• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፖለቲካ እንቅስቃሴ ሽብርተኝነት አይደለም!!!

May 5, 2013 11:04 am by Editor Leave a Comment

አሁንም የፖለቲካና የህሊና እስረኞች በአፋጣኝ እንዲፈቱ እንጠይቃለን!!!

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

ፓርቲያችን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በሰላማዊና ህጋዊ የትግል መንገድ ለውጥ ማምጣት ይቻላላል፤ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንፈጥራለን፤ ስልጣንም በግለሰቦች ወይም በቡድኖች ይሁንታ የሚገኝ ሳይሆን በህዝቡ በልካም ፈቃድ ይሆናል የሚል ጠንካራ እምነት በመያዝ ከአምባገነኑ ስርዓት ጋር እየታገለ የሚገኝ ነው፡፡

ይሄ ጠንካራ የትግል መነሳሳታችን እና ያለን  የህዝብ ድጋፍ ጠንካራ ተቃዋሚ በዓይኑ ማየት የማይፈልገው ገዥ ፓርቲ ጥርስ ውስጥ የከተተን በምስረታችን ማግስት ጀምሮ ነው፡፡ በርካታ አባሎቻችንንና አመራሮቻችንን ተልካሻ ምክንያት እየተለጠፈባቸው ታስረዋል፣ ተሳድደዋል፣ ተደብደበዋል፡፡

በተለይ ከቅርብ አመታት ወዲህ ደግሞ ጠንካራ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችና ተቃውሞዎች ሁሉ የሚሰጣቸው ስም ሽብርተኝነት የሚል ነው፡፡ የስርዓቱ የስልጣን ማቆያ፣ የሀቀኛ ተቀናቃኞችና ስርዓቱን የሚተቹ ጋዜጠኞች ማሸማቀቂያ ብሎም ማስወገጃ መሳሪያ ሽብርተኝነት ከሆነ ውሎ አድሯል፡፡

ፓርቲያችን አንድነትም ጠኋትና ማታ እየተጠቀሰ ዜጎች እንዲሸማቀቁ የሚደረግበትና የፖለቲካ አመራሮች የሚታሰሩበት የፀረ-ሽብርተኝነት ህግ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ተቃውሞውን አሰምቷል፡፡ ሰኔ 18 ቀን 2001 ዓ.ም የፀረ ሽብር ህጉ ገና ረቂቅ አዋጅ እንደነበረ ለማፈን እየተሰናዳ መሆኑን በመጥቀስ ‹‹የፀረ–ሽብርተኝነት ረቂቅ አዋጅ በዜጎች ላይ ሽብር ፈጣሪ ነው›› በሚል ርዕስ ባወጣነው መግለጫችን ረቂቅ አዋጁ እንዳይፀድቅ የሚሰማ ባይኖርም አበክረን ጩኸታችንን አሰምተን ነበር፡፡

ወዲያው ህግ ሆኖ እንደወጣም የፀረ ሽብርተኝነት ትግልን ሽፋን በማደረግ የገዥው ፓርቲ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የማፈን ድብቅ ፍላጎት ተግባራዊ መሆን ጀመረ፡፡ የመጀመሪያው ሰለባ አንድነት ፓርቲ ነው ብንል ማጋነን አይደለም፡፡ አንዱአለም አራጌንና ናትናኤል መኮነንን የመሰሉ ከፍተኛ የፓርቲ አመራሮችንና ሌሎችን የፓርቲያችን አባሎች በእስር አጥተናል፡፡ እነዚህ በማናለብኝነት የሚፈፀሙ የገዥው ፓርቲ ሸፍጦች ትግላችንን የበለጠ የሚያጠናክሩና አፈናውን ለመስበር ጉልበት የሚሆኑን ናቸው እንጂ አንገታችንን አያስደፉንም፡፡ የፍትህ ተቋማት ላይ እምነት መጥፋቱ፣ ከላይ እስከታች ያለው የአፈና ቋንቋ ተመሳሳይ መሆኑና የገዥው ፓርቲ እጅ መርዘም ትግሉን ማፋፋምና አጠናክሮ መቀጠል ዋና መፍትሄ እንደሆነ የሚጠቁመን ነው፡፡

ሚያዚያ 24 ቀን 2005 ዓ.ም ይግባኝ ሰሚ ችሎት በነ አንዷለም አራጌ ፍርድ ላይ በአንድ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል የአንዱን ጥቂት ዓመታት ከመቀነስ ባለፈ የስረኛውን ፍ/ቤት ውሳኔ ትክክል ነው ብሏል፡፡ ይሄ ፍርድ የሚያስታውሰን የኪሊማንጃሮ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ሊሚትድ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ከፀረ ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር ይፋ ያደረገውን ጥናት ነው፡፡ በ27 የመንግስት ተቋማት ላይ በተደረገ ጥናት ‹‹በከፍተኛ ደረጃ የህዝብ አመኔታ ያጡ ተቋማት›› በሚል ርዕስ ስር በመጀመሪያ ደረጃ የተቀመጡት ፍ/ቤቶች ናቸው፡፡ ይሄ የሚያሳየው ፍ/ቤቶች የገዥው ፓርቲ ጉዳይ አስፈፃሚዎች እንጅ ገለልተኛ ተቋማት አለመሆናቸውን ነው፡፡

ከፍተኛው ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ወጣቱን ፖለቲከኛና ከፍተኛ አመራር አንዱአለም አራጌና ናትናኤል መኮንን ሽብርተኞች እንደሆኑና በሰላማዊ ትግል ሽፋን ሽብርተኝነትን እንሚያራምዱ ተደርጎ የቀረበው ሀተታ የፓርቲያችንን ጠንካራ መዋቅር ያላገናዘበ፣ የፓርቲያችንን መልካም ስም የሚያጎድፍ ነው፡፡ እነ አንዷለምም ሰላማዊ ታጋዮች እንጅ ሽብርተኞች አይደሉም፡፡ ሽብርተኝነት በኮሃራም ናይጀሪያ፣ በፓኪስታንና አፍጋኒስታን በየዕለቱ የምንሰማው እንጅ የኢትዮጵያ ችግር አይደለም፡፡

በአጠቃላይም የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ የኢህአዴግ የዕድሜ ማራዘሚያና መጠቀሚያ ከመሆን በዘለለ ፋይዳ አለው ብለን አናምንም፡፡ የአመራሮቻችንንና አባሎቻችንን መታሰር አጥብቀን እንቃወማለን፡፡ አሁንም ደግመን ደጋግመን የምንለው በሽብርተኝነት ስም ዜጎችን ማሰር ይቁም፤ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ሽብርተኝነት አይደለም፤ የፖለቲካና የህሊና እስረኞ በአስቸኳይ ይፈቱ፡፡

ትግላችን እስከለውጥ ድረስ ይቀጥላል!!!

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት)

ሚያዝያ 25 ቀን 2005 ዓ.ም

አዲስ አበባ    

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule