር፡፡ መጀመሪያ አከባቢ ባጋጠመን የቴክኒክ ችግር ጥሩ መጫወት ባንችልም ችግሩ ተስተካክሎ በጥሩ ሁኔታ መጫወት ችለናል፤ በልምምድ የሰራነውን በውድድሩ በመድገም ጥሩ ውጤት ማሳየት በመቻላችን 2ኛ ደረጃ መውጣት ችለናል፡፡” ብላለች፡፡

“ሀገራችንን ወክለን በውድድሩ 2ኛ ደረጃ መውጣታችን ሲነገረን በጣም ደስተኞች ነበርን፡፡ ይህም ደስ የሚል ትልቅ ስሜት ፈጥሮብናል፡፡ በሮቦቲክስ ውድድሩ ከዓለም 2ኛ ደረጃ በመውጣት ያገኘነው ትልቁ ሽልማታችን የሀገራችን ሰንደቅ ዓላማ በስፍራው ማውለብለብ ፤ ሀገራችንን በዓለም መድረክ ስሟን ማስጠራት መቻላችን ነው” ብላለች፡፡

ወደፊት ብዙ ሰርታ በውድድሮች በመሳተፍ ሀገሯን ዳግም ማስጠራት እፈልጋለሁ የምትለው ታዳጊዋ በኢትዮጵያ ስለ ሮቦቲክስ ያለው አመለካከት እየተሸሻለ ቢሆንም አሁን ሰፊ ክተቶች አሉ ባይ ናት፡፡ ለዘርፉ ተገቢ ትኩረት መስጠት ከተቻለ ወደፊት የተሻለ ውጤት መምጣት እንደሚቻልም ታምናለች፡፡ ት/ቤቶች፤ መንግስት ለሮቦቶክስ ቴክኖሎጂ ምቹ አውድ ቢፈጠሩ ብቃት ያላቸው ታዳጊዎችን ማፍራት ይቻላል ብላለች፡፡

ኖህ ጌታቸው በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የ4ኛ ዓመት የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ተማሪና የፈረስት ግሎባል ቡድን የቴክኒክ ቡድን መሪ ነው፡፡ ከህፃንነቱ ጀምሮ ለቴክኖሎጂ ለፈጠራ ፍላጎት ያለው ሲሆን ከተሳተፉ 7 አባላት አንዱ ነው፡፡

ስለ ውደድሩ ሲናገር “አራት ኳስ መያዝ የሚችል ሮቦት መስራት ችለናል፡፡ እኛ ማሸነፍ የቻልነው ሆልሞኒክ ድራይቭ የሚባለውን ማለትም የሰራነው ሮቦት እየሄደ እያለ ወደ ፈለገው አቅጣጫ መዞር ሲፈልግ ወዲያው መዞርና ወደ ሁለም አቅጣጫ መሄድ አንዲችል አድርገን ነው የሰራነው፤ በዚህም ጊዜ መቆጠብ ይቻላል፡፡ አብዛኛዎቹ ሌሎች ተፎካካሪዎች የሰሩት ሮቦት 2 ኳስ ነበር የሚይዘው እኛ ግን በአንዴ 4 ኳስ መያዝ የሚችልና ዓላማውን ማሳካት የሚችል አስተማሪ ሮቦት ሰርተናል፡፡ ይህም እንድናሸንፍ በጣም አግዞናል” ብሏል፡፡

በሮቦቲክስ ውድድሩ ከዓለም 2ኛ ደረጃ በመውጣት ያገኘነው ትልቁ ሽልማታችን የሀገራችን ሰንደቅ ዓላማ በስፍራው ማውለብለብ፤ ሀገራችንን በዓለም መድረክ ስሟን ማስጠራት መቻላችን ነው ሲሉ የፈረስት ግሎባል ቡድን አባላት ተናግረዋል፡፡

በአቴንስ በነበራቸው ቆይታ ከ30 ሀገራት 12 ጨዋታዎችን ማድረጋቸውን፤ የፈጠራ አቅማቸውን፤ የተግባቦት ክህሎታቸውን ማሳደግ መቻላቸውን የሚናገሩት የቡድኑ አባላት ወደፊት የሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንጂነሪንግ እና የሒሳብ እውቀትን አጣምሮ በመጠቀም ለተማሪዎች ተደራሽ ማድረግ ዓላማቸው መሆኑን ታናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ተስጥኦና ፍላጎት እያላቸው ግን እድል ያላገኙ ወጣቶች ብዙ ናቸው፤ ለእነዚህ እድል መፍጠር አቅማቸውን በማውጣት ለችግሮች መፍትሄ እንዲዘይዱ፤ በዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች መስራት እንደምንችል ለማሳየት የጀመርናቸውን ጥረቶች  ወደፊት አጠናክረን እንቀጥላለን  ብለዋል፡፡

ሮቦቱ ውስብስብ ቢመስልም ፍላጎት ካለ፤ ትኩረት መስጠት ከተቻለ አይከብድም፡፡ ወደፊት በኢትዮጵያ ሮቦቲክስን ማስፋፋት በውድድሮች ማሳተፍ፤ ሰው ሰራሸ አስተውሎትን እውቀት የሚጠይቅ ስለሆነ ፍላጎት ላላቸው ምቹ ሁኔታ ቢፈጠር ጥሩ ነው የሚል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ሮቦት ሲባል የመጫወቻ ብቻ ይመስላቸዋል፡፡ ስለ ሮቦቲክስ ያለው ግንዛቤ አነተስኛ ነው፡፡ ሮቦቲክስ ሰዎች እንደሚያስቡት መጫወቻ ሳይሆን ትልቅ ችግር ፈቺ የሆነ ኃላፊነት የሚጠይቅ ቴክኖሎጂ ነው፡፡ ስለ ሮቦቶ ሁሉም ሰው ትክክለኛ ግንዛቤ መፍጠር ይገባል፡፡ መንግስትም ለዘርፉ እድገት የጀመራቸውን የመሰረት ልማት ግንባታ አጠናክሮ ከቀጠለ ወደፊት የተሻለ ውጤት መምጣት ይቻላል  ብለዋል የቡድኑ አባላት፡፡ (ኢቢሲ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: Ethiopia AI, Ethiopia First Global, Ethiopia Robotics, Feed The Future

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule