• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር “እየቀለለ” ነው!

July 6, 2016 08:25 am by Editor 5 Comments

ጠቅላላ ወጪው 475 ሚሊዮን ዶላር እንደሆነ የተነገረለት የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር በብልሽት ምክንያት ግማሽ ያህል ባቡሮቹ እንደማይሰሩ ተነገረ፡፡ የባቡሩ ፕሮጀክት ከመጠናቀቁ በፊት ሥራው እንዲጀመር ህወሃት/ኢህአዴግ ግፊት አድርጎ ነበር፤ የቀላል ባቡር ፕሮጀክት የፖለቲካ ውሳኔ ነው፤ ቀላል ባቡሩ “እየቀለለ ነው” ተብሏል፡፡

ማክሰኞ ዕለት የተሰማው ሸገር ሬዲዮ ስማቸውና ድምጻቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ መረጃ አቀባዮቼ አደረሱኝ ባለው መሠረት ከተጀመረ ዓመት ያልሞላው የአዲስ አበባ የቀላል ባቡር ሥራ “እየቀለለ” መሆኑን ተናግሯል፡፡ ለአገልግሎት ከተመደቡት 41 ባቡሮች ውስጥ በሥራ ላይ የሚገኙት 28ቱ ብቻ መሆናቸውን መረጃ አቀባዮቹን ጠቅሶ ሬዲዮው አስረድቷል፡፡ ሃያ አንዱ ባቡሮች በብልሽት ምክንያት አብዛኛውን ጊዜያቸውን የሚሳልፉት በጥገና እንደሆነ፤ የመለዋወጫ ችግር ደግሞ ይበልጥ ሁኔታውን እንዳባባሰውና ለዚህም ተጠያቂው ኃላፊነቱን የፈረመው የቻይናው ኩባንያ ሲኤንአር መሆኑን አክሎ አስታውቋል፡፡train

በጉዳዩ ላይ የተምታታ ምላሽ የሰጡት የህወሃት/ኢህአዴግ ሹመኛ ደረጀ ተፈራ 21ዱ ባቡሮች አገልግሎት እንደማይሰጡ አልካዱም፡፡ ግን የቆሙት ባቡሮች ምክንያታቸው ብልሽት ብቻ ሳይሆን ለመጠባበቂ ነው በማለት ከተናገሩ በኋላ ብልሽት ያለባቸውን ደግሞ ህወሃት/ኢህአዴግ ለሰው ህይወት በጣም የሚያስብና የሚጠነቀቅ በመሆኑ ለአገልግሎት እንዳይወጡ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡

ሹመኛው አክለውም ባቡሮቹ የማይሠሩት የተጠቃሚ ቁጥር በሚያንስበት ጊዜ እንዲሁም የኤሌክትሪክ አቅርቦት በማይኖርበት ወቅት መሆኑን አልሸሸጉም፡፡ “ለመጠባበቂያ ነው የቆሙት” በማለት አስቀድመው የሰጡትን ሃሳብ በመቃወምም የባቡሩ ተጠቃሚ ብዙ እንደሆነና አቅርቦቱና ፍላጎቱ ባለመመጣጠኑ ባቡሮቹ ከመጠን በላይ በመሥራታቸው ለጥገና መጋለጣቸውን ተናግረዋል፡፡ የተሳፋሪውን መጠንም ሲገልጹ “የሚጠቀመው ሰው በጣም ብዙ ነው” ያሉት ሹም “ባቡሩ ቶሎ ወደ አገልግሎት እንዲገባ ግፊት እንደነበር” በመናገር የግፊቱ እና የችኮላው መንስዔ የህዝቡ ፍላጎት እና “የእኛ ግፊት” ነበር በማለት ዋንኛው ተጽዕኖ “ሌጋሲ፤ ውርስ፤ ህዳሴ፤ የሙት መንፈስ፤ …” መሆኑን ከመጥቀስ በመቆጠብ በደምሳሳው አልፈውታል፡፡

ሬዲዮው ባገኘው መረጃ መሠረት የባቡሩ ውል ከቻናው ሲኤንአር ኩባንያ ጋር ሲፈረም የህወሃት ሹሞች ኩባንያው መለዋወጫም እንዲያቀርብ በስምምነቱ ላይ ኩባንያውን አለማስፈረማቸው እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ምናልባት እንደ ውጫሌ ውል የቻይንኛውና የአማርኛው (ወይም የህወሃት ሰዎች እንዲገባቸው የተጻፈበት ቋንቋ) ቅጂ ካልተለያየ በስተቀር እንዲህ ዓይነቱ እጅግ በርካታ ገንዘብ የፈሰሰበት ፕሮጀክት ላይ የመለዋወጫ ዕቃ ውል መፈጸም ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም በማለት አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የባቡር ኮርፖሬሽኑ ለጥገና ብሎ ያስቀመጠው ወይም የበጀተው አለመኖሩ የቀላል ባቡሩን ቅለት የሚሳይ ብቻ ሳይሆን በግልጽ የፖለቲካ ውሳኔ የተፈጸመ ፕሮጀክት ለመሆኑ አብሮ ይነገራል፡፡l rail

ገና ከጅማሬው ታላቅ ገቢ ያስገኛል፤ የከተማዋን የትራንስፖርት ችግር ያስወግዳል፤ በአንድ ጉዞ ከ300 በላይ ተጓዦችን ያሳፍራል፤ በሰዓት 80ኪሜ መብረር ይችላል፤ ከምስራቅ አፍሪካ ብቸኛው ነው፤ በአፍሪካ ከሚጠቀሱት ሰባት የከተማ ባቡሮች የዘመነው ነው፤ … ተብሎ ከበሮ የተደለቀለትና ፈንዲሻ የተነሰነሰለት ቀላል ባቡር አንድ ዓመት ሳይሞላው እንዲህ እንደ ስሙ መቅለሉ የህወሃት/ኢህአዴግ ማንነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው በማለት አንድ የጎልጉል አስተያየት ሰጪ በላኩልን መልዕክት ላይ አስታውቀዋል፡፡

በአንድ ጀምበር ታላላቅ ፕሮጀክቶችን በመጀመር የታላቅነትን ነጋሪት እየመታ የሕዝብን ቀልብ ለመሳብ የሚፈልገው ህወሃት/ኢህአዴግ የከተማ ዜጎችን ቁም ስቅል እያሳየ ለከተማ ነዋሪዎች አስባለሁ ማለቱ አብሮ የማይሄድ እንደሆነ የሚናገሩ ወገኖች፤ በርግጥ ህወሃት/ኢህአዴግ ለከተማው ህዝብ የሚያስብ ከሆነ በክረምት እመጫቶችን ሳይቀር ከጨቅላ ህጻናቶቻቸው ጋር ከደሳሳ ጎጇቸው ማፈናቀሉን ያቁም፤ በሞትና በህይወት ላይ ባለ በሽተኛ ማላገጡን ትቶ ለህክምና ነጻነት ይስጠው፤ … እነዚህን ቀላል ነገሮችን ያድርግልን በማለት አንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ከተዘረጋላቸው የሃዲድ መስመሮች እያፈተለኩ እንደሚወጡ የሚነገርላቸው ባቡሮች እንቅፋት እንዳመታቸው ሃዲዶቹ እንደሚጠረጉና በባቡር ቫዝሊንም (ግራሶ) እንደሚለሰልሱ ሬዲዮው ጨምሮ ተናግሯል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    July 6, 2016 04:08 pm at 4:08 pm

    Golgul eyekelele new

    Anti Ethiopian news site .

    Reply
  2. gud says

    July 6, 2016 04:09 pm at 4:09 pm

    You fools . You criticize everything ,then the public see u as clowns .

    Reply
  3. አሳፋሪዎች says

    July 6, 2016 05:54 pm at 5:54 pm

    ምነው ኢሃድግም እንደ ባቡሮቹ ቢወላልቅልን ምን ነበረበት።

    Reply
  4. tesfai habte says

    July 13, 2016 03:25 pm at 3:25 pm

    ለኢትዮጵያ ህዝቢ ለማታለል እጂ ለስራ እውነተኛ ወይም ለሃገር ግንባታ ተብሎ የተሰራ ኣለመሆኑ የተረጋገጠ ነው።

    Reply
  5. ሸመልስይማም says

    July 14, 2016 12:58 pm at 12:58 pm

    መነዉ አንደ ሊቢያው መአመር ጋዳፊ ህወሀት ኢህአዴግ ቢፈራርስ ፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ደስታ ነበር ፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule