• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ይብላኝ ወንድሜ፣ ላንተ ይብላኝ!

December 18, 2019 09:41 pm by Editor 1 Comment

(ወለላዬ ከስዊድን)

ስንቱን ጉድ ይኾን የምታልፈው? ስንቱ ጉድ ይኾን የሚያልፍህ?
ለተነሳህበት ዓላማ፣ ለአንድነት፣ ለመደመር፣ ለብልጽግና የሰላም ጉዞህ።
ስንት ውትብትብ ይኾን የምትፈታው
ተናግረህ ምታሳምን – ተሻግረህ ምታሻግረው
እየሠራህ ላለኸው ላንተ ይቅርና ለእኔ ደከመኝ ያንተ ጣር፣
እንዴት ይኾን? የአንድ ቀን ውሎህ? እንዴት ይኾን? የአንድ ቀንህ አዳር
ለዘመናት የተቆለለ የአገር ጉድ አንተ ላይ ወድቆ ተከምሮ
ውሎ ሲያድር ሸክምህን እየጨመረው ከሮ
አላሠራ ቢልህም አላረፍክ – ይኸው ሥራህ ጎልቶ ወጣ
አዳዲስ ነገር ይዞ ነፍሰ ሥጋ ጨብጦ መጣ
ግን ይብላኝልህ ወንድሜ አይችሉ መቻል ለወደቀብህ
ሐሜት፣ ጥርጣሬ፣ ተንኮል፣ ምቀኝነት፣ ክዳትና መሰሪነት ላከሰለህ
እኔማ ምን ልረዳህ ከመብሰልሰል ከማሰብ በላይ አቅም የለኝ
ስደት አርቆ ያሰረኝ
ሐሳብ አመንምኖ ያኖረኝ
አንድ ብኩን አልሞት ባይ ነኝ።
አሁንማ ተስፋ ቆረጥኩ
በጽሞና ልኖር አሰብኩ
ፖለቲካው ተምታታብኝ
አካሔዱ ጠጠረብኝ
የሰው ሥራው ራቀብኝ
አመስግኘው ጨርሼ፣ አድሬ ሳልመጣ
ቃሌ በክህደት ቀርሽቶ ምርቃቴ እፌቴ ሲገረጣ
ስንት ግዜ አየሁ ስንት ግዜ ትዝብት ዋጠኝ
ስንት ጊዜ አሳቀቀኝ ስንት ግዜ አሳፈረኝ
ወንድምዬ ይብላኝ ላንተ፣ ላንተ ይብላኝ
እንደው ግን ለነገሩ የሰው ልጅ እንዲህ ነው ወይ ለካ
ሥልጣን የማይበቃው በተደረገለት የማይረካ
በቀለለለት ቁጥር ተጨመረብኝ ብሎ የሚያማርር
መሪውን በቁልቢጥ የሚሰፍር
ወንድሙን ለዕለት ውሎ የሚገድል
እንዲህ ነው እንዴ የኢትዮጵያዊነት የማስተሳሰሪያው ውል
ይኼን ነው እንዴ ከዘር ግንዱ የወረሰው
ይኼን ነው እንዴ ዓይቶ ሰምቶ ያደገው
ይሄን ሳስብ ያንተ ብርታት ሁሉን አስንቆኝ
እንደገና ነፍስ ዘርቶ አስነስቶኝ
ተስፋ ሠጥቶ ያውለኛል
ያንተ ነገር ግን ያሳሳኛል
የጉድ አገር ገንፎ እያደር ይፋጃል እንዲሉ
የኛም ጣጣ በረደ ስንል መጋሉ
ያሳስበኛል ላንተና ለአገር
ውጥንህ ተበላሽቶ መና ሆኖ እንዳይቀር
ይኼው ኢትዮጵያን ከዳበስካት ከመጣህላት ጀምሮ
እውነትና ውሸት ተስፋና ፍርሃት – አንድ ላይ ተከምሮ
በአስመሳዩ አዋሻኪው አሾክሻኪው
በአውደልዳዩ አጎብዳጁ ወሬ ነፊው
በሥልጣን ጥም በናወዘው
የዘር ልክፍት ባሳበደው
አገር እየተናጠች እየተላጋች ብታድርም
ያንተ ሥራ አልነጠፈም
ቀን በቀን እየተቃጠልክ እየከሰልክ
ስንቱን ፈውሰህ ስንቱን አዳንክ
ስንቱን ለምነህ እርቅ አወረድክ
ስንት ከቤቱ አግብተህ አሳደርክ
ያም ሆኖ ይብላኝልህ ላንተ፣ ነጋ ስትል ለሚጋርድህ ጭለማ
አለኝ ያልከው ለሚርቅህ ለሚጠነሰስብህ አድማ
ግን ማን ይመንህ በእጅህ ሰይፍ ሳትጨብጥ – ግዳይ ጥለህ ሳታቅራራ
አገር የለመደበትን አስጥተህ መች እሺ ይልሃል ስለ ፍቅር ብታወራ
ሰላም ፍቅርና ተስፋ፣ ለካ አያምርብንም ጃን
ይኼው ደም የለመደው እጃችን
እያጋደለ፣ እያጫረሰ ያውለናል
መተማመንና አንድነትን ነስቶናል
ያንተም እድልህ አልቀና አለ፣ መከራው ችግሩ እያደር ባሰ
ለሰላም ያልከው ለጥላቻ፣ ለፍቅር ያልከው ለጸብ ተነሳሳ፣
እርስ በእርስ ተጫረሰ
ከጎሬው ወጥቶ ስንቱ ደነፋ ስንቱ ዱላ ቀሰረ
ስንቱ በጠራራ ፀሐይ አበደ ስንቱ ቀን ለቀን ሰከረ
ስንቱ በተኛበት ተገደለ
ስንቱ ከኖረበት ተፈናቀለ
ይኼን ሁሉ መከራ እላይህ ላይ ተሸክመህ
ያላሰብከው ተፈጽሞ ሆኖ እያየህ
እንዴት ይኾን ውሎህ፣ እንዴት ይኾን እኮ አዳርህ
መቼ ይኾን ባፍህ ‘ሚዞር የለት ጉርስህ
ወንድምዬ! ይብላኝ ላንተ ይብላኝልህ
ሐውልት ብታቆም መርገምት፣
አንድነት ብትፈጥር ውግዘት፣
አገር ብታጸዳ ሹፈት፣
እርቅ ብታወርድ ቅጥፈት፣
ሆኖ ሲወራብህ መልኩን ለውጦ ሲቀርብልህ
ወንድምዬ ምን ተሰማህ?
የዘመናትን ግፍና በደል
በአንድ ግዜ ነቃቅለህ ለመጣል
አገር እንድታድግ ነፃነት ከአጥናፍ አጥናፍ እንድታበራ
ሕዝብ በአንድነት ተደምሮ እንዲሠራ
ያ’ረከውን ምንም እኛ ባንመሰክር ባናወራ
ከአገር አልፎ ዓለም ሰምቶት
ጥበብህን አውቆ አድንቆት
ስምህን ከአድማስ አድማስ እየጠራ አጉልቶ እያየህ
ከትልልቆቹ ተርታ አሰልፎ ሽልማት አሸከመህ
ያም ሆኖ ወንድምዬ ስንት ይኾን ገና የሚቀርህ
ለተነሳህበት ዓላማ የከፈልከው ገና ደግሞ ‘ሚያስከፍልህ
ብዬ እያሰብኩ የአገሬና ያንተ ነገር የሚጨንቀኝ
አንድ አንተኑ የምከተል ሥራህ ጉዞህ የሚገባኝ
ከሩቅ ኾኜ የምታዘብ ስደት ውጪ የጠፈረኝ
ለፍቶ ሠሪ ማስኖ አዳሪ የአገር ልጅ ነኝ
አንተ ግና የስንቱ ዐመል የጠበሰህ፣ ሸክሙ ከብዶ የተጫነህ
ትልቅ ሐሳብ እቅድ ያለህ የአገር ጉዳይ የሚያበርህ
ወጀብ ጎርፉ የሚንጥህ፣ ወዲያ ወዲህ የሚያላጋህ
ብዙ ገና ገና ብዙ የሚቀርህ፣
እረፍት የለሽ ውድ ወንድሜ፣ ይብላኝ ላንተ ይብላኝልህ!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Akalu Tadesse says

    December 27, 2019 11:19 pm at 11:19 pm

    Thank you for speaking out my feelings about the very challenging and demanding environment in which Dr. Abiy is leaving each second. We need to pray to god to give him energy , patience and moreover guide him more. Thank you again Wolelaye. I always liked your poems.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule