• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ትምህርት ቤታችን እና ኮሚኒቲውን የከበበው አደጋ …!

February 5, 2014 10:06 pm by Editor Leave a Comment

የመምህራን ማስጠንቀቂያ …

ሰሞነኛው የጅዳዎች ጉዳይ የመኖሪያ ፈቃድን በማስተካከል ዙሪያ ቢሆንም ከ 3000 (ከሶስት ሽህ) በላይ ታዳጊዎችን የሚያስተናግደው የጅዳው አለም አቀፍ ት/ቤት አሁንም አደጋ ላይ መሆኑን እየሰማን ዝም ብለናል!  ከሳምንታት በፊት መምህራን አመጽ አድርገው ነበር። ከቀናት በፊትም  25 መምህራን ስብሰባ ተቀምጠው፣ በአንድ አቋም ጸንተው ጠንከር ያለ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል። ላለፉት 8 ወራት በትምህርት ቤቱ ባለቤት በኮሚኒቲው ጉዳያቸው ቢያዝም እስካሁን ከወሬ ያላለፈ አርምጃ አለማየታቸውን ገልጸዋል።  25 ቱ school letterመምህራን ለትምህርት ቤቱ አስተዳደር፣ ለኮሚኒቲው፣ ለጅዳ ቆንስልና ለወላጅ መምህራን ህብረት ባስገቡት ደብዳቤ እስከ ቀጣዩ ሳምንት የሁለተኛው የትምህት አጋማሽ መጀመሪያ የመኖሪያና የስራ ፈቃዳቸው ተስተካክሎ ካልተሰጣቸው  በማስተማር መደበኛ ስራቸው እንደማይገኙ በላኩት የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ማስጠንቀቃቸውን በእጀ የገባው ሰነድ ያመላክታል!

የወላጅ መምህራን ህብረት ስብሰባ ጥሪ …

“ወላጅና መምህራን ህብረት” በሚል ካች አምና በመንግስት ትዕዛዝ የወላጅ ኮሚቴን የተካው ኮሚቴ በትምህርት ቤቱ ዙሪያ ለመምከር ለወላጅ ስብሰባ ጠርቷል። ኮሚቴው የሳውዲን የምህረት አዋጅ ማለቅ ተከትሎ የጅዳ አለም አቀፍ ትምህርት ቤት ለሳምንት ሲዘጋ የሚወክለውን ወላጅም ሆነ መምህራኑን ብሎ ድምጹን አላሰማም። ትምህርት ቤቱ ካንድም ሁለት ሶስቴ በመምህራን ስራ ማቆም አድማ ሲናጥ፣ ከፍተኛ የማህበረሰቡ መዋዕለ ንዋይ ከመጋረጃ ጀርባ ለሚደረጉ የመምህራን እና ሰራተኛ ዝውውር መባከኑ ሲሰማ የዝሆን ጀሮ ስጠኝ ማለቱ አይደንቅ ይሆናል። የመንግስት ሃላፊዎች ትኩረትና ጥበቃ የማይደረግለትን  የትምህርት ማዕከል ህልውና ለማስጠበቅ ስብሰባ መጥራትና ወላጁን ባለማማከሩ ተወቃሽ ከመሆን ግን አላመለጠም። ለሚታየው እንግዳ፣ ለሚሰማው ባዳ መሆናቸው ያስከፋው ወላጅ ከትናንትም ዛሬ ተስፋ ቆርጧል።

ዛሬ የወላጅ መምህራን ህብረት ተብየውን ምን እንዳሰናከለው፣ ምን እንዳሽመደመደው መስማት ባያጓጓም የወደፊት የወላጁን፣ የመምህራንንና የታዳጊዎችን ትምህርት ቤት አደጋ ላይ መውደቅ  እያየ ስለያዘው አቋም መስማት ጓጉተናል። ማስታወቂያ ባወጣ በሳምንቱ፣ ስብሰባውን ሊያደርግ ቀናት ሲቀሩት ደግሞ ዛሬ ምሽት የህብረቱ አመራሮች በጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ሃላፊዎች ለአስቸኳይ ስብሰባ ተጠርተዋል። አሁንም ኮሚቴው በዚህ ስብሰባ ምን በል ሊባልም ሆነ ከወላጅ መምህራን ጋር በሚደረገው ስብሰባ ላይ እንዳይነካ የሚፈለገውን ቦታና  እንዳይታለፍ የሚፈለገው የቀይ መስመር ገደብ ምን ሊሆን እንደሚችል አንገምትም።  ብቻ ሁነኛ ባለቤት አጥቶ አንደ ስደተኛው ተገፊ ወገን ለሚከላተመው የ3000 ታዳጊዎች ትምህርት ቤት መጻኢ ህይዎት ወላጁ በስብሰባው በመሳተፍ መምከር ይኖርበታል።sch letter

በመግስት ሊደራጅ ያታቀደው ኮሚኒቲ …

ዛሬ ያለው ኮሚኒቲ በአዲስ የመተኪያው የምርጫ ጊዜ በቆንስል መስሪያ ቤቱ ትዕዛዝ ተላልፏል። የሚተካው ኮሚቴ ደግሞ የሚደራጀው በመንግስት እንደሆነ እየተነገረን ነው። የምርጫው መዘግየትም ዋናው ምክንያት ይህ እውነት መሆኑ ቆንስል መስሪያ ቤቱ ከመካከለኛው ምስራቅ አገኘሁ ያለውን ሞዴል የኮሚኒቲ ህግና ደንብ ረቂቅ ጊዜውን ለጨረሰው ኮሚኒቲ ይፋ አድርጎታል። ቅንነት በሌለበት መንደር በወረቀት ላይ በሰፈረ ህግና መመሪያ ለወጥ ያመጣ ይመስል የማይገባ ስራ መሰራት ተጀመሯል። የሚጠፋውን ጊዜና የሚባክነውን የማህበረሰብ ንብረት ብክነት ነዋሪው ህብረት ፈጥሮና ማህበሩን ከፖለቲካና ከድርጅት አደረጃጀት ጣለቃ ገብ ሂደት በማስቆም ነጻ ካላወጣው አደጋው የከፋ እንደሚሆን ጥርጣሬው ያየለብኝ ለእኔ ብቻ ቢሆን መልካም ነበር ። ግን አይደለም። ብዙ ነዋሪ አዲሱን አካሄድ አልወደደውም!

ኮሚኒቲውን በአንድ ባንዴራ ስር ከማደራጀት ተወጥቶ በብሔር ብሔረሰብ ስብጥርና የፖለቲካ ድርጅት ሰወች በኮሚኒቲው በማሰግሰግ የሰራነው ስራ እንዳላዋጣን እናስተውለው። ወላጁም ሆነ አብዛኛው የጅዳና አካባቢው ነዋሪ ለአመታት የራቀው ኮሚኒቲ የጥቂቶች መፈንጫ ከሆነ ወዲህ የሆነውን ቆም ብለን እናስብ! እናም ቢያንስ በልጆቻችን ትምህርት ቤትን ህልውና ለማስጠበቅ ኮሚኒቲውን ሊውጠው ከተዘጋጀ ክፉ አውሬ አፍ ለማዳን እንረባረብ!  በኮሚኒቲውና በትምህርት ቤቱ ዙሪያ በሚደረጉ ስብሰባዎች ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የልጆቻችን ትምህርት ቤት ለመታደግና ለህልናው ወሳኝ የሆነውን ኮሚኒቲ ከወደቀበት አዘቅት አውጥተን ለብሩህ ተስፋ ሂደቱ እንታደገው፣ እናጎልብተው!  ወላጅና መምህራን ህብረት በጠሩት ስብሰባ ተሳታፊ እንሁን፣ በነጻነት ሃሳባችን እናንሸራሽር! የልጆቻችን ትምህር ቤተችን ከአደጋ እንታደገው!  ይህ ማንም የማይገሰው መብታችን ነውና!

ጀሮ ያለው ይስማ!

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule