• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደሳለኝ ደበረኝ

November 1, 2015 04:59 pm by Editor Leave a Comment

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱ” “መንግሥት ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። እነዚህ ከባባድ ኢንቨስተሮች ምርቱን በሞኖፖል ከያዙት፣ ይኸ ነገር በሃገራችን “እየተሰፋፉ የመጡትን መካከለኛ ኢንቨስተሮች” ሊያፈናቅላቸው ይችላል ተብሎ ይሰጋል። ይህንን እንዴት ይመለከቱታል።

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ትክክል ነው ልማታዊው መንግሥታችን ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። ይህን ነገር እኮ እኛ የፈለሰፍነው አይደለም። ከሌሎች ሃገሮች ተመክሮ (ኮርጀን – ባግባቡ ወይም ባላግባቡ) ወስደን፣ ለምሳሌ ከደቡብ ኮርያ፣ ቬትናምና ቻይና አይተን ነው። የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የምንሰራበት ምክንያት ኢንቨስተሮች እንዳይቸገሩ ነው። ለምሳሌ መብራት እንዳይቋረጥባቸው። እነሱ ለምን ይቸገሩ? እ? ጨርቁን ቀለም እየቀቡት እያለ መብራት ቢቋረጥ እኮ በቃ ያ ሁሉ ጨርቅ ተበላሸ ማለት ነው። ባለም ገበያ ላይ እኮ ተወዳድረው ነው የሚሸጡት…እ!” (ይሄ የመጨረሻው አረፍተ ነገር ቃል በቃል የተወሰደ ነው [1] ከ 4ኛው ደቂቃ ጀምሮ።

እንግዲህ የትልልቅ ኢንቨስተሮች መብዛት አነሥተኛ ኢንቨስተሮችን ያፈናቅላል አያፈናቅልም ለሚለው ጥያቄ መልሱን አልሰማሁም። ዎልማርት አንድ ቦታ ሲከፈት ያካባቢውን ትንንሽ ነጋዴዎች እንደሚያፈናቅለው ማለት ነው። ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ነው መልሱ። እኔ ደግሞ ይህንን መልስ ሰምቼ ደሳለኝ ደበረኝ። (ወፍጮ ቤቶችና ሱቆች እየፈረሱ መሬት ለሌሎች እየተፈለገ እያለ ማለት ነው።)

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ” “ሶቨሪን ቦንድ የሚባለው ነገርስ ለሃገራችን ትልቅ ጫና ይሆናል የሚባለውስ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “እሱማ ምንም ችግር የሌለበት ብድር ማለት እኮ ነው።ከቻይናና ከወርልድ ባንክ ስትበደሪ ጣጣ አለው። ለምሳሌ ለምን እንደምትፈልጊው፣ ምን ፕሮጄክት ላይ ማዋል እንደምትፈልጊ በዝርዝር ጽፈሽ፣ ፈርመሽ ነው የምትቀበይው። ሶቨሪን ቦንድ ግን በቃ ብር ሥጡኝ ብለሽ መበደር ነው። በሶስት ቀናት የሚገኝ ብድር ነው። ለፈለግሽው ጉዳይ ማዋል ትችያለሽ። እኛ ግን ዝም ብለን ልንበላው አይደለም የምንበደረው … ለሜጋ ፕሮጄክቶች እንዲሆን ነው”

“በሶስት ቀን የሚገኝ ብድር?” … እንዴ ከማን ነው የምትበደሩት? ከማፍያ? “ዝም ብለን ልንበላው አይደለም? ሜጋ ፕሮጄክቶች? ለምሳሌ የብአዴን 35ኛ አመት ማክበሪያ ሜጋ ፕሮጄክት … እየጨፈረን፣ ዝም ሳንል የምንበላው?” ብለን እንጠራጠር የሚል ሃሳብ ውል ባይልብኝም የደሳለኝ መልስ ግን ደበረኝ።

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ” “ግብጽ በአባይ ግድብ የተነሳ በጣም ከማሥጋቷ የተነሳ መሳሪያ እያጠራቀመች ነው ይባላል። ይህንን እንዴት ያዩያል?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ግብጽ ከፈለገች ሃገሩን በሙሉ መሳሪያ ታድርግ። የሚዋጋው መሳሪያ አይደለም አስተሳሰብ ነው”

ደሳለኝ አሳቀኝ። የሚዋጋው አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚባል አስተሳሰብ ነው?

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “መንግሥትዎ ዲሞክራቲክ ነው?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ያለጥርጥር።”

ደሳለኝ አሳቀኝ። ጥርሴ እስኪነቃነቅ።

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “የእርስዎ መንግሥት የሚኮራበትና ሁሌም የሚለው ሃገርዎ እንዴት እያደገች እንዳለች ነው። አነጋጋሪው ጉዳይ ግን የእድገቱ ተጠቃሚዎች በአንድ እጅ ላይ ባሉ ጣቶች ብቻ የሚቆጠሩ ብቻ ናቸው መባሉ ነው። ምን ይመልሳሉ ለዚህ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ጥያቄሽ ጠለቅ ያለ ምርመራና ጥናት የጎደለው ነው። በሃገራችን ከ70 ሚሊዮን ገበሬዎች መሃከል ከድህነት መሥመር በታች ያሉት 15 በመቶ ብቻ ናቸው። ሌላው ሃብታም ነው።”

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “ሃብት በሃብት ከሆናችሁ ታዲያ እልፍ አእላፍ ኢትዮጵያውያን ለምን ይሰደዳሉ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “እንዴ? አልጃዚራ ስለ ስደተኞች ዶክሜንተሪ ሲሰራ አንድም ኢትዮጵያዊ አላሳየም እኮ! ይህ በመሆኑ በጣም ነው ደሳለኝ።” [2] ከ10:47 ደቂቃ ጀምሮ ያዳምጡ።

ደሳለኝ ደሳለኝ አለ። እኔን ግን ደሳለኝ ደበረኝ።

ማብራሪያ ¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ ላልኩበት ምክንያት።

ባለፈው ሰሞን አንድ ደሳለኝን የሚያሞግስ ጽሁፍ አነበብኩ። እኚህ ሰውዬ ደሳለኝ ሥልጣን የሚጋሩት ኒዎ ሊበራሎች እንደሚናገሩት አሻንጉሊት ሆነው ሳይሆን በሃገራችን ሥልጣን የመጋራት ልምድ ኢህአዲግ በማስለመዱና በማስፈሩ ነው ብለው ይደመደማሉ። ከሌሎች ሶስት ሰዎች ጋር ሥልጣን ከተጋሩ ደሳለኝ እንግዲህ ¼ኛ ጠ/ሚ ናቸው። በጫወታችን ላይ የሚያስቀኝ ነገር በጠፋበት ዘመን እኝህ ሰውዬ ይህንን ጽፈው ስላሳቁኝ ባለውለታዬ ናቸው።።

[1] https://www.youtube.com/watch?v=pOSDvm4weOM

[2] https://www.youtube.com/watch?v=VwimUr2C7mY

***********

ጌቱ ኃይሉ አማዞን (amazon.com) ላይ በመሸጥ ያለው ጸሃዮቹ (tsehayochu) የተባለው መጽሃፍ ደራሲ ነው።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule