• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደሳለኝ ደበረኝ

November 1, 2015 04:59 pm by Editor Leave a Comment

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱ” “መንግሥት ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። እነዚህ ከባባድ ኢንቨስተሮች ምርቱን በሞኖፖል ከያዙት፣ ይኸ ነገር በሃገራችን “እየተሰፋፉ የመጡትን መካከለኛ ኢንቨስተሮች” ሊያፈናቅላቸው ይችላል ተብሎ ይሰጋል። ይህንን እንዴት ይመለከቱታል።

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ትክክል ነው ልማታዊው መንግሥታችን ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። ይህን ነገር እኮ እኛ የፈለሰፍነው አይደለም። ከሌሎች ሃገሮች ተመክሮ (ኮርጀን – ባግባቡ ወይም ባላግባቡ) ወስደን፣ ለምሳሌ ከደቡብ ኮርያ፣ ቬትናምና ቻይና አይተን ነው። የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የምንሰራበት ምክንያት ኢንቨስተሮች እንዳይቸገሩ ነው። ለምሳሌ መብራት እንዳይቋረጥባቸው። እነሱ ለምን ይቸገሩ? እ? ጨርቁን ቀለም እየቀቡት እያለ መብራት ቢቋረጥ እኮ በቃ ያ ሁሉ ጨርቅ ተበላሸ ማለት ነው። ባለም ገበያ ላይ እኮ ተወዳድረው ነው የሚሸጡት…እ!” (ይሄ የመጨረሻው አረፍተ ነገር ቃል በቃል የተወሰደ ነው [1] ከ 4ኛው ደቂቃ ጀምሮ።

እንግዲህ የትልልቅ ኢንቨስተሮች መብዛት አነሥተኛ ኢንቨስተሮችን ያፈናቅላል አያፈናቅልም ለሚለው ጥያቄ መልሱን አልሰማሁም። ዎልማርት አንድ ቦታ ሲከፈት ያካባቢውን ትንንሽ ነጋዴዎች እንደሚያፈናቅለው ማለት ነው። ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ነው መልሱ። እኔ ደግሞ ይህንን መልስ ሰምቼ ደሳለኝ ደበረኝ። (ወፍጮ ቤቶችና ሱቆች እየፈረሱ መሬት ለሌሎች እየተፈለገ እያለ ማለት ነው።)

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ” “ሶቨሪን ቦንድ የሚባለው ነገርስ ለሃገራችን ትልቅ ጫና ይሆናል የሚባለውስ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “እሱማ ምንም ችግር የሌለበት ብድር ማለት እኮ ነው።ከቻይናና ከወርልድ ባንክ ስትበደሪ ጣጣ አለው። ለምሳሌ ለምን እንደምትፈልጊው፣ ምን ፕሮጄክት ላይ ማዋል እንደምትፈልጊ በዝርዝር ጽፈሽ፣ ፈርመሽ ነው የምትቀበይው። ሶቨሪን ቦንድ ግን በቃ ብር ሥጡኝ ብለሽ መበደር ነው። በሶስት ቀናት የሚገኝ ብድር ነው። ለፈለግሽው ጉዳይ ማዋል ትችያለሽ። እኛ ግን ዝም ብለን ልንበላው አይደለም የምንበደረው … ለሜጋ ፕሮጄክቶች እንዲሆን ነው”

“በሶስት ቀን የሚገኝ ብድር?” … እንዴ ከማን ነው የምትበደሩት? ከማፍያ? “ዝም ብለን ልንበላው አይደለም? ሜጋ ፕሮጄክቶች? ለምሳሌ የብአዴን 35ኛ አመት ማክበሪያ ሜጋ ፕሮጄክት … እየጨፈረን፣ ዝም ሳንል የምንበላው?” ብለን እንጠራጠር የሚል ሃሳብ ውል ባይልብኝም የደሳለኝ መልስ ግን ደበረኝ።

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ” “ግብጽ በአባይ ግድብ የተነሳ በጣም ከማሥጋቷ የተነሳ መሳሪያ እያጠራቀመች ነው ይባላል። ይህንን እንዴት ያዩያል?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ግብጽ ከፈለገች ሃገሩን በሙሉ መሳሪያ ታድርግ። የሚዋጋው መሳሪያ አይደለም አስተሳሰብ ነው”

ደሳለኝ አሳቀኝ። የሚዋጋው አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚባል አስተሳሰብ ነው?

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “መንግሥትዎ ዲሞክራቲክ ነው?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ያለጥርጥር።”

ደሳለኝ አሳቀኝ። ጥርሴ እስኪነቃነቅ።

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “የእርስዎ መንግሥት የሚኮራበትና ሁሌም የሚለው ሃገርዎ እንዴት እያደገች እንዳለች ነው። አነጋጋሪው ጉዳይ ግን የእድገቱ ተጠቃሚዎች በአንድ እጅ ላይ ባሉ ጣቶች ብቻ የሚቆጠሩ ብቻ ናቸው መባሉ ነው። ምን ይመልሳሉ ለዚህ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ጥያቄሽ ጠለቅ ያለ ምርመራና ጥናት የጎደለው ነው። በሃገራችን ከ70 ሚሊዮን ገበሬዎች መሃከል ከድህነት መሥመር በታች ያሉት 15 በመቶ ብቻ ናቸው። ሌላው ሃብታም ነው።”

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “ሃብት በሃብት ከሆናችሁ ታዲያ እልፍ አእላፍ ኢትዮጵያውያን ለምን ይሰደዳሉ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “እንዴ? አልጃዚራ ስለ ስደተኞች ዶክሜንተሪ ሲሰራ አንድም ኢትዮጵያዊ አላሳየም እኮ! ይህ በመሆኑ በጣም ነው ደሳለኝ።” [2] ከ10:47 ደቂቃ ጀምሮ ያዳምጡ።

ደሳለኝ ደሳለኝ አለ። እኔን ግን ደሳለኝ ደበረኝ።

ማብራሪያ ¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ ላልኩበት ምክንያት።

ባለፈው ሰሞን አንድ ደሳለኝን የሚያሞግስ ጽሁፍ አነበብኩ። እኚህ ሰውዬ ደሳለኝ ሥልጣን የሚጋሩት ኒዎ ሊበራሎች እንደሚናገሩት አሻንጉሊት ሆነው ሳይሆን በሃገራችን ሥልጣን የመጋራት ልምድ ኢህአዲግ በማስለመዱና በማስፈሩ ነው ብለው ይደመደማሉ። ከሌሎች ሶስት ሰዎች ጋር ሥልጣን ከተጋሩ ደሳለኝ እንግዲህ ¼ኛ ጠ/ሚ ናቸው። በጫወታችን ላይ የሚያስቀኝ ነገር በጠፋበት ዘመን እኝህ ሰውዬ ይህንን ጽፈው ስላሳቁኝ ባለውለታዬ ናቸው።።

[1] https://www.youtube.com/watch?v=pOSDvm4weOM

[2] https://www.youtube.com/watch?v=VwimUr2C7mY

***********

ጌቱ ኃይሉ አማዞን (amazon.com) ላይ በመሸጥ ያለው ጸሃዮቹ (tsehayochu) የተባለው መጽሃፍ ደራሲ ነው።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule