• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አርቲስት ጥላሁን ጉግሳ ምን ነካው?

September 4, 2017 08:02 pm by Editor Leave a Comment

ከአጭር ግዜ እረፍት በኋላ፣ EBC ላይ ብቅ ያለው “ቤቶች” በተሰኘው ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ በክፍል185 እጅግ አስደምሞናል። ተመልካቹ ህዝብ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ጥላሁን ጉግሳ ላይ እየወረደበት ያለው “አሽቃባጭ፣ የወያኔ አቃጣሪ…” ወዘተ ውግዘቶችና ስድቦችን ባልጋራም፣ ይህ አንጋፋ አርቲስት ጥበብን የፖለቲካ መደለያ ስለማድረጉ ግን ምስክር አያሻም። በአንድ ወቅት እጅግ ተወዳጅ የነበረ ይህ ድራማ በመጠነኛ የህወሃት ልማታዊ ቅኝት እየተቃኘ መጥቶ አሁን ላይ ወገን የለየ ይመስላል። ዶፍ ሲጥል ገሚሱ ይበሰብሳል፤ ሌላው ተጠልሎ ይመለከታል፣ ጥቂቱ  ደግሞ ይቀልዳል። ቀልደው ሞተዋል!

ይህንን ድራማ ስመለከት፣ ገሃዱን አለም ከምናቡ አለም በቅጡ ሳይለዩ፣  ሃያልነትዋን ያልተረዱ አርቲስቶች ጥበብን ለተልካሻ ጉዳይ ሲመነዝሩዋት አስተዋልኩ። ወዶ ይሁን ተገድዶ ብቻ፣ በህዝብ ላይ የተከፈተ ጦርነት ላይ ተሰልፎ ፣ በተለይ ለጥበብ ጥብቅና ቆሞ ሲገዘትላት ከኖረ ስው ማየቱ ደግሞ የበለጠ ያምማል።

“…ምን ፍትህ አለ እያልን እጃችንን አጣጥፈን እንቀመጣለን። ይህ ትክክል አይደለም።… “ይለናል አንጋፋው ጥላሁን ጉግሳ። ይህንን የስክሪፕት ረቂቅ ልቦናው ይንገረው ወይንም ደግሞ ህወሃት እንጃ። ነጋዴዎች ቅሬታቸውን በአግባቡ ለሚመለከተው ክፍል እንዲያቀርቡ የሚመክረው የጥበብ ሰው የመንግስት አካላትም ሲያጠፉ እንደሚከሰሱ በዚሁ ትወና አስረግጦልናል። ግና እነዚህ ባለስልጣናት መች እና የት እንደተከሰሱ ጨምሮ ቢነግረን ኖሮ ከውግዘቱ ይድን ነበር። “(የግብሩ) ትመና ፍትሃዊ ነው።” በሚለው ላይ ጸንቶ ሲያበቃ፣  “አንዳንድ” ያላቸው ነጋዴዎች በማጭበርበር ላይ እንደተሰማሩም ይጠቁማል።

ከሕዝብ የምንሰማው ግን ሌላ ነው። ነጋዴዎች በመገኛኛ ብዙሃን እየቀረቡ፣ የተጣለብን ግብር አግባብ አይደለም ቅሬታችንን የሚሰማ አካል አጣን ነው የሚሉን። ጥበብ የገሃዱ አለም ነጸብራቅ እንጂ ተቃራኒ የሚለውን አስተምሮት ጥላሁን በዚህ ተውኔቱ አሳየን።

ለመሆኑ ለፍቶ አዳሪውን ነጋዴውን “አጭበርባሪ” እያሉ በአደባባይ መሳደብ ጥበብ ነውን?

“መረጃ  ደብቀውናል። ያለመረጃ ነው ውሳኔ የምሰጠው” እያሉ የሚያላዝኑት ሃይለማርያም ደሳለኝ እንኳን ደፍረው “በሃገሪቱ ፍትህ አለ” ብለው አይናገሩም።

“ወጣ ወጣና እንደሸምበቆ…” አለ ያገሬ ሰው። ቀጣዩ ስንኝ አያድርስ ነው። ከአጀማመሩ አምሮ ዝናው ሲገንን፣ ነገር አለሙን ወዲያ ሲል የሚወርድ ዱብዳ ነገር። አያድርስ ነው። ሕዝብ “ስራህን ወደድነው።” ሲለው ድራማው የእስትንፋስ ያህል ያስፈልገው እየመሰለው የሚሳሳት ጥቂት አይደለም።

ወትሮውን በየመገናኛ ብዙሃን እየቀረቡ “ሃብታችን ሕዝብ ነው፣ …!” ሲሉ የሚደመጡ አርቲስቶቻችን ከግዚያዊ የግል ችግራቸው በዚህ መንገድ ያመልጡና፣  አንዳች ማዕበል ሲነሳ ደግሞ ከሕዝብ ሲላተሙ ማየት ሳያስተዛዝብ አልቀረም።

ወገን  በኢ-ፍትሃዊ የግብር ተመን ተወጥሮ እያለቀሰ ባለበት በዚህች ቀውጢ ወቅት፣ እንደ ሙሴ “ህዝቤን ልቀቅ!” ማለት እንኳን ባይገድደው ብሶቱን በዚያች ትንሽ ቀዳዳ ማሰማት ያባት ነበር። ነገሩ ተገበጠና ጭራሽ በዱብዳ የግብር አዋጅ እየተሰቃየ ያለውን ነጋዴ አብሮ መውጋት ጀመረ።

የቤቶች ድራማ ከጥበባዊ ይዘቱ ወደ ልማታዊ ይዘቱ ማጋደል የጀመረው መሃል መንገድ ላይ እንደነበር አስታውሳለሁ። ባልጠፋ የሙያ ሰው፣ ባልጠፋ የጥበብ አፍቃሪ፣ ጥላሁን ጉግሳ  እነ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ጠርቶ በአደባባይ ስራውን ሲያስገመግመው ነው ቤቶች የህወሃትን ጠረን ያያዘው። ከዚያን ግዜ ጀምሮ ኩምክናውና ጥበቡ ለዛውን አጥቶ፣ ልማት ተኮር ሆነ።

የጥበብ ሰው ለህብረተሰቡ ፍትህ የሚቆም።  ከፊትም ተስልፎ መስዋዕት የሚሆን እንጂ ሕዝብ አቤት ብሎ የሚተነፍስበት ቀዳዳ ባጣበት ግዜ፣ ይልቁንም በቁስሉ ላይ እንጨት የሚሰድድ አይደለም። የቤቶች ድራማም ቢሆን ከነጋዴው ትከሻ ላይ ተንጠልጥሎ ነጋዴውን መልሶ እንደ አጭበርባሪ አድርጎ ማቅረብ የጤና ነው?

በንግዱ ማህበረሰብ ላይ በመረጃ ሳይሆን በግምት የተቆለለው የገቢ ግብር ተገቢ አይደለም። ይህ  ደግሞ በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል መወገዝ ያለበት ጉዳይ ነው።

“ህዝቡ አጎብዳጆች ይለናል።” ብላ ነበር አርቲስት አስቴር በዳኔ በአንድ ወቅት። ለጥበብ ሰው ከዚህ በላይ ሞት የለም። ከምንወድዳቸው የጥበብ ሰዎች እንዲህ አይነቱን ስናይ ደግሞ ያምማል!

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule