አዲሱ የሃይማኖት ህግና የሃገሪቱ ህገመንግስት (በሰለሞን) መንግሥት ሕገ-መንግስቱን ሊያከበር ይገባል! (ከእምነት ቤቶች) በጉዳዩ ላይ እንድንወያይ ስንጠየቅ ይህ የሃገረቱን ህገመንግስት ይቃረናል እኛም እዚህ ተወክለን የመጣነው ለሌላ ጉዳይ እንጂ በህግ ላይ ህግ ለማውጣት አይደለም ብለን አጀንዳው እንዲመለስ አድርገናል ፡፡(ከተስብሳቢዎች አንዱ) በስራ ላይ የዋለውን እንደ አዲስ ለማጸደቅ በተዘጋጀው ረቂቅ ላይ ውይይት እንዲደረግ የእምነት ተቌማት የጋራ ጉባኤ ላይ ቀርቦ ነበር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አይመለከተኝም ብላ ወጥታ ነበር ቀጥሎም የኢትዮጵያ እስልምና ጽህፈት ቤትም አይመለከተኝም ብሎ ነበር፡፡ በመጨረሻምወንጌላዊያን ይህ ህግ እነርሱ ላይ ተፈጻሚ ሆኖ የቆየ ቢሆንም በህግ መልክ እንደገና ሲቀርብ ግን ተገርመውበታል፡፡ “ኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መርጠው በላኳቸው … [Read more...] about አዲሱ የሃይማኖት ህግና የሃገሪቱ ህገመንግስት
Archives for January 2013
ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም “በኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኛ የለም”
አስመራ ለመሄድና ለመደራደር ፈቃደኛ ከሆኑ የመድረክ ተወካዮች እርሳቸው ቢሮ ድረስ በመሄድ እንዲደራደሩ እንዲፈቅዱ ተጠይቀዋል። በኢትዮጵያ ያለውን እስርና እንግልት፣እንዲሁም “የውንጀላ” ቅንብር ከንጹህ ህሊና እንዲመረምሩ በትህትና የልመና ያህል ቀርቦላቸዋል። በምትሰጠዋ አጭር የመናገሪያ ደቂቃ መነጋገሪያ የሚሆኑ ጥያቄዎች ተሰንዝረዋል። የእያንዳንዱን ቤት የሚያንኳኳ ሰብአዊነትን የሚፈታተን ጥያቄዎች በማንሳት አቶ ግርማ ሰይፉ ተሳክቶላቸዋል። በትህትና ያቀረቡዋቸው ጥያቄዎች በተለይም ዶ/ር ደብረጽዮንን በተደጋጋሚ ሲስቁ እንድንመለከት ከመጋበዙ በላይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ነጻነት የተሞላው መልስ አልተሰጠባቸውም። አቶ ሃይለማርያም ቀሪዋን ሁለት ዓመት ለመጨረስ ውለታ አስቀማጭ በመሰሉበት የፓርላማ ውሏቸው ፖለቲካ ውሸትና ክህደት የሚበዛበት የአይነ ደረቆች ጨዋታ ነው ቢባልም፣ እሳቸው ግን … [Read more...] about ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም “በኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኛ የለም”
ወሬ ይገድላል
በጎርጎሪያኑ የቀን መቁጠሪያ ለምትገለገሉ ሁሉ መልካም አዲስ ዓመት!! በአዲሱ ዓመት ከራስ ጋር በመታረቅ፣ ከህሊናና ከእዕምሮ ባርነት በመላቀቅ፣ ከይሉንታ ጥብቆ ውስጥ በመውጣት፣አካሄድን ለማሳመር ይቻል ዘንድ የተጠቀለለውን አሮጌ ዓመት ትምህርት ማድረግ ታላቅ ጉዳይ ነው። አዲሱ ዓመት ከባከኑት ዓመታቶች ጋር ተዳምሮ እንዳያጎብጠን፣ ተስፋችንን እንዳይበላውና ወደ ከፋ የፖለቲካ መሰላቸት ውስጥ እንዳይከተን መጠንቀቅ ደግሞ ከሁሉም በላይ ወሳኝ ይመስለናልና ከከንቱና የማያንጽ ወሬው ቆጠብ፣ ከተግባሩ ጨመር እናድርግ!! ወሬ ይገድላል እንዲሉ!! ይሉኝታን እንቅበር ባለፉት ዓመታት የይሉኝታ ፖለቲካ ጉዳት አድርሷል። በይሉኝታ በመነዳት የማይረሳ ኪሳራ ተመዝግቧል። በይሉኝታ ብቻ የደረሰብን የፖለቲካ ጠባሳ ሰምበሩ በያንዳንዳችን ሰውነት ላይ ይታያል። በተፎካካሪ ፓርቲዎችና ለለውጥ በተነሱ ፓርቲዎች … [Read more...] about ወሬ ይገድላል
የማፍረስ አባዜ
በአለፉት ሃያ አንድ ዓመታት፣ በተለይም ከ1997 ዓ.ም. ወዲህ፣ የወያኔ/ኢሕአዴግ አገዛዝ ልዩ መታወቂያው ያደረገው እያፈረሱ መገንባትን ነው፤ ማፍረስ ቀላል ሥራ ነው፤ ጭንቅላትም፣ ማሰብም አይጠይቅም፤ ልብም፣ ስሜትም አይጠይቅም፤ የሚጠይቀው የዝሆን አካልና ጉልበት ብቻ ነው፤ አንድ ቤተሰብ ስንት ዓመት በዚያ ቤት ውስጥ ኖረ? ጎረቤቶች ምን ዓይነት ትስስር አላቸው? በማኅበር፣ በእድር፣ በዝምድና በቤተ ክርስቲያን ወይም በቤተ መስጊድ፣ በመቃብር፣ በሥራ፣ በአጠቃላይ የእያንዳንዱ ሰው ኑሮ ከልደት ጀምሮ የተፈተለበትና የተደራበት ውስብስብ የኅብረተሰብ አካል መኖሪያ ነው፤ ይህንን አካል ለማፍረስ ትንሽ ጭንቅላትና ግዙፍ ጡንቻ ያለው አይቸግረውም፡፡ መኖሪያ ቤቶችን ማፍረስ፣ መቃብሮችን ማፍረስ፣ የንግድ ድርጅቶችን ማፍረስ፣ ትምህርት ቤቶችን ማፍረስ፣ … ማፍረስ… ማፍረስ… ማፍረስ! ሳያለቅሱ … [Read more...] about የማፍረስ አባዜ