• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ብክነትና ምክነት

April 21, 2016 01:32 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ ውስጥ ገንዘብ የሚያባክን ማን እንደሆነ እናውቃለን። ጊዜም የሚያባክነው ማን እንደሆነ ሳናውቅ አንቀርም። እንዲሁም ወንድና ሴት እንደየተፈጥሯቸው እንዳይወልዱ የሚያመክናቸው ምን እንደሆነ አሳምረን እናውቃለን። አንናገርም እንጂ። ምሁራንንስ የሚያባክንንና የሚያመክን ማነው? ጎበዝ ማለት ይህን የሚያውቅ ነው። እኔም ማወቅ የምፈልገው ያገሬን ምሁራን የሚያባክንብኝና የሚያመክንብኝ ማን እንደሆነ ነው።

ሰሞኑን ያዲስ አበባው መንግስት ቀለም ቀለም ሲሸተው ጊዜ እኔንም እንዲሁ ቀለም ቀለም ስለሸተተኝ ስለምሁራን ብንጫወት ምናለ ብዬ ለዛሬ ቁም ነገሬ እንዲሆን መረጥኩት፤ የኢትዮጵያ ምሁራን ጉዳይ፤ በተለይ ያቋማቸውና የጥቅማቸው ጉዳይ። በይበልጥ ደግሞ እንዲያው እንደዋዛ የመባከናቸው ነገር። ባክነዋል እንዴ? ካላችሁ መልሴ እንክት ነዋ!   የሚል ነው። ላስረዳ። የምናገረው ባሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ምድር ስላሉ ምሁራን መሆኑን ልብ በሉልኝ። የውጪዎቹማ  እንዲያው እንዳይቆጡኝ ድምፃችሁን ዝቅ አድርጋችሁ አንብቡልኝ እንጂ እነርሱማ የባከኑት ገና ዱሮ ካገር ከወጡበት እለት ጀምሮ ነው።

ታዲያ ምሁር ማነው? እስከ ስንተኛ ክፍል የተማረ ነው? ምናምን አትበሉኝ። ከመንግስት ጋር የሚያጣላ ጥያቄ አልወድም። በቃ ምሁር። ይገባችኋል። ለምሳሌ ባለፈው በአሜሪካ ድምፅ አማርኛው አገልግሎት ቀርበው በኢትዮጵያ ወቅታዊ ይዞታ ላይ አስተያየትና ትንተና የሰጡትን ከአዲስ አበባ ዩኒበርሲቲ የህግ፣ ሶሲዮሎጂና የፖለቲካ ትምህርት ምሁራን አይነት ማለት ነው። ስም አልጠራም።

ምሁራን በሰው ልጅ እድገት ታሪክ ውስጥ የተጫወቱትን ሚና መዘርዘር ጊዜ ስለሚፈጅ ብቻ ሳይሆን እኔም ስለማላውቀው አናነሳውም። ግን አለምን ለውጠዋል፤ አቅጣጫዋንም ወስነዋል፣ ሲባል ስለሰማሁ እኔም እንዲያ ብንል ዋስ ጥራ የሚለን ያለ አይመስለኝም። በተለይ ከ18ኛው መቶ ክፍለዘመን ጀምሮና ምናልባትም ከዚያም በፊት በየዘርፉ የተቀመሩት ሳይንሳዊ ንድፈሃሳቦችና ግኝቶች ሰውን ዛሬን እንዲመስል አድርገውታል። በተለይ በመንግስታዊ ያስተዳደር ጉዳይና የፖለቲካ ጥያቄዎች አቅጣጫ እንደየሀገሩ ተጨባጭ ሁኔታ አወንታዊም አሉታዊም ሚና ተጫውተዋል። ባንፃሩ ደግሞ ምንም ፋይዳ ያለው ስራ ሳያከናውኑ እንዲያውም ለክፉ ገዢዎች መሳሪያ አቀባይ ሆነው ያለፉበት ታሪክም ይኖር ይሆናል። መሰረታዊ ጥያቄው የቱ ሀገር በምን አኳኋን ተጠቀመባቸው የሚለው ነው። የት ባከኑ? የትስ መከኑ? በማለት መጠየቅ ማለት ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ምሁራን ጠቅመውናል? በፖለቲካው ምዳ ሚና ኖሯቸው ካልጠቀሙን ባክነዋል ማለት ነው። ምናልባትም መክነዋል።

በኔ አስተያየት በተለይ ባለፉት 40 የምጥ አመታት ምሁራንን ሳንጠቀምባቸው ባክነዋል። ያባከናቸውም መንግስት ነው፤ ያለውም የሄደውም። ደርግ ከፊሉን በመግደል ቀሪውን ደግሞ በውድም በግድም አባሪ በማድረግ እውቀታቸውን አባከነው። ብዙዎቹም የሀገራቸው ጉዳይ ሆዳቸውን እያመማቸውና አንጀታቸው እያረረ በምሁርነት ካባቸው ላይ መንግስታዊ መለዮ ደርበው ከእገሌ ጋር ወደፊት እንዲሉ ተገደዱ። ቀሪዎችም ሲያቀብጣቸው (ወይም ሲፈርድባቸው ማለት ይሻል ይሆናል) ለምን አሉና ተገደሉ። ባከኑ ማለት ይሄ አይደል? ወግነው የተረፉትም ተቃውመው የጠፉትም ያው ባክነዋል።

ዛሬስ? ዛሬም ቢሆን ታሪክ እምብዛም የተለወጠ አይመስልም። እንደመጥምቁ ዮሃንስ በበረሃ ያለሰሚ የሚጮኹ ሀቀኛ ምሁራን መኖራቸው ሳይካድ ብዙሃኑ ግን ወይ ለሆዱ ያለዚያም ለባለክንዱ አድሯል። ቀሪውም ጭልፊት እንዳየች ጫጡት በየተቋሙ ጎሬ አድፍጧል። የቀናውም ይብላኝልሽ ሀገሬ ብሎ ካገር ፈርጥጧል። እናም ሁሉም ባክነዋል።

ልማታዊ ምሁራኑ ሳይንስ፣ መንግስትና እድገት አንድም ሶስትም ናቸው በሚል ተጠምቀው 11 ሚሊዮን ህዝብ በርሃብ በሚያጣጥርባት ኢትዮጵያ 11 ጊዜ አድገናል ይሉናል። ማንም ሰው በማንነቱ መብት አለው የሚለውን የቀለም ትምህርት በላፒስ አጥፍተው ማንነት በሞት በሚያስቀጣባት ሀገር የብሄር መብት ተከበረ ይሉናል። ታዲያ ከዚህ በላይ ብክነትና ምክነት ከየት ይመጣል?

እዚህ ላይ መቼም አንተስ በኢህአዴግ አፍንጫ ስር ብትሆን ኖሮ ውዳሴ መንግስትን ከመድገም ሌላ ምን ታደርግ ነበር የሚል ተፈታታኝ አንባቢ መኖሩ አይቀርም። እኔም ባልሆን እውነቱን ተናግረው እመሸበት የሚያድሩ እውነተኛ የቀለም ልጆች መኖራቸውን አሌ የምንል አይመስለኝም። ያመኑበትን ተናግረው የለት እንጀራቸውን ያጡ ግን ደግሞ የቀለም ቃልኪዳናቸውን የጠበቁ ጀግና ምሁራን መኖራቸውን ዋቢ ጠቅሶ መከራከር ይቻላል። ሌላው ቢቀር የባለጊዜ ፖለቲከኞች ቃለአቀባይ በመሆን ሳይማር ባስተማረን ወገን ላይ ባላስተማረን ትምህርት በሃሰት ከምንፈርድ እሰየው ባያሰኝም እንኳን ጎመን በጤና ያሉትን ጎራ መቀላቀል ሳይሻል ይቀራል። ለነገሩ እሱም መፈቀዱ እርግጠኛ መሆን አይቻልም።

አንድ በንጉሱ ዘመን ሹመት የተሰጠው ሰው ሹመቱን አልፈለገው ኖሮ ንጉሱ ፊት ቀረበና እባክዎ ጃንሆይ፣ ሹመቱ ቀርቶብኝ አርሼ ልብላበት ቢላቸው፥ አይ ሞኝ፣ እሱንስ እኛ ስንፈቅድ አይደል? አሉት ይባላል። እውነት ይሁን አይሁን አላውቅም ግን ተናግሮም ሆነ ዝም ብሎ መኖር በዛሬይቱ ኢትዮጵያ እንዲህ ቀላል ምርጫ እንዳልሆነ እረዳለሁ። እናም ዝም ብሎ ከመጠቃት ዋሽቶ መጠቀም የሚል ፈታኝ እና ጨካኝ አቋም የሚወስዱ ምሁራን ቢኖሩ ልንፈርድባቸው አይገባም ካላችሁ ባላምንበትም ልስማማ እችላለሁ። ብቻ ቁም ነገሩ ሀሰት ተናግረው የተጠቀሙትም፣ ፈርተው ዝም ያሉትም መባከናቸው ነው።

ኢትዮጵያ ከሁለቱም አላተረፈችም። ሁሉንም አጥታለች።

ኢትዮጵያ እግዜር ያፅናሽ! አሜን?


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule