• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፖለቲካ እንቅስቃሴ ሽብርተኝነት አይደለም!!!

May 5, 2013 11:04 am by Editor Leave a Comment

አሁንም የፖለቲካና የህሊና እስረኞች በአፋጣኝ እንዲፈቱ እንጠይቃለን!!!

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

ፓርቲያችን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በሰላማዊና ህጋዊ የትግል መንገድ ለውጥ ማምጣት ይቻላላል፤ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንፈጥራለን፤ ስልጣንም በግለሰቦች ወይም በቡድኖች ይሁንታ የሚገኝ ሳይሆን በህዝቡ በልካም ፈቃድ ይሆናል የሚል ጠንካራ እምነት በመያዝ ከአምባገነኑ ስርዓት ጋር እየታገለ የሚገኝ ነው፡፡

ይሄ ጠንካራ የትግል መነሳሳታችን እና ያለን  የህዝብ ድጋፍ ጠንካራ ተቃዋሚ በዓይኑ ማየት የማይፈልገው ገዥ ፓርቲ ጥርስ ውስጥ የከተተን በምስረታችን ማግስት ጀምሮ ነው፡፡ በርካታ አባሎቻችንንና አመራሮቻችንን ተልካሻ ምክንያት እየተለጠፈባቸው ታስረዋል፣ ተሳድደዋል፣ ተደብደበዋል፡፡

በተለይ ከቅርብ አመታት ወዲህ ደግሞ ጠንካራ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችና ተቃውሞዎች ሁሉ የሚሰጣቸው ስም ሽብርተኝነት የሚል ነው፡፡ የስርዓቱ የስልጣን ማቆያ፣ የሀቀኛ ተቀናቃኞችና ስርዓቱን የሚተቹ ጋዜጠኞች ማሸማቀቂያ ብሎም ማስወገጃ መሳሪያ ሽብርተኝነት ከሆነ ውሎ አድሯል፡፡

ፓርቲያችን አንድነትም ጠኋትና ማታ እየተጠቀሰ ዜጎች እንዲሸማቀቁ የሚደረግበትና የፖለቲካ አመራሮች የሚታሰሩበት የፀረ-ሽብርተኝነት ህግ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ተቃውሞውን አሰምቷል፡፡ ሰኔ 18 ቀን 2001 ዓ.ም የፀረ ሽብር ህጉ ገና ረቂቅ አዋጅ እንደነበረ ለማፈን እየተሰናዳ መሆኑን በመጥቀስ ‹‹የፀረ–ሽብርተኝነት ረቂቅ አዋጅ በዜጎች ላይ ሽብር ፈጣሪ ነው›› በሚል ርዕስ ባወጣነው መግለጫችን ረቂቅ አዋጁ እንዳይፀድቅ የሚሰማ ባይኖርም አበክረን ጩኸታችንን አሰምተን ነበር፡፡

ወዲያው ህግ ሆኖ እንደወጣም የፀረ ሽብርተኝነት ትግልን ሽፋን በማደረግ የገዥው ፓርቲ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የማፈን ድብቅ ፍላጎት ተግባራዊ መሆን ጀመረ፡፡ የመጀመሪያው ሰለባ አንድነት ፓርቲ ነው ብንል ማጋነን አይደለም፡፡ አንዱአለም አራጌንና ናትናኤል መኮነንን የመሰሉ ከፍተኛ የፓርቲ አመራሮችንና ሌሎችን የፓርቲያችን አባሎች በእስር አጥተናል፡፡ እነዚህ በማናለብኝነት የሚፈፀሙ የገዥው ፓርቲ ሸፍጦች ትግላችንን የበለጠ የሚያጠናክሩና አፈናውን ለመስበር ጉልበት የሚሆኑን ናቸው እንጂ አንገታችንን አያስደፉንም፡፡ የፍትህ ተቋማት ላይ እምነት መጥፋቱ፣ ከላይ እስከታች ያለው የአፈና ቋንቋ ተመሳሳይ መሆኑና የገዥው ፓርቲ እጅ መርዘም ትግሉን ማፋፋምና አጠናክሮ መቀጠል ዋና መፍትሄ እንደሆነ የሚጠቁመን ነው፡፡

ሚያዚያ 24 ቀን 2005 ዓ.ም ይግባኝ ሰሚ ችሎት በነ አንዷለም አራጌ ፍርድ ላይ በአንድ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል የአንዱን ጥቂት ዓመታት ከመቀነስ ባለፈ የስረኛውን ፍ/ቤት ውሳኔ ትክክል ነው ብሏል፡፡ ይሄ ፍርድ የሚያስታውሰን የኪሊማንጃሮ ኢንተርናሽናል ኮርፖሬሽን ሊሚትድ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ከፀረ ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር ይፋ ያደረገውን ጥናት ነው፡፡ በ27 የመንግስት ተቋማት ላይ በተደረገ ጥናት ‹‹በከፍተኛ ደረጃ የህዝብ አመኔታ ያጡ ተቋማት›› በሚል ርዕስ ስር በመጀመሪያ ደረጃ የተቀመጡት ፍ/ቤቶች ናቸው፡፡ ይሄ የሚያሳየው ፍ/ቤቶች የገዥው ፓርቲ ጉዳይ አስፈፃሚዎች እንጅ ገለልተኛ ተቋማት አለመሆናቸውን ነው፡፡

ከፍተኛው ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ወጣቱን ፖለቲከኛና ከፍተኛ አመራር አንዱአለም አራጌና ናትናኤል መኮንን ሽብርተኞች እንደሆኑና በሰላማዊ ትግል ሽፋን ሽብርተኝነትን እንሚያራምዱ ተደርጎ የቀረበው ሀተታ የፓርቲያችንን ጠንካራ መዋቅር ያላገናዘበ፣ የፓርቲያችንን መልካም ስም የሚያጎድፍ ነው፡፡ እነ አንዷለምም ሰላማዊ ታጋዮች እንጅ ሽብርተኞች አይደሉም፡፡ ሽብርተኝነት በኮሃራም ናይጀሪያ፣ በፓኪስታንና አፍጋኒስታን በየዕለቱ የምንሰማው እንጅ የኢትዮጵያ ችግር አይደለም፡፡

በአጠቃላይም የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ የኢህአዴግ የዕድሜ ማራዘሚያና መጠቀሚያ ከመሆን በዘለለ ፋይዳ አለው ብለን አናምንም፡፡ የአመራሮቻችንንና አባሎቻችንን መታሰር አጥብቀን እንቃወማለን፡፡ አሁንም ደግመን ደጋግመን የምንለው በሽብርተኝነት ስም ዜጎችን ማሰር ይቁም፤ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ሽብርተኝነት አይደለም፤ የፖለቲካና የህሊና እስረኞ በአስቸኳይ ይፈቱ፡፡

ትግላችን እስከለውጥ ድረስ ይቀጥላል!!!

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት)

ሚያዝያ 25 ቀን 2005 ዓ.ም

አዲስ አበባ    

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule