• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ይብላኝ ወንድሜ፣ ላንተ ይብላኝ!

December 18, 2019 09:41 pm by Editor 1 Comment

(ወለላዬ ከስዊድን)

ስንቱን ጉድ ይኾን የምታልፈው? ስንቱ ጉድ ይኾን የሚያልፍህ?
ለተነሳህበት ዓላማ፣ ለአንድነት፣ ለመደመር፣ ለብልጽግና የሰላም ጉዞህ።
ስንት ውትብትብ ይኾን የምትፈታው
ተናግረህ ምታሳምን – ተሻግረህ ምታሻግረው
እየሠራህ ላለኸው ላንተ ይቅርና ለእኔ ደከመኝ ያንተ ጣር፣
እንዴት ይኾን? የአንድ ቀን ውሎህ? እንዴት ይኾን? የአንድ ቀንህ አዳር
ለዘመናት የተቆለለ የአገር ጉድ አንተ ላይ ወድቆ ተከምሮ
ውሎ ሲያድር ሸክምህን እየጨመረው ከሮ
አላሠራ ቢልህም አላረፍክ – ይኸው ሥራህ ጎልቶ ወጣ
አዳዲስ ነገር ይዞ ነፍሰ ሥጋ ጨብጦ መጣ
ግን ይብላኝልህ ወንድሜ አይችሉ መቻል ለወደቀብህ
ሐሜት፣ ጥርጣሬ፣ ተንኮል፣ ምቀኝነት፣ ክዳትና መሰሪነት ላከሰለህ
እኔማ ምን ልረዳህ ከመብሰልሰል ከማሰብ በላይ አቅም የለኝ
ስደት አርቆ ያሰረኝ
ሐሳብ አመንምኖ ያኖረኝ
አንድ ብኩን አልሞት ባይ ነኝ።
አሁንማ ተስፋ ቆረጥኩ
በጽሞና ልኖር አሰብኩ
ፖለቲካው ተምታታብኝ
አካሔዱ ጠጠረብኝ
የሰው ሥራው ራቀብኝ
አመስግኘው ጨርሼ፣ አድሬ ሳልመጣ
ቃሌ በክህደት ቀርሽቶ ምርቃቴ እፌቴ ሲገረጣ
ስንት ግዜ አየሁ ስንት ግዜ ትዝብት ዋጠኝ
ስንት ጊዜ አሳቀቀኝ ስንት ግዜ አሳፈረኝ
ወንድምዬ ይብላኝ ላንተ፣ ላንተ ይብላኝ
እንደው ግን ለነገሩ የሰው ልጅ እንዲህ ነው ወይ ለካ
ሥልጣን የማይበቃው በተደረገለት የማይረካ
በቀለለለት ቁጥር ተጨመረብኝ ብሎ የሚያማርር
መሪውን በቁልቢጥ የሚሰፍር
ወንድሙን ለዕለት ውሎ የሚገድል
እንዲህ ነው እንዴ የኢትዮጵያዊነት የማስተሳሰሪያው ውል
ይኼን ነው እንዴ ከዘር ግንዱ የወረሰው
ይኼን ነው እንዴ ዓይቶ ሰምቶ ያደገው
ይሄን ሳስብ ያንተ ብርታት ሁሉን አስንቆኝ
እንደገና ነፍስ ዘርቶ አስነስቶኝ
ተስፋ ሠጥቶ ያውለኛል
ያንተ ነገር ግን ያሳሳኛል
የጉድ አገር ገንፎ እያደር ይፋጃል እንዲሉ
የኛም ጣጣ በረደ ስንል መጋሉ
ያሳስበኛል ላንተና ለአገር
ውጥንህ ተበላሽቶ መና ሆኖ እንዳይቀር
ይኼው ኢትዮጵያን ከዳበስካት ከመጣህላት ጀምሮ
እውነትና ውሸት ተስፋና ፍርሃት – አንድ ላይ ተከምሮ
በአስመሳዩ አዋሻኪው አሾክሻኪው
በአውደልዳዩ አጎብዳጁ ወሬ ነፊው
በሥልጣን ጥም በናወዘው
የዘር ልክፍት ባሳበደው
አገር እየተናጠች እየተላጋች ብታድርም
ያንተ ሥራ አልነጠፈም
ቀን በቀን እየተቃጠልክ እየከሰልክ
ስንቱን ፈውሰህ ስንቱን አዳንክ
ስንቱን ለምነህ እርቅ አወረድክ
ስንት ከቤቱ አግብተህ አሳደርክ
ያም ሆኖ ይብላኝልህ ላንተ፣ ነጋ ስትል ለሚጋርድህ ጭለማ
አለኝ ያልከው ለሚርቅህ ለሚጠነሰስብህ አድማ
ግን ማን ይመንህ በእጅህ ሰይፍ ሳትጨብጥ – ግዳይ ጥለህ ሳታቅራራ
አገር የለመደበትን አስጥተህ መች እሺ ይልሃል ስለ ፍቅር ብታወራ
ሰላም ፍቅርና ተስፋ፣ ለካ አያምርብንም ጃን
ይኼው ደም የለመደው እጃችን
እያጋደለ፣ እያጫረሰ ያውለናል
መተማመንና አንድነትን ነስቶናል
ያንተም እድልህ አልቀና አለ፣ መከራው ችግሩ እያደር ባሰ
ለሰላም ያልከው ለጥላቻ፣ ለፍቅር ያልከው ለጸብ ተነሳሳ፣
እርስ በእርስ ተጫረሰ
ከጎሬው ወጥቶ ስንቱ ደነፋ ስንቱ ዱላ ቀሰረ
ስንቱ በጠራራ ፀሐይ አበደ ስንቱ ቀን ለቀን ሰከረ
ስንቱ በተኛበት ተገደለ
ስንቱ ከኖረበት ተፈናቀለ
ይኼን ሁሉ መከራ እላይህ ላይ ተሸክመህ
ያላሰብከው ተፈጽሞ ሆኖ እያየህ
እንዴት ይኾን ውሎህ፣ እንዴት ይኾን እኮ አዳርህ
መቼ ይኾን ባፍህ ‘ሚዞር የለት ጉርስህ
ወንድምዬ! ይብላኝ ላንተ ይብላኝልህ
ሐውልት ብታቆም መርገምት፣
አንድነት ብትፈጥር ውግዘት፣
አገር ብታጸዳ ሹፈት፣
እርቅ ብታወርድ ቅጥፈት፣
ሆኖ ሲወራብህ መልኩን ለውጦ ሲቀርብልህ
ወንድምዬ ምን ተሰማህ?
የዘመናትን ግፍና በደል
በአንድ ግዜ ነቃቅለህ ለመጣል
አገር እንድታድግ ነፃነት ከአጥናፍ አጥናፍ እንድታበራ
ሕዝብ በአንድነት ተደምሮ እንዲሠራ
ያ’ረከውን ምንም እኛ ባንመሰክር ባናወራ
ከአገር አልፎ ዓለም ሰምቶት
ጥበብህን አውቆ አድንቆት
ስምህን ከአድማስ አድማስ እየጠራ አጉልቶ እያየህ
ከትልልቆቹ ተርታ አሰልፎ ሽልማት አሸከመህ
ያም ሆኖ ወንድምዬ ስንት ይኾን ገና የሚቀርህ
ለተነሳህበት ዓላማ የከፈልከው ገና ደግሞ ‘ሚያስከፍልህ
ብዬ እያሰብኩ የአገሬና ያንተ ነገር የሚጨንቀኝ
አንድ አንተኑ የምከተል ሥራህ ጉዞህ የሚገባኝ
ከሩቅ ኾኜ የምታዘብ ስደት ውጪ የጠፈረኝ
ለፍቶ ሠሪ ማስኖ አዳሪ የአገር ልጅ ነኝ
አንተ ግና የስንቱ ዐመል የጠበሰህ፣ ሸክሙ ከብዶ የተጫነህ
ትልቅ ሐሳብ እቅድ ያለህ የአገር ጉዳይ የሚያበርህ
ወጀብ ጎርፉ የሚንጥህ፣ ወዲያ ወዲህ የሚያላጋህ
ብዙ ገና ገና ብዙ የሚቀርህ፣
እረፍት የለሽ ውድ ወንድሜ፣ ይብላኝ ላንተ ይብላኝልህ!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Akalu Tadesse says

    December 27, 2019 11:19 pm at 11:19 pm

    Thank you for speaking out my feelings about the very challenging and demanding environment in which Dr. Abiy is leaving each second. We need to pray to god to give him energy , patience and moreover guide him more. Thank you again Wolelaye. I always liked your poems.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule