• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኔና አንቺ … ፩

October 3, 2013 09:14 am by Editor 1 Comment

መቼም እኔና አንቺን ሲፈጥረን

ጉዳችሁ አይለቅ ያለን ነን

ይሄው ደግሞ ተሰደንም

ልንስማማ አልደፈርንም።

ሳትሰሚኝ አጣጥመሽ

እኔም ያንቺን ሳላውቅልሽ

መግባባቱ እንዳቃተን

በየአቅጣጫው ተበታትነን

ስንፋተግ ዕድሜ ገፋን።

እውነታውን ስንሸሸው፣ መወያየት ስንፈራ

ቀለብ ሆነን ሀሜት ጉራ።

በይ ተይው ግዴለም፣ ድሮውንም ሲፈጥረን

ጉዳችሁ አይለቅ ያለን ነን።

ለነገሩ ትተነውስ ወዴት ልንደርስ

ግደለሽም እኛው ደፍረን እንዋቀስ

የዕለት የዕለቱን ትተነው

ዘላቂውን እንመርምረው።

የጋራ ችግራችንን ተነጋግረን

በጋራ እንፈታለን እያልን

በአፍ ብቻ ስንወተውት

ከልብ አጣን ስምምነት።

ስለሀገሬ ስለሀገርሽ

አንቺም ስሚኝ፣ እኔም ልስማሽ!

የማተያት፤ የማልተዋት

የጋራችን አንድ ሀገር ናት።

ታዲያ ይሄንን እያውቅን

በድርጅት ተከፋፍለን

እላይ ላዩን ታጋይ መስለን

ውስጥ ለውስጥ ተሸዋውደን

“በእከክልኝ ልከክልህ” ተዘማምደን

እንኳን ካለው ከጎናችን

ጸበኛ ሆ’ን ከህሊናችን።

የጠላታችንን ጠላት፣ ወዳጅ ማድረግ

እንቢ ብለን በማፈግፈግ

እሱ ራሱ ተስፋ እንዲቆርጥ

እንጥራለን ለመበጥበጥ

ይሄን አውቀን በአዲስ መንፈስ

ካልፈታነው ያለንን ቀውስ

ከቶ አንችልም የትም ልንደርስ።

ከአፍ ብልጠት ሳትቆጥሪብኝ

ማነህ? ብለሽ ሳታይብኝ

እንደ አባቶች በእርጋታ፣ እንደ እናቶች በጽሞና

ተወቃቅሰን እንቃና

ህዝብ ማለት እኮ-እኔና አንቺ ነን

ሀገርም ማለትም እኛ ነን።

ሀገር ሀገር ብንላት

በምላሳችን ጫፍ ለጥፈናት

አናድናትም ከጥፋት

እስቲ እንተወው አልልሽም ይሄንንስ

ትተነውስ ወዴት ልንደርስ?

ሌላ ሀገር እኮ ቢኖሩት

ያስጨንቃል የራስ እጦት

አዎን! ችሎ ማደር ይባላል

ችሎ ማደር ይቻላል

ሀገር ካልኖረ ችሎ፣ ታድሮስ የት ይገባል?

ይሄው! በትግሉ ጎራ ብንኮለኮልም

እኔና አንቺ ጠርተን አንጠራም

እርስ በእርስ ተቆራቁዘን

ተኮራርፈን ተሰዳድበን

ስም መግደያ ሰይፍ መዘን

ስንቱን ጥለን ጨፈጨፍነው

ስንቱን ሰቅለን አወረድነው

እኔና አንቺ ከመጣብን

ምን ያስዋሻል እንደዚህ ነን።

በይ! እንፍታው በንግግር

እንድንድን ከዚህ ችግር

እስከመቼ ተፈራርተን

ተባባሉ መባል ጠልተን

እውነታውን አንሸፍን

ድንገት እንኳን ቢሆነን ፈውስ

ተገጣጥመን እንዋቀስ።

አንዴ ወጥተን ሥልጣን ላይ

የልጅ ልጆች እዛው ሳናይ

እኔና አንቺን የሚነካን

ወያኔ ነው ውረድ ካለን።

የኔና ያንቺ ሥልጣን አቅም

ከልጆች መብት ብዙ አያንስም

ብናጠፋስ ማን ተናግሮን

እንዳላየ ነው የሚያልፈን

ይሄን ይሄን ካላረምን

ገዚው ፓርቲ የሚበልጠን

ልብ ብለን ካስተዋልነው

በሚንስትር ብቻ እኮ ነው።

እንተወው አልልሽም ይሄንንስ

እኔና አንቺው እንዋቀስ

መወቃቀስ ለህሊናው ላደረ ሰው

እንደ እንቆቆ መዳኒት ነው

ይሄን አውቀን አምነንበት

መራሯን ቃል እንጨልጣት

ካለን ሕመም ለመፈወስ

ደግመን ደግመን እንዋቀስ

ግድ የለሽም ገጽታሽን አታጥቁሪ

አንገትሽን  አታዙሪ

ለሰው ያሉትን – ለኔ ብሎ መስማት

ይጠቅማል እንጂ የለውም ጉዳት።

በይ! እንግዲህ እንዋቀስ፣ ብለን ካልን

ስህተታችን ካስተማረን፤

ትንሽ ሲገኝ የምንኮራ

ወሬ ሰምተን የምንፈራ

በገዢና ተገዢ አይነት

በኔ አውቃለሁ ግትርነት

በተበለጥኩ ምቀኝነት

ተተብትበን ምንራኮት

የጠራ አቋም ያልጨበጥን

የማንፈትሽ ውስጣችንን

እኛን ጥለን ሌላ ምንጥል

በግማሽ ልብ ምንታገል

መወያየት አስፈርቶን

አሉባልታ የተጫነን

ምን ያስዋሻል፣ እኔና አንቺ እንደዚህ ነን።

(ወለላዬ ከስዊድን welelaye2@yahoo.com)

 

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gebremeskel degu says

    October 8, 2013 11:39 am at 11:39 am

    work for immdiate change with the collaboration of the society specialy with higer education institution students.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule