• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሕዝባዊው ንቅናቄ ኢህአዴግ ሠግቷል

December 12, 2015 11:25 am by Editor 1 Comment

ለጎልጉል የእማኝ ዘጋቢ (ireporter) የሆኑ በላኩልን መረጃ መሠረት በኢትዮጵያ የተለያዩ ቦታዎች የተነሣው ንቅናቄ ወደ ሲቪል ሠራተኞች ዘልቆ እንዳይገባ ስጋት ውስጥ የገባው ኢህአዴግ ሠራተኞችን ማባበልና ማንቃት ጀምሯል፡፡

በተያዘው ዕቅድ መሠረት በአዲስ አበባ በሚገኙ ወረዳዎች ውስጥ በሲቪል ሠራተኝነት የሚታወቁ ዜጎችን ኢህአዴግ በየቦታው መሰብሰብ ጀምሯል፡፡ እማኙ በላኩት መረጃ እንደገለጹት ለሁለት ቀን በሚካሄደው ስብሰባ በየወረዳው ለሚሰበሰቡ ሠራተኞች ቢያንስ ብር 300 አበል በመስጠት የማባበያ ስብሰባው እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡ በየወረዳው ካለው ሲቪል ሠራተኛ አንጻር ለአበል የታሰበው ብር በሚሊዮን ሊቆጠር እንደሚችል እማኙ ጨምረው አስረድተዋል፡፡

ዋናው አጀንዳ ሲቪል ሠራተኛው እየተካሄደ ባለው ንቅናቄ ተሳታፊ እንዳይሆን፤ እንዳይተባበር፤ ድጋፍ እንዳይሰጥ፤ … ሲሆን ተሰብሳቢዎቹ ወደ ስብሰባው የመጡት የህወሃት/ኢህአዴግ ደጋፊ ሆነው ሳይሆን አለመሳተፍ የሚያመጣባቸውን ከመፍራትና በነጻ ስለሚያገኙት አበል በማሰብ እንደሆነ እማኝ ዘጋቢው ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ሰብሳቢዎቹ “ንቅናቄውን እንዳትደግፉ” ወይም “ማስተር ፕላኑን በተመለከተ የተነሳውን የኦሮሞ ተቃውሞ እንዳትደግፉ” ወይም መሰል ግልጽ ማስጠንቀቂያ ለተሰብሳቢዎቹ እንዳልሰጡ መረጃውን የላኩት እማኝ ዘጋቢ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ይልቅ ግን በተዘዋዋሪ ሁኔታ ከጸረ ልማት ኃይሎች ጋር እንዳትተባበሩ፤ ጸረ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎችን እንዳትደግፉ፤ ተገልጋዩን ኅብረተሰብ በጥሩ ያዙ፤ የገቢ ግብር ይቀነሳል፤ … የሚሉ ማባበያና ማስጠንቀቂያ አዘል ንግግሮች ከሰብሳቢዎቹ እንደተደመጡ ዘጋቢው አስረድተዋል፡፡

ይህ በግምገማ ሽፋን የሚካሄደውን የሲቪል ሠራተኞች ስብሰባ ከሌላ ነጻ ምንጭ ለማረጋገጥ ባይቻልም እማኝ ዘጋቢው በላኩልን መረጃ መሠረት ስብሰባው በይፋ እንዳይታወቅ መፈለጉንና ከወረዳ ጽ/ቤቶች ውጪ በሚገኙ ቦታዎች መካሄዳቸውና በዚሁ እንደሚቀጥል አክለው ተናግረዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዙሪያ የታቀደውን ማስተር ፕላን በመቃወም በተማሪዎች የተነሳው ተቃውሞ በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች በመቀጠሉ ከተማሪዎች አልፎ ነዋሪዎች እየተቀላቀሉት እንደሆነ በስፋት ይነገራል፡፡ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በንቅናቄው ምክንያት እስከ 25 ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል፡፡ ከሞቱት መካከል ከአስር ዓመት በታች የሚሆኑ እንዳሉበት የተነገረ ሲሆን በምዕራብ ሸዋ ነዋሪዎች አንዳንድ ከተሞችን በራሳቸው ቁጥጥር ሥር ማዋላቸው ሲነገር ይህንኑ መረጃ አፍቃሪ ህወሃት/ኢህአዴግ የሆኑ የሥርዓቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚዎች፣ ተላላኪዎች፣ አሽቃባጮችና ጭፍን ደጋፊዎች በየፊናቸው አረጋግጠዋል፡፡

ሕዝባዊ ንቅናቄውን የኦሮሞ ብቻ አድርጎ መውሰድና በዚያ መልኩ ፕሮፓጋንዳ መስጠት በኢትዮጵያ ውስጥ በህወሃት ሲረጭ የኖረውን የዘር ጥላቻና መከፋፈል የከፋ ደረጃ ላይ አድርሶ ራስን ለህወሃት መጠቀሚያነት የሚያጋልጥ የሚናገሩ ወገኖች “ኦሮሚያን” እንደ አገር እያሰቡና ሠንደቅ እየያዙ መውጣት በንቅናቄው ላይ ሊጠገን የማይችል አሉታዊ ተጽዕኖ ያመጣል ሲሉ ስጋታችን ይገልጻሉ፡፡ (ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Jaawii says

    December 15, 2015 11:01 pm at 11:01 pm

    Hallo Gulgoole,
    Good that your covering the current situation in Ethiopia and express the overall fear of a risk that the country is going to face. BUT as media outlet be careful with a message you are passing. Yes, the Oromoo people is right now fiercely raising its voice and being killed day and night by brutal government heavy armed forces. Unless others join the Oromoo to make it a national popular uprising, how can you claim it will be a national uprising. You can not stand passive and say criticize by saying “Oromoo is fighting for itself’. The Oromoo people did not say we are fighting for an oromoo nation alone; they say we are fighting for our right. Do not mess up things, please !! You need to give a message that encourage all other oppressed people to genuinely and immediately act in supporting the Oromoo people.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule