• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምን ስም ይሰጠዋል?

October 4, 2016 08:23 am by Editor 1 Comment

በዓለም ላይ የነበሩና ያሉ ዘረኞች፣ ግፈኞችና አምባገነኖች የተለያዩ ምክንያቶች እየፈለጉ ሕዝብ ገድለዋል፣ አስረዋል፣ አሰቃይተዋል። በዚህም ተግባራቸው፣ « ናዚ፣ ፋሽስት፣ ጨፍጫፊ፣ አረመኔ» ወዘተርፈ ተብለዋል። ከእነዚህ እጅግ በከፋ ሁኔታ የዘረኛው የትግሬ ወያኔ ቡድን በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ በአጠቃላይ፣ በተናጠል ደግሞ በዐማራው፣ በኦሮሞው፣ በአኙዋኩ፣ በኑኤሩ፣ በሶማሊው፣ በአፋሩ፣ በሲዳማው ወዘተርፈ ነገዶች ላይ የሚፈጽመው ሁለንታናዊ ግፍ በምን ቃላት ሊገለጽ እንደሚችል የቋንቋ ሊቃውንት ሊያስቡበት የሚገባ ነው። ከላይ የተገለጹት የጭካኔ እና የአረመኔነት ስያሜዎች በፍፁም የወያኔን ማንነትና ዕውነተኛ ባሕሪ አይገልጹትም። ይገልጹታል ከተባለም ተለምዶአዊ በመሆኑ፣ የቃሎቹ የያዟቸው ጽንሰ ሀሳቦችና ድርጊቶቹ የሚጣጣሙ አይደሉም። በምንም ታምር ከጥንት ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የኖረ በዓልን ለማክበር ቄጤማ ይዘው በተቀመጡ ሽማግሌዎች፣ ሕፃናት፣ ሴቶችና ወንዶች ላይ ከሰማይ በአውሮፕላን፣ ከምድር በመትረየስ የሞት ዶፍ ማውረድ በምንም መመዘኛ ምክንያታዊነት የለውም። እገዛዋለሁ የሚለውን ሕዝብ፣ ያውም «ለብሔር/ብሔረሰቦች እኩልነት» ቆሜአለሁ እየለ ጧት ማታ በሚምል የገዛ ወገኑን የደበደበ አረመኔ የሚባል ቡድን በዓለም ታሪክ ስለመኖሩ በእርግጠኝነት ለመናገር አይቻልም።

የትግሬ ወያኔ ፣ በሀሰት ያሰራቸውን የኅሊና እስረኞች በራሱ የፍርድ ሂደት ቢያቀርባቸው አደረጉ ያላቸውን ስለማድረጋቸው ማስረጃ ማቅረብ አልቻለም። ስለሆነም እስካሁንም የሚሠራው ትያትር ሕዝቡ ያወቀበት መሆኑን በመረዳቱ፣ በቂልንጦ፣ በጎንደርና በደብረታቦር እስር ቤቶች በቁጥጥሩ ሥር ያሉትን እስረኞች በእሳት ለኩሶ፣ ንፁሐን ዜጎችን አጠቃ፣ በአሰቃቂ ሁኔታ ጨረሰ። እስረኞችን የወባ መድኃኒት ነው ብሎ፣ ማላታይን አጠጥቶ ፈጀ። ኤች አይ ቪ ቫይረስን በመርፌ እየወጋ ሕዝብ ጨረሰ። የዐማራውን ነገድ ቁጥር ለመቀነስና ፈጽሞ ለማጥፋት ባለው ዕቅድ፣ ዐማራ ሴቶችን ለይቶ በወሊድ ቁጥጥር ስም ታማሚና መካን አደረገ። የዐማራ ወንዶችን የመራቢያ አካላቸውን እየቀጠቀጠ፣ ሰዎችን በቁማቸው ጉድጓድ ውስጥ ከቶ አሰቃየ። እንዲህ ዓይነት ፍፁም አረመኔና ፋሽስት የተባለ ቡድን ከወያኔ በቀር የኢትዮጵያ ታሪክ አያውቅም።

ግፈኛውና ዘረኛው የትግሬ ወያኔ ቡድን ባለፈው እሑድ ጥቅምት 22 ቀን 2009 ዓም በደብረ ዘይት ከተማ የእሬቻን የኦሮሞ ባህላዊ በዓል ለማክበር ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በተሰበሰቡ ንፁሐን ዜጎች ላይ የፈጸመው ቃላት ሊገልጹት የማይችሉት የጅምላ ግድያና ፍጅት ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በጽኑ ያወግዛል።

ግድያው ወያኔ ለ25 ዓመታት ካደረጋቸው የሚለየው፣ ላለፉት ዘጠኝና አሥር ወራት በተከታታይ በሐረርጌ፣ በወለጋ፣ በጅማ፣ በአርሲ፣ በኢሉባቡር፣ በሸዋ፣ በጎንደር፣ በጎጃምና መሰል ክፍለሀገሮች የዘለቀው ሕዝባዊ እንቢተኝነትና የዐማራው የማንነት ትግል ገዝፎና ገፍቶ ምኒልክ ቤተመንግሥት በራፍ ላይ በመድረሱ፣ በወያኔና አሽከሮቹ ላይ የፈጠረው የፍራት መጠን ከፍተኛ መሆን በአልሞት ባይ ፍርግጫ ያላቸውን የመጨረሻ ኃይል ያሳዩበት መሆኑ ነው። ነፃነትን የተጠማ፣ ማንነቱን ለማስከበር ቆርጦ የተነሳን ሕዝብ፣ ይህ ዓይነቱ የፈሪ በትር የታጋዩን ሕዝብ ወኔ ያጎለብታል እንጂ፣ እንደማይቀንሰው የኢትዮያ ሕዝብ ደጋግሞ ለዓለም ማኅበረሰብ አሳይቷል። በመሆኑም የትግሬ ወያኔ ፍርሀት በወለደው ስሜት በእሬቻ በዓል ተሳታፊዎቹ ላይ የወሰደው ዘግናኝና ሰቅጣጭ የጅምላ ፍጅት፣ የወያኔን በቃላት ሊገለጽ የማይችል ጭካኔ ከማሳየት በቀር፣ የሥልጣን ዕድሜውን ያራዝማል ተብሎ አይታሰብም። በአንፃሩ የወያኔን ዕድሜ በእጅጉ የሚያሳጥር፣ የሕዝቡን ነባር አንድነት ወደነበረበት ደረጃ የሚመልስ ነው። እንዲያውም የትግሬ ወያኔ ጠባብና አናሳ ቡድን ለሥልጣን ዕድሜው ማራዘሚያ በኦሮሞውና በዐማራው ነገዶች መካከል በሀሰት ገንብቶት የነበረው የጥላቻ፣ የመጠራጠርና የመገፋፋት ድልድይ ይሰብራል።

ሰሞኑን ደብረዘይት ላይ የፈሰሰው የኦሮሞው፣ የዐማራውና መሰል ነገዶች ልጆች ደም፣ ትናንት ጎንደር፣ ባሕርዳር፣ ደብረታቦር፣ ደብረማርቆስ፣ ነፋስ መውጫ፣ ወረታ፣ አምባ ጊዮርጊስ፣ ደባርቅ፣ ዳንግላ፣ ኮሶ በር፣ ቡሬ፣ ፍኖተ ሰላም፣ ወዘተርፈ ላይ ከፈሰሰው የዐማሮች ደም የሚለየው አንዳችም ነገር የለም።  በሁሉም አካባቢዎች በወያኔ ነፍሰ ገዳዮች የፈሰሰው ደም የኢትዮጵያውያን ደም ነው። ወያኔ ከሁሉም በላይ የዐማራውንና የኦሮሞውን ልዩነት ሊያሰፋው የሚፈልገው ሁለቱ ነገዶች አንድ ከሆኑ ኢትዮጵያን ሊገዛና ሊዘርፋት እንደማይችል ስለሚያውቅ ነው። ይህንን የትግሬ-ወያኔን መሰሪ ሴራ፣ የኦሮሞውና የዐማራው ልጆች «አውቀንባችኋል» በማለት ወደ ነባሩ አንድነታችን በፍጥነት መመለስ ወያኔን አይሞቱ ሞት የሚገድለው እንደሆነ አይጠረጠርም። ስለሆነም የመከራ ጊዜአችን ለማሳጠር የሁለቱ ነገዶች አንድነት ፍቱን የወያኔ አገዛዝ ማርከሻ እንደሚሆን ተረድተን፣ ፍትሕ የተነፈጉ ፍትሕን እንዲያገኙ፣ በአረመኔዎች የተገደሉ ደማቸው ደመከልብ ሆኖ እንዳይቀር፣ ኢትዮጵያውያን በነገድ ሳይሆን፣ በዕኩልነት ላይ በተመሠረተ ኢትዮጵያዊ ማንነት ላይ እንድናተኩር ያሻል።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

የኢትዮጵያ ትንሣዔ በትግላችን ዕውን ይሆናል!
ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት
ማክሰኞ መስከረም ፳፬ ቀን ፪ሺህ፱  ዓ.ም. ቅፅ ፬ ፣ ቁጥር ፴


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Markos says

    October 5, 2016 03:22 pm at 3:22 pm

    TPLF-Tigres have a satanic bacground.
    They even do not belong to the Axumites.
    They are Jews who migrated to Ethiopia during the time of king Kaleb.
    There was Christian masacre in Yemen Nagra by Jews.
    Jews by the leader of Phinhas in Nagra killed and burned Christians and churches.
    King Kaleb waged war against Jews leader Phinhas to save Christians in NAgra.
    He defeated the Jewsish leader Phinhas and the Jewish there.
    He made them captives and brought them to Axum.
    Then they lived there under the rule of Christian Axumite kings.
    During Yodit Gudit they became so powerful to revenge Axumite Christians.
    Now they made a name Tigre and claim all Axumite Civilization.
    They belive in JUdaism of Babylonian TAlmud.
    They are inherently against Christianity and Christians.
    That is why they hate Amhara,Orthodox Christianity and the Monarchy.
    TPLF is a mask for the Nagra Jewish conspiracy.
    The nature of TPLF is same as the nature of satanic Jewish.
    World Jewery used to disposes every nation it controls.
    The same is true of TPLF.
    They use fake names the same way Jews do.
    The total war against Ethiopia is the war waged by international satanic Jewery.
    TPLF is the agent of Illuminati.
    TPLF is part of satanic world jewry and illuminati.
    THey have formed satanic alliance.
    TPLF exploits the sp called Tigres the same way satanic world jewry exploits ordinary Jews.
    TPLF and Illuminati want to deliberately create chaos and dismantle Ethiopia.
    Then they want Tigre republic to be created out of chaos.
    They are creating chaos to achieve independent Tigray.
    Additional referces for my views.
    SOURCE:http://www.rense.com/general66/rosen.htm
    http://www.satenaw.com/amharic/archives/21224

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule