• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አርቲስት ጥላሁን ጉግሳ ምን ነካው?

September 4, 2017 08:02 pm by Editor Leave a Comment

ከአጭር ግዜ እረፍት በኋላ፣ EBC ላይ ብቅ ያለው “ቤቶች” በተሰኘው ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ በክፍል185 እጅግ አስደምሞናል። ተመልካቹ ህዝብ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ጥላሁን ጉግሳ ላይ እየወረደበት ያለው “አሽቃባጭ፣ የወያኔ አቃጣሪ…” ወዘተ ውግዘቶችና ስድቦችን ባልጋራም፣ ይህ አንጋፋ አርቲስት ጥበብን የፖለቲካ መደለያ ስለማድረጉ ግን ምስክር አያሻም። በአንድ ወቅት እጅግ ተወዳጅ የነበረ ይህ ድራማ በመጠነኛ የህወሃት ልማታዊ ቅኝት እየተቃኘ መጥቶ አሁን ላይ ወገን የለየ ይመስላል። ዶፍ ሲጥል ገሚሱ ይበሰብሳል፤ ሌላው ተጠልሎ ይመለከታል፣ ጥቂቱ  ደግሞ ይቀልዳል። ቀልደው ሞተዋል!

ይህንን ድራማ ስመለከት፣ ገሃዱን አለም ከምናቡ አለም በቅጡ ሳይለዩ፣  ሃያልነትዋን ያልተረዱ አርቲስቶች ጥበብን ለተልካሻ ጉዳይ ሲመነዝሩዋት አስተዋልኩ። ወዶ ይሁን ተገድዶ ብቻ፣ በህዝብ ላይ የተከፈተ ጦርነት ላይ ተሰልፎ ፣ በተለይ ለጥበብ ጥብቅና ቆሞ ሲገዘትላት ከኖረ ስው ማየቱ ደግሞ የበለጠ ያምማል።

“…ምን ፍትህ አለ እያልን እጃችንን አጣጥፈን እንቀመጣለን። ይህ ትክክል አይደለም።… “ይለናል አንጋፋው ጥላሁን ጉግሳ። ይህንን የስክሪፕት ረቂቅ ልቦናው ይንገረው ወይንም ደግሞ ህወሃት እንጃ። ነጋዴዎች ቅሬታቸውን በአግባቡ ለሚመለከተው ክፍል እንዲያቀርቡ የሚመክረው የጥበብ ሰው የመንግስት አካላትም ሲያጠፉ እንደሚከሰሱ በዚሁ ትወና አስረግጦልናል። ግና እነዚህ ባለስልጣናት መች እና የት እንደተከሰሱ ጨምሮ ቢነግረን ኖሮ ከውግዘቱ ይድን ነበር። “(የግብሩ) ትመና ፍትሃዊ ነው።” በሚለው ላይ ጸንቶ ሲያበቃ፣  “አንዳንድ” ያላቸው ነጋዴዎች በማጭበርበር ላይ እንደተሰማሩም ይጠቁማል።

ከሕዝብ የምንሰማው ግን ሌላ ነው። ነጋዴዎች በመገኛኛ ብዙሃን እየቀረቡ፣ የተጣለብን ግብር አግባብ አይደለም ቅሬታችንን የሚሰማ አካል አጣን ነው የሚሉን። ጥበብ የገሃዱ አለም ነጸብራቅ እንጂ ተቃራኒ የሚለውን አስተምሮት ጥላሁን በዚህ ተውኔቱ አሳየን።

ለመሆኑ ለፍቶ አዳሪውን ነጋዴውን “አጭበርባሪ” እያሉ በአደባባይ መሳደብ ጥበብ ነውን?

“መረጃ  ደብቀውናል። ያለመረጃ ነው ውሳኔ የምሰጠው” እያሉ የሚያላዝኑት ሃይለማርያም ደሳለኝ እንኳን ደፍረው “በሃገሪቱ ፍትህ አለ” ብለው አይናገሩም።

“ወጣ ወጣና እንደሸምበቆ…” አለ ያገሬ ሰው። ቀጣዩ ስንኝ አያድርስ ነው። ከአጀማመሩ አምሮ ዝናው ሲገንን፣ ነገር አለሙን ወዲያ ሲል የሚወርድ ዱብዳ ነገር። አያድርስ ነው። ሕዝብ “ስራህን ወደድነው።” ሲለው ድራማው የእስትንፋስ ያህል ያስፈልገው እየመሰለው የሚሳሳት ጥቂት አይደለም።

ወትሮውን በየመገናኛ ብዙሃን እየቀረቡ “ሃብታችን ሕዝብ ነው፣ …!” ሲሉ የሚደመጡ አርቲስቶቻችን ከግዚያዊ የግል ችግራቸው በዚህ መንገድ ያመልጡና፣  አንዳች ማዕበል ሲነሳ ደግሞ ከሕዝብ ሲላተሙ ማየት ሳያስተዛዝብ አልቀረም።

ወገን  በኢ-ፍትሃዊ የግብር ተመን ተወጥሮ እያለቀሰ ባለበት በዚህች ቀውጢ ወቅት፣ እንደ ሙሴ “ህዝቤን ልቀቅ!” ማለት እንኳን ባይገድደው ብሶቱን በዚያች ትንሽ ቀዳዳ ማሰማት ያባት ነበር። ነገሩ ተገበጠና ጭራሽ በዱብዳ የግብር አዋጅ እየተሰቃየ ያለውን ነጋዴ አብሮ መውጋት ጀመረ።

የቤቶች ድራማ ከጥበባዊ ይዘቱ ወደ ልማታዊ ይዘቱ ማጋደል የጀመረው መሃል መንገድ ላይ እንደነበር አስታውሳለሁ። ባልጠፋ የሙያ ሰው፣ ባልጠፋ የጥበብ አፍቃሪ፣ ጥላሁን ጉግሳ  እነ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ጠርቶ በአደባባይ ስራውን ሲያስገመግመው ነው ቤቶች የህወሃትን ጠረን ያያዘው። ከዚያን ግዜ ጀምሮ ኩምክናውና ጥበቡ ለዛውን አጥቶ፣ ልማት ተኮር ሆነ።

የጥበብ ሰው ለህብረተሰቡ ፍትህ የሚቆም።  ከፊትም ተስልፎ መስዋዕት የሚሆን እንጂ ሕዝብ አቤት ብሎ የሚተነፍስበት ቀዳዳ ባጣበት ግዜ፣ ይልቁንም በቁስሉ ላይ እንጨት የሚሰድድ አይደለም። የቤቶች ድራማም ቢሆን ከነጋዴው ትከሻ ላይ ተንጠልጥሎ ነጋዴውን መልሶ እንደ አጭበርባሪ አድርጎ ማቅረብ የጤና ነው?

በንግዱ ማህበረሰብ ላይ በመረጃ ሳይሆን በግምት የተቆለለው የገቢ ግብር ተገቢ አይደለም። ይህ  ደግሞ በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል መወገዝ ያለበት ጉዳይ ነው።

“ህዝቡ አጎብዳጆች ይለናል።” ብላ ነበር አርቲስት አስቴር በዳኔ በአንድ ወቅት። ለጥበብ ሰው ከዚህ በላይ ሞት የለም። ከምንወድዳቸው የጥበብ ሰዎች እንዲህ አይነቱን ስናይ ደግሞ ያምማል!

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule