• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት – ስዩም ተሾመን በአሰቃቂ ሁኔታ እንደምትገል ማስጠንቀቂያ ላከች

October 28, 2019 09:31 am by Editor 11 Comments

“ሕዝብ ስዩምን ሊጠብቀው ይገባል”

በጃዋር ትዕዛዝ ንጹሃን መጨፍቸፋቸውን፣ መታረዳቸውን፣ የእምነት ተቋማት መቃጠላቸውንና ንብረት መውደሙን ተከትሎ ሴራው እንዴትና በነማን ቅንጅት እንደተቀነባበረ ይፋ በማድረግ ላይ ባለው አምደኛና የሰብአዊ መብት ተሟጋች ስዩም ተሾመ ላይ የግድያ ዛቻ ተሰነዘረ። የግድያው ዛቻ በቀጥታ የተላከው ከህወሓት ሥራ አስፈጻሚ አባል ጌታቸው ነው።

ህወሓት ፖሊሱን፣ ደህንነቱን፣ መከላከያውን፣ ኢኮኖሚውን ከፍተኛውን የአገሪቱን ሥልጣን በተቆጣጠረበት ወቅት በዩኒቨርስቲ መምህርነቱ ጎን ለጎን ትግል ሲያካሂድ የነበረው ስዩም ተሾመ በተደጋጋሚ ታስሯል፣ ቶርቸር ተደርጓል፣ ተሰቃይቷል፣ እንደዜጋ ለምን ጻፍክ በሚል የከፋ ወንጀል ተፈጽሞበታል።

በዚህ ሁሉ መከራ ውስጥ ቢያልፍም ግንባሩን ሳያጥፍ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባርን በብዕሩ ተጋፍጧል። ለውጡ እውን ከሆነ በኋላም ሥራውን አቁሞ “ነጻ ውይይት” በሚል ርዕስ ቃለ መጠይቅ በማቅረብ የህወሓትን ገበና አደባባይ እርቃን አውጥቷል። 

ቀድሞም ጥርስ የተነከሰበት ስዩም እሁድ ይፋ እንዳደረገው አቶ ጌታቸው ረዳ ለወሲብ ሲዳራ የሚያሳይ፣ ከጃዋር መሀመድ ጋር አገሪቱን አተራምሶ መንግሥት ለመገለበጥ ያሴሩትን ሤራ የሚያጋልጥ የኢሜል መልዕክቶችን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ነው ማስፈራሪያው በቀጥታ የተላከለት።

ዜጎች ጥበቃ ሊያደርጉለት እንደሚገባ በተደጋጋሚ ቢነገርም ስዩም ግን ግንባሩን እንደማያጥፍና እስከወዲያኛው በጀመረው ሥራ እንደሚቀጥል በፌስቡክ ገጹ ይፋ አድርጓል።

ህወሓት ከፍተኛ ኃላፊነት የሰጠችውና የፓርላማ አባል የሆነው ጌታቸው የራያን ህዝብ በመሸጡ ብቻ ሳይሆን በሴሰኛነት፣ በዝሙት፣ ሃብት በማሸሽ፣ ከአገር ውጪ ንብረት በማካበት፣ በሶማሊ ክልል የተሞከረው አገር የመበተን አጀንዳ ከከሸፈ በኋላ፣ አሁን ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሚመሩትን መንግሥት በነውጥ ለመጣል ከድብረጽዮን (ጌታቸው አሰፋ) ውክልና ወስዶ በቅማንት፣ በወላይታ፣ በኦሮሚያ፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በጋምቤላና በሌሎች አካባቢዎች ለሚፈጸሙ የማተራመስ ዕቅዶች ዋና አስተባባሪ መሆኑ ይታወቃል።

ለዚህ የጌታቸው ረዳ ዛቻ “ይድረስ ለጌታቸው ረዳ፤ እኔ ያመንኩበትን ሰርቼ እንጂ አንተን ፈርቼ አልሞትም” ስዩም የሰጠው መልስ የሚከተለው ነበር፤

ይህን የኢሜይል መልዕክት የፃፍከው እኔን በማስፈራራት አንተና ድርጅትህ ህወሓት በሀገር ደህንነትና የዜጎች ህይወት ላይ የምትፈፅሙትን ወንጀል ከማጋለጥ እንድታቀብ ለማድረግ ነው። ነገር ግን እኔን በማስፈራራት ያመንኩበትን ነገር ከማድረግ ለማስቆም መሞከር ሞኝነት ነው። ምክንያቱም ይህን ፈፅሞ ማድረግ አይቻልም። አንድ የማዕከላዊ መርማሪ ልክ አንደ አንተ በእብሪት ተወጥሮ “ጥጋብህ እዚህ ደርሷል! ጠብቅ ቆይ አሳይሃለሁ!” ብሎ ሲዝትብኝ “ሌሊት ላይ ወደ ማሰቃያ ክፍል ወስጄ ጥፍርህን እየነቀልኩ አሰቃይሃለሁ!” ማለቱ እንደሆነ ገምቼያለሁ። ነገር ግን ክፍሌ ውስጥ ገብቼ በፍርሃት ስንበቀበቅ አታገኘኝም። ከዚያ ይልቅ ከእግሬ ጣቶች የአንዱን ጥፍር በገዛ እጄ ነቅዬ ስቃዩን ተለማምጄ ነው የጠበቅኩት!!! አሁን አንተም ይህን ማስፈራሪያ እዚህ ፌስቡክ ላይ ከለጠፍኩት “እንደ ውሻ በድንጋይ ተወግረህና ተሰቃይተህ ትሞታለህ” ብለሃል አይደል?? ቱፍ!! እኔ ወንድ የአባቴ ልጅ ነኝ። ያመንኩበትን ሰርቼ እንጂ ፈርቼ አልሞትም። ይሄው የአንተን ማስፈራሪያ እዚህ አውጥቼ ለጠፍኩት!!! በል እስኪ እንዳልከው ቅጥረኞችህን ላክና ግደለኝ!

ጎልጉል አስተያየት የጠየቃቸው እንደተናገሩት ከሆነ መንግሥት እንደ ጃዋር ላሉት ጥበቃ የሚያቆም ከሆነ በዚያ ተጻራሪ ለአገርና ለሕዝብ ኅልውና በዚህ መልኩ መስዋዕትነት ለሚከፍሉ ዋስትና ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል።

“ስዩም ያለመታከት ከሚወጣቸው መረጃዎች በእጅጉ እየተጠቀመ ያለው ሕዝብ ወገናዊነቱን ለስዩም ጥበቃ በማድረግ ሊወጣ ይገባዋል” ያሉ አስተያየት ሰጪ ደግሞ “አገር ለመበታተንና ሕዝብን ለማጋደል ቀን ተሌት ለሚሠራው ጃዋር ድጋፍ እየሰጡ ካሉት ቄሮዎች የእውነትና የአገር ፍቅር ስሜት ላቸው ትምህርት ቢወስዱ መልካም ነው፤ እነርሱ ለጥፋት ይህንን ያህል ሲተጉ እኛ ደግሞ አገር ለማዳን ለሚሠሩ ከዚህ እጥፍ ልንሠራና ልንተጋ ይገባል” ብለዋል።

በአጠቃላይ አስተያየት የሰጡ እንደተናገሩት ከሆነ ግን እንደዚህ ባለ መልኩ የግድያ ሙከራና ሤራ ከአንድ የህወሓት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሲሰነዘር መንግሥት እየሰማ ዝም ማለት የለበትም፤ ጌታቸው ረዳን በኃላፊነት መጠየቅ ብቻ ሳይሆን ለስዩም ተሾመም ልዩ ጥበቃ ሊያደርግለት ይገባል ብለዋል።   


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column, seyoum teshome, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Silesh Seyoum says

    October 29, 2019 02:37 pm at 2:37 pm

    እዉነተኛ እና እዉነት አይሞትም ሞት ለዉሸታሞች

    Reply
  2. Babilon Jutass says

    November 1, 2019 12:07 am at 12:07 am

    ድሮም የቁሞ ቀር አስተሳሰብ እና የአምባነን፣ የጠባብ ፣ የሙሰኛ እና የሌባ ድርጅት ከዚህ በላይ ማሰብ የት ያውቅና! መግደል፣ ማሰቃየት፣ መዝረፍ፣ ማሸማቀቅ፣ ወዘተ. ላለፉት 28አመታት ሲሰራው የኖረ የደንቆሮ ስራ ነው! አገር መምራትማ የት ያውቅና! ለነገሩ ችሎታውስ የት ኖሮት!ዛሬም በስብሰውም እየሸተቱ እንኳ መግማታቸውን ማያውቁ ለመታጠብም ሆነ ለመፅዳት ማያስቡ መትላታቸውን መገንዘብ ያቃታቸው እና በተቀመጡበት እራሳቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው መቀመጫ ሚያበላሹ ሰዎች እንዴት ለሌላ ሰው ብሎም ለሀገር ሊያስቡ ይችላሉ! ምክንያቱም ሲጀመር ማርክዝም ሌኒዝም ሚስማር ቀርቅሮ ይዟቸው እንዴት ይለወጡ! በ60ውቹ አሰተሳሰብ እንዴት የዛሬ ሀገር ይመራል! ለዚህ ነው ሰው ሲቀነጭር ሚታየው መግደል ማስገደል ብቻ የሚሆነው! ስለዚህ ወንድሜ ስዩም እራስህን ጠብቀህ ስራህን ስራ ለበሰበሱ በሽተኞች ጆሮህን አትስጥ! የተዘረፈ ገንዘብ ስለያዙ ሁሉን ማድረግ ሚቻል ይመስላቸዋል! ፈጣሪ አንድ ቀን የጃቸውን ይሰጣቸዋል! #ኢትዮጵያ# ድሮም ሆነ ዛሬ ጠባቂዋ በሰበሱ መሪዎች ሳይሆን በፀዱ በነቁ ባስተዋሉ ልጆቿ እና ፈጣሪዋ ነው! እንደ ሰዎች እማ ብሆን………..!!!

    Reply
  3. Yilna says

    November 1, 2019 03:30 pm at 3:30 pm

    ወገቡን የተመታ ጅብ እስኪሞት ማላዘኑ አይቀርም። እዚህም ያለው ልሙስሙስ መንግስ እድላቸውን አስፍቶላቸዋል። አገር እያበጡና የዘር ማጥፋትን ሲፈጽሙ አንገድልም በሚል ልፍስፍስነት በተንሻፈፈ የቀን ቅዘት ፍልስፍና የሚንከዋረረው ጅል መሪ ነው የተጫወተብን። ጥፋተኛና ወንበዴን አንገልም እያለ ንጹሀንን አቅመ የሌላቸውን አዛውንቶች የሚያስገድል።

    Reply
  4. yhenew says

    November 1, 2019 04:18 pm at 4:18 pm

    How it is thought
    No, he scoffs when pure blood cries out.
    I # Ethiopia
    እንዴት ሆኖ ይታሰባል
    አይ የንፁሃን ደም ሲጮህ እንዲህ ያስለፈልፋል።
    አይ #ኢትዮጵያዬ
    ስይሜ ኑርልን
    ገዳዮች ሟቾች ናቸው።

    Reply
  5. ሲራክ says

    November 1, 2019 05:25 pm at 5:25 pm

    እውነትና እውነተኛ አይሞትም::

    Reply
  6. ????? says

    November 1, 2019 05:28 pm at 5:28 pm

    እውነትና እውነተኛ አይሞትም:: ሞት ለገዳይ!!

    Reply
  7. Ashenafi says

    November 1, 2019 09:23 pm at 9:23 pm

    NO coment

    Reply
  8. biniyam says

    November 1, 2019 09:53 pm at 9:53 pm

    መንግስት ሽብር ፈጣሪዎችን አንድ ይበልልን

    Reply
  9. Getachew says

    November 1, 2019 09:56 pm at 9:56 pm

    ቱፍ!! እኔ ወንድ የአባቴ ልጅ ነኝ። ማለቱ ጀግና ነኝ የሚል ሰው ጥበቃ የሚያስፈልገው አይመስለኝም

    Reply
  10. Kiburjela says

    November 2, 2019 09:38 am at 9:38 am

    Both TPLF and Seyoum are terrorist, but so sadly Seyoum is a beggar on top of that. He soon plans to open a go fund me account to ridicule Amhara and snatch their money through the emotionally charged but false write ups like this one.

    Reply
  11. Kibrom says

    November 13, 2019 03:04 am at 3:04 am

    If source of email is authentic then
    Seyoum should report to Ethiopian
    authorities, international consulates
    in Addis, and human rights groups.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule