• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሕዝባዊው ንቅናቄ ኢህአዴግ ሠግቷል

December 12, 2015 11:25 am by Editor 1 Comment

ለጎልጉል የእማኝ ዘጋቢ (ireporter) የሆኑ በላኩልን መረጃ መሠረት በኢትዮጵያ የተለያዩ ቦታዎች የተነሣው ንቅናቄ ወደ ሲቪል ሠራተኞች ዘልቆ እንዳይገባ ስጋት ውስጥ የገባው ኢህአዴግ ሠራተኞችን ማባበልና ማንቃት ጀምሯል፡፡

በተያዘው ዕቅድ መሠረት በአዲስ አበባ በሚገኙ ወረዳዎች ውስጥ በሲቪል ሠራተኝነት የሚታወቁ ዜጎችን ኢህአዴግ በየቦታው መሰብሰብ ጀምሯል፡፡ እማኙ በላኩት መረጃ እንደገለጹት ለሁለት ቀን በሚካሄደው ስብሰባ በየወረዳው ለሚሰበሰቡ ሠራተኞች ቢያንስ ብር 300 አበል በመስጠት የማባበያ ስብሰባው እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡ በየወረዳው ካለው ሲቪል ሠራተኛ አንጻር ለአበል የታሰበው ብር በሚሊዮን ሊቆጠር እንደሚችል እማኙ ጨምረው አስረድተዋል፡፡

ዋናው አጀንዳ ሲቪል ሠራተኛው እየተካሄደ ባለው ንቅናቄ ተሳታፊ እንዳይሆን፤ እንዳይተባበር፤ ድጋፍ እንዳይሰጥ፤ … ሲሆን ተሰብሳቢዎቹ ወደ ስብሰባው የመጡት የህወሃት/ኢህአዴግ ደጋፊ ሆነው ሳይሆን አለመሳተፍ የሚያመጣባቸውን ከመፍራትና በነጻ ስለሚያገኙት አበል በማሰብ እንደሆነ እማኝ ዘጋቢው ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ሰብሳቢዎቹ “ንቅናቄውን እንዳትደግፉ” ወይም “ማስተር ፕላኑን በተመለከተ የተነሳውን የኦሮሞ ተቃውሞ እንዳትደግፉ” ወይም መሰል ግልጽ ማስጠንቀቂያ ለተሰብሳቢዎቹ እንዳልሰጡ መረጃውን የላኩት እማኝ ዘጋቢ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ይልቅ ግን በተዘዋዋሪ ሁኔታ ከጸረ ልማት ኃይሎች ጋር እንዳትተባበሩ፤ ጸረ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎችን እንዳትደግፉ፤ ተገልጋዩን ኅብረተሰብ በጥሩ ያዙ፤ የገቢ ግብር ይቀነሳል፤ … የሚሉ ማባበያና ማስጠንቀቂያ አዘል ንግግሮች ከሰብሳቢዎቹ እንደተደመጡ ዘጋቢው አስረድተዋል፡፡

ይህ በግምገማ ሽፋን የሚካሄደውን የሲቪል ሠራተኞች ስብሰባ ከሌላ ነጻ ምንጭ ለማረጋገጥ ባይቻልም እማኝ ዘጋቢው በላኩልን መረጃ መሠረት ስብሰባው በይፋ እንዳይታወቅ መፈለጉንና ከወረዳ ጽ/ቤቶች ውጪ በሚገኙ ቦታዎች መካሄዳቸውና በዚሁ እንደሚቀጥል አክለው ተናግረዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዙሪያ የታቀደውን ማስተር ፕላን በመቃወም በተማሪዎች የተነሳው ተቃውሞ በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች በመቀጠሉ ከተማሪዎች አልፎ ነዋሪዎች እየተቀላቀሉት እንደሆነ በስፋት ይነገራል፡፡ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በንቅናቄው ምክንያት እስከ 25 ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል፡፡ ከሞቱት መካከል ከአስር ዓመት በታች የሚሆኑ እንዳሉበት የተነገረ ሲሆን በምዕራብ ሸዋ ነዋሪዎች አንዳንድ ከተሞችን በራሳቸው ቁጥጥር ሥር ማዋላቸው ሲነገር ይህንኑ መረጃ አፍቃሪ ህወሃት/ኢህአዴግ የሆኑ የሥርዓቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚዎች፣ ተላላኪዎች፣ አሽቃባጮችና ጭፍን ደጋፊዎች በየፊናቸው አረጋግጠዋል፡፡

ሕዝባዊ ንቅናቄውን የኦሮሞ ብቻ አድርጎ መውሰድና በዚያ መልኩ ፕሮፓጋንዳ መስጠት በኢትዮጵያ ውስጥ በህወሃት ሲረጭ የኖረውን የዘር ጥላቻና መከፋፈል የከፋ ደረጃ ላይ አድርሶ ራስን ለህወሃት መጠቀሚያነት የሚያጋልጥ የሚናገሩ ወገኖች “ኦሮሚያን” እንደ አገር እያሰቡና ሠንደቅ እየያዙ መውጣት በንቅናቄው ላይ ሊጠገን የማይችል አሉታዊ ተጽዕኖ ያመጣል ሲሉ ስጋታችን ይገልጻሉ፡፡ (ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ)

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Jaawii says

    December 15, 2015 11:01 pm at 11:01 pm

    Hallo Gulgoole,
    Good that your covering the current situation in Ethiopia and express the overall fear of a risk that the country is going to face. BUT as media outlet be careful with a message you are passing. Yes, the Oromoo people is right now fiercely raising its voice and being killed day and night by brutal government heavy armed forces. Unless others join the Oromoo to make it a national popular uprising, how can you claim it will be a national uprising. You can not stand passive and say criticize by saying “Oromoo is fighting for itself’. The Oromoo people did not say we are fighting for an oromoo nation alone; they say we are fighting for our right. Do not mess up things, please !! You need to give a message that encourage all other oppressed people to genuinely and immediately act in supporting the Oromoo people.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
Copyright © 2026 · Goolgule