• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አንድ ህዝብ አንድ ሀገር!

July 29, 2016 03:15 am by Editor 2 Comments

ሰው ነፃነት ይፈልጋል። ነፃነት ላለመፈለግ ራሱ ነፃነት ይጠይቃል። ስለዚህ ነፃነቱን የሚቃወም አይኖርም። ምክንያቱም ነፃነትን በራስ መቃወም በራሱ ነፃነት ነው። ሰው ነፃ ለመሆንም ላለመሆንም ነፃ መሆን አለበት። ሰው ነፃ ላለመሆን የመወሰን ነፃነት አለው። ዋናው ጉዳይ ዉሳኔው የራስ መሆን አለበት፤ የሌላ አካል ጣልቃ ገብነት ሊኖረው አይገባም።

ነፃነት የሰው ነው፤ የራሳችን ሃብት ነው። በሌሎች ጣልቃ ገብነት ሊገደብ ግን ይችላል። ስለዚህ ነፃነታትችን ከፈለግን መጠበቅ ይኖርብናል። ነፃነታችንን ለመጠበቅ ፈፃሚ ተቋም ያስፈልጋል። ፈፃሚ ተቋም ወይ ስርዓት የሚኖረው መንግስት ሲኖር ነው። መንግስት የሚኖረው ሀገር ሲኖር ነው። ሀገር የሚኖረው ህዝብ ሲኖር ነው።

የምንፈልገው ነፃ ህዝብ ነው። ነፃ ህዝብ የሚኖረው ዴሞክራሲያዊ መንግስት ሲኖር ነው። ዴሞክራሲያዊ መንግስት የሚኖረው የዴሞክራሲ ግንዛቤ ያለው ህዝብ ሲኖር ነው። ግንዛቤ ያለው ህዝብ መብቱ ያውቃል፤ መንግስት አገልጋይ እንጂ ጌታ አለመሆኑ ይረዳል።

ባጠቃላይ ህዝብ የስልጣን ባለቤት ሲሆን ዴሞክራሲያዊ መንግስት ይኖራል። እናም ነፃነቱን ያረጋግጣል። ህዝብ የስልጣን ባለቤት የሚሆነው መንግስትን መቆጣጠር ሲችል ነው። መንግስትን መቆጣጠር ስልጣን መስጠትንና መንጠቅን ይጨምራል።

ህዝብ መንግስትን መቆጣጠር የሚያስችል ዓቅም የሚፈጥረው አንድነት ሲኖረው ነው። ሰለማዊ ህዝብ በጎሳ፣ በቋንቋ፣ በሀይማኖት፣ በአከባቢ ወዘተ ሳይከፋፈል በአንድነት ሲቆም መንግስትን ይቆጣጠራል። በአንድነት መቆም ማለት የግድ አንድ ዓይነት የፖለቲካ ኣቋም መያዝ አይደለም። የራሱ የመሰለውን አመለካከት ይኖረዋል። የሚወሰነውም በአብዛሃ (አብላጫ) ድምፅ ነው። ምክንያቱም ሁሉም ሰው ነፃ ነው።

ስለዚህ ነፃ ህዝብ እንዲኖረን ነፃ መንግስት ያስፈልጋል። ነፃ መንግስት እንዲኖረን የህዝቦች አንድነት ያስፈልገናል። የህዝቦች አንድነት እንዲኖር የሀገር አንድነት መኖር አለበት። ምክንያቱም የሀገር አንድነት ከሌለ የህዝብ አንድነት አይኖርም። የህዝብ አንድነት ከሌለ የህዝብ ስልጣን አይኖርም። የህዝብ ስልጣን ከሌለ ዴሞክራሲ አይኖርም። ዴሞክራሲ ከሌለ ነፃነት አይኖርም። ነፃነት ከሌለ እኩልነት አይኖርም። እኩልነት ከሌለ ፍትሕ አይኖርም። ፍትሕ ከሌለ የህዝቦች አንድነት አይኖርም። የህዝቦች አንድነት ከሌለ የእርስበርስ ችግር ይኖራል። የእርስበርስ ችግር ሀገርን ያፈርሳል። ሀገር ከፈረሰ ምንም አይኖርም።

ስለዚህ ነፃነት ከፈለግን ሀገር ያስፈልገናል። ሀገር ከፈለግን አንድ ህዝብ (የሚተባበር ህዝብ) ያስፈልገናል። አንድ ህዝብ ከፈለግን ነፃነት ያለው መሆን አለበት። ነፃነት የሌለው ህዝብ ወይ ሀገር አይቆምም። ስለዚህ ሀገር እንዲቆም ነፃነት ያስፈልጋል። ነፃነት እንዲከበር አንድ ሀገር፣ አንድ ህዝብ አስፈላጊ ነው።

ጨቋኝ ገዢዎች ግን የህዝቦችን አንድነት አይፈልጉም። ምክንያቱም ህዝብ አንድ ከሆነ፣ ከተባበረ ከስልጣን ያስወግዳቸዋል። ለዚህም ነው ብዙ ግዜ “የከፋፍለህ ግዛ” ስትራተጂ የሚጠቀሙ። ስለዚህ ነፃነት ፈላጊዎች እንዲያሸንፉና የህዝብና የሀገር አንድነት እንዲጠብቁ የህዝቦችን አንድነት አደጋ ላይ የሚጥል ተግባር አንስራ። መከፋፈል ለገዢዎች ይጠቅማል።

አዎ! አንድ ህዝብ አንድ ሀገር ለነፃነት።

It is so!!!

(ምንጭ: መረጃ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    July 30, 2016 02:58 pm at 2:58 pm

    Excellent and meticulous job of EPRDF has exposed One country advocates as Narrow
    racists .

    One country one people mask unveiled .
    Viva nation nationalities . Amhara is just one gosa in the equation .

    Reply
  2. koster says

    July 31, 2016 07:41 am at 7:41 am

    As long as the fascists from TIGRAI are not dismantelled, our dream of freedom and equality will be in vain. So we should unite to dismantle these home grown fascists. TPLF fascists made the politics very complicated but if we unite all could be solved. The 23 years of the fascists experiment of ethnic federalism/ethnic cleansing is a failure. The forcefully taken land from Gondar, Wollo, Afar and the land grabbing of TPLF fascists should be stopped.The federalism and the constitution made by TPLF and OLF which excluded one of the major ethnic group – Amharas is not binding and should be dismantelled with the fascists. We are not barbaric like the fascists to evict the Tigrians settled on Amhara and Afar land but the ethnic federalism should be dismantelled so that all Ethiopians can live whereever they want. No greater Tigrai, the pre-1991 Ethiopian map should be restored and then the administrative regions will be reorganized again by a free and democratic parliament. There will be two or more national/official languages so that citizens living in one country understand each other.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule