• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደሳለኝ ደበረኝ

November 1, 2015 04:59 pm by Editor Leave a Comment

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱ” “መንግሥት ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። እነዚህ ከባባድ ኢንቨስተሮች ምርቱን በሞኖፖል ከያዙት፣ ይኸ ነገር በሃገራችን “እየተሰፋፉ የመጡትን መካከለኛ ኢንቨስተሮች” ሊያፈናቅላቸው ይችላል ተብሎ ይሰጋል። ይህንን እንዴት ይመለከቱታል።

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ትክክል ነው ልማታዊው መንግሥታችን ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። ይህን ነገር እኮ እኛ የፈለሰፍነው አይደለም። ከሌሎች ሃገሮች ተመክሮ (ኮርጀን – ባግባቡ ወይም ባላግባቡ) ወስደን፣ ለምሳሌ ከደቡብ ኮርያ፣ ቬትናምና ቻይና አይተን ነው። የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የምንሰራበት ምክንያት ኢንቨስተሮች እንዳይቸገሩ ነው። ለምሳሌ መብራት እንዳይቋረጥባቸው። እነሱ ለምን ይቸገሩ? እ? ጨርቁን ቀለም እየቀቡት እያለ መብራት ቢቋረጥ እኮ በቃ ያ ሁሉ ጨርቅ ተበላሸ ማለት ነው። ባለም ገበያ ላይ እኮ ተወዳድረው ነው የሚሸጡት…እ!” (ይሄ የመጨረሻው አረፍተ ነገር ቃል በቃል የተወሰደ ነው [1] ከ 4ኛው ደቂቃ ጀምሮ።

እንግዲህ የትልልቅ ኢንቨስተሮች መብዛት አነሥተኛ ኢንቨስተሮችን ያፈናቅላል አያፈናቅልም ለሚለው ጥያቄ መልሱን አልሰማሁም። ዎልማርት አንድ ቦታ ሲከፈት ያካባቢውን ትንንሽ ነጋዴዎች እንደሚያፈናቅለው ማለት ነው። ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ነው መልሱ። እኔ ደግሞ ይህንን መልስ ሰምቼ ደሳለኝ ደበረኝ። (ወፍጮ ቤቶችና ሱቆች እየፈረሱ መሬት ለሌሎች እየተፈለገ እያለ ማለት ነው።)

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ” “ሶቨሪን ቦንድ የሚባለው ነገርስ ለሃገራችን ትልቅ ጫና ይሆናል የሚባለውስ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “እሱማ ምንም ችግር የሌለበት ብድር ማለት እኮ ነው።ከቻይናና ከወርልድ ባንክ ስትበደሪ ጣጣ አለው። ለምሳሌ ለምን እንደምትፈልጊው፣ ምን ፕሮጄክት ላይ ማዋል እንደምትፈልጊ በዝርዝር ጽፈሽ፣ ፈርመሽ ነው የምትቀበይው። ሶቨሪን ቦንድ ግን በቃ ብር ሥጡኝ ብለሽ መበደር ነው። በሶስት ቀናት የሚገኝ ብድር ነው። ለፈለግሽው ጉዳይ ማዋል ትችያለሽ። እኛ ግን ዝም ብለን ልንበላው አይደለም የምንበደረው … ለሜጋ ፕሮጄክቶች እንዲሆን ነው”

“በሶስት ቀን የሚገኝ ብድር?” … እንዴ ከማን ነው የምትበደሩት? ከማፍያ? “ዝም ብለን ልንበላው አይደለም? ሜጋ ፕሮጄክቶች? ለምሳሌ የብአዴን 35ኛ አመት ማክበሪያ ሜጋ ፕሮጄክት … እየጨፈረን፣ ዝም ሳንል የምንበላው?” ብለን እንጠራጠር የሚል ሃሳብ ውል ባይልብኝም የደሳለኝ መልስ ግን ደበረኝ።

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ” “ግብጽ በአባይ ግድብ የተነሳ በጣም ከማሥጋቷ የተነሳ መሳሪያ እያጠራቀመች ነው ይባላል። ይህንን እንዴት ያዩያል?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ግብጽ ከፈለገች ሃገሩን በሙሉ መሳሪያ ታድርግ። የሚዋጋው መሳሪያ አይደለም አስተሳሰብ ነው”

ደሳለኝ አሳቀኝ። የሚዋጋው አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚባል አስተሳሰብ ነው?

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “መንግሥትዎ ዲሞክራቲክ ነው?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ያለጥርጥር።”

ደሳለኝ አሳቀኝ። ጥርሴ እስኪነቃነቅ።

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “የእርስዎ መንግሥት የሚኮራበትና ሁሌም የሚለው ሃገርዎ እንዴት እያደገች እንዳለች ነው። አነጋጋሪው ጉዳይ ግን የእድገቱ ተጠቃሚዎች በአንድ እጅ ላይ ባሉ ጣቶች ብቻ የሚቆጠሩ ብቻ ናቸው መባሉ ነው። ምን ይመልሳሉ ለዚህ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ጥያቄሽ ጠለቅ ያለ ምርመራና ጥናት የጎደለው ነው። በሃገራችን ከ70 ሚሊዮን ገበሬዎች መሃከል ከድህነት መሥመር በታች ያሉት 15 በመቶ ብቻ ናቸው። ሌላው ሃብታም ነው።”

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “ሃብት በሃብት ከሆናችሁ ታዲያ እልፍ አእላፍ ኢትዮጵያውያን ለምን ይሰደዳሉ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “እንዴ? አልጃዚራ ስለ ስደተኞች ዶክሜንተሪ ሲሰራ አንድም ኢትዮጵያዊ አላሳየም እኮ! ይህ በመሆኑ በጣም ነው ደሳለኝ።” [2] ከ10:47 ደቂቃ ጀምሮ ያዳምጡ።

ደሳለኝ ደሳለኝ አለ። እኔን ግን ደሳለኝ ደበረኝ።

ማብራሪያ ¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ ላልኩበት ምክንያት።

ባለፈው ሰሞን አንድ ደሳለኝን የሚያሞግስ ጽሁፍ አነበብኩ። እኚህ ሰውዬ ደሳለኝ ሥልጣን የሚጋሩት ኒዎ ሊበራሎች እንደሚናገሩት አሻንጉሊት ሆነው ሳይሆን በሃገራችን ሥልጣን የመጋራት ልምድ ኢህአዲግ በማስለመዱና በማስፈሩ ነው ብለው ይደመደማሉ። ከሌሎች ሶስት ሰዎች ጋር ሥልጣን ከተጋሩ ደሳለኝ እንግዲህ ¼ኛ ጠ/ሚ ናቸው። በጫወታችን ላይ የሚያስቀኝ ነገር በጠፋበት ዘመን እኝህ ሰውዬ ይህንን ጽፈው ስላሳቁኝ ባለውለታዬ ናቸው።።

[1] https://www.youtube.com/watch?v=pOSDvm4weOM

[2] https://www.youtube.com/watch?v=VwimUr2C7mY

***********

ጌቱ ኃይሉ አማዞን (amazon.com) ላይ በመሸጥ ያለው ጸሃዮቹ (tsehayochu) የተባለው መጽሃፍ ደራሲ ነው።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule