• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሙስሊሙ ኅብረተሰብ ላይ በደል እየፈጸመ ነው” ተጓዦች

September 22, 2015 09:29 am by Editor 1 Comment

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚጓዙ መንገደኞችን በአሮጌው ተርሚናል በኩል በማስተናገድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዜጎች በማንነታቸው ተለይተው እየተዋከቡ መሆኑን መንገደኞቹ የደረሰባቸውን በደል ዋቢ በማድረግ ምንጮች ገልጸዋል። በተለይ ከሳውዲ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ተጓዦችን በአየር መንገዱ የሚገኙ የደኅንነት ሰዎች ግልጽ ጉቦ እየጠየቁ እንደሆነ ተነገረ፡፡

በተለይ ወደ ሳውዲ አረቢያ የሚጓዘው ኢትዮጵያውያዊ አብዛኛው ሙስሊም ማህበረሰብ እንደመሆኑ መጠን ጥብቅ ቁጥጥር እና ክትትል እንደሚደረግባቸው የሚገልጹ እነዚህ ምንጮች ዜጎች በገዛ አገራቸውና አየር መንገዳቸው እንደ ሁለተኛ ዜጋ መታየታችው የመንግስት እጅ እንዳለበት አመላካች መሆኑን ይጠቁማሉ።

በአሮጌው ተርሚናል የሚስተናገድ እነዚህ የአየር መንገዱ ተገልገላይ ኢትዮጵያውያን ደምበኞች ይዘውት በሚወጡትና በሚገቡት እቃዎቻቸው ላይ ያለአግባብ ጥብቅ ፍተሻ ይደረጋል፤ ለቤተሰብ፣ ዘመድ አዝማድ ስጦታ የሚውል እቃዎቻቸው ላይ ከፍተኛ ቀረጥ ይጣላል፤ የመንገደኛው ሻንጣ ቁልፍ ተሰብሮ ይዘረፋል፤ ሻንጣዎቹ እስክነ አካቴው የውሃ ሽታ ሆነው ይቀራሉ፣ ወዘተ። ከዚህም ሌላ በዚህ ተርሚናል የሚስተናገዱ ደንበኞች በአየር መንግዱ ሰራተኞች ክብር አይሰጣቸውም መብቱን ለማስከበር “ለምን?” ብሎ የጠየቀ መንገደኛ ይሰደባል፣ ይገለመጣል፣ አልፎ አልፎ በጥፊና በካልቾ የሚሰተናገድበት አሳዛኝ አጋጣሚ እንደሚከሰት የአይን እማኞች ገልፀዋል።

ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው እና የከፋው ሳውዲ አረቢያ “መካ” ለሃጅ የፀሎት ሥርዓት በቤተሰብ አጀብ የሚሸኙ የጸሎት ተጓዥ ምእመናን ወደ አሮጌው ተርሚናል ከገቡ በኋላ እንደ ፀሎት ተጓዥ ሳይሆን አንደ አንድ መንገደኛ ማግኘት የሚገባቸውን ክብር አጥተው ስርዓት በሌላቸው አንዳንድ የአየር መንገዱ አስተናጋጆችና የፀጥታ አባላት እንደሚዋከቡ በደሉ የደረሰባቸውን ዜጎች ዋቢ በማድረግ ይገልጻሉ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሮጌው ተርሚናል እያደረገ ካለው የወረደ መስተንግዶ ይልቅ “ጅዳ” ሳውዲ አረቢያ አየር ማረፊያ በባዕዳኑ የአየር መንገዱ ሰራተኞችና የፀጥታ ሃይሎች የሚደረጉላቸው አቀባበልና መስተንግዶ ምንም እንደማይገናኝ ሰሞኑን ጅዳ ከገቡ ምዕመናን የሃጅ ጸሎት ተጓዥ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ማረጋገጥ ተችሏል።

የኢትዮጵያ አየር መንገዱ መስተንግዶ “አገዛዙ ሃገር ውስጥ በጋራ እና በተናጠል ህዝበ ሙስሊሙ ተቋም ላይ ከሚፈጽመው በደል አይለይም” የሚሉ አንዳንድ ወገኖች፤ በአሮጌው ተርሚናል በኩል የሚያልፍ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም እንደ ዜጋ ቀርቶ አንድ ቆዳው ነጣ ያለ መንገደኛ የሚሰጠውን ክብር ያህል ቦታ የለንም ይላሉ።

የኢትዮጵያ አየር መንገዱ መስተንግዶ በኢትዮጵያዊን ሙስሊም ወገኖቻችን ላይ ብቻ ያነጣጠር ይሁን እስካሁን ማረጋገጫ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ባይሳካም “ከተልባ የተገኘህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ” እንዲሉ በኮንተራት ስራም ሆነ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ተጠቀሱት ሃገርት የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ሳይቀሩ በደሉ እየተፈፀመባቸው መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

የሃገሪቱን ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ አርማው በማድረግ ከግማሽ መዕተ አመት በላይ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው ይህ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ ህዝብ የሆነው አየር መንገድ በገዥው ፓርቲ ህ.ወ.ሃ.ት/ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ስርአት ካድሬዎች እጅ ከወደቀ ወዲህ ዜጎች በማንነታቸው እየተለዩ የዜግነት ክብራቸውን የሚያጡበት ብቻ ሳይሆን የአየር መንገዱ ሰራተኞች ጭምር በብሄር ማንነታቸውና በፖለቲካ አመለካከታቸው እየተለዩ ግፍና በደል የሚፈፀምባቸው ማዕከል እየሆነ መምጣቱ ይታወቃል።

የህወሃት/ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ስርዓት የዜጎችን ከሃገር ወደ ሃገር የመዘዋወር ህገመንግስታዊ መብት በመጣስ ከሳውዲ አረቢያ ቤተዘመድ ጥየቃ ለእረፍት ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ ዜጎች የዕረፍት ግዜያቸውን ጨርሰው ሲመለሱ የሚኖሩበትን ሃገር የመኖሪያ ፈቃድ መታወቂያ “ኢቃማ” ካላመጣችሁ አታልፉም በሚል ምክንያት በአየር መንግዱ ውስጥ በተሰገሰጉ የፀጥታ ሃይሎች እስከ 10 ሺህ ሪያል የሚደርስ ጉቦ በግልጽ እንደሚጠየቁ ለመረዳት ተችሏል።

በሳውዲ አረቢያ ህግ ማንኛውም የውጭ ሃገር ዜጋ ፓስፖርቱን ከአሰሪው እጅ ሲቀበል የመኖሪያ ፈቃዱን ለአሰሪው ማስረከብ እንደሚገባ ይደነግጋል። (Ethiopian Hagere Jed Bewadi ለጎልጉል የላኩት)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. chombe says

    October 3, 2015 06:56 am at 6:56 am

    this comment is quite true, but those who control the Airport are Civil Aviation or Airport Administration, not Ethiopian Airlines. Ethiopians Airlines only has Aircraft and its service in the plane.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule