• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትግሬዎች መንግሥት አወዳደቁና ክፋቱ!

August 18, 2016 12:00 am by Editor Leave a Comment

ባሁን ሰዓት፤ በገዥነት ሕልሙ እየተንሳፈፈ ካለው የትግሬዎች ቡድን በስተቀር፤ ኢትዮጵያን አደጋ ላይ የጣላት ይሄው ቡድን፤ የውድቀት አፋፉ ላይ መሆኑ ለሁላችን ግልጽ ነው። አሁን ካለንበት ሰዓት እስከመጨረሻው ውድቀቱ ያለው ጊዜ ግን፤ በጣም የከፋና የተመሰቃቀለ ነው። ይህ የሚሆነው፤ ከፊል በዚህ ወራሪ ቡድን ተግባር ሲሆን፤ ከፊሉ ደግሞ በኛው በታጋዩ ክፍል ያለነው ለዚህ ውድቀት በማድረግና ባለማድረግ ላይባለው ሂደታችን ነው። በተጨማሪ ደግሞ፤ የሃያ አምስት ዓመት የዚህ ቡድን ፀረ-ኢትዮጵያ አገዛዝ፤ ሀገራችንን ለከፋ ወደፊት አዘጋጅቷታል። ሀቁን ተቀብለን ከአሁኑ መደረግ ያለበትን ካላደረግን፤ በኋላ ይሄን ብናደርግ ኖሮ ብለን የመቆጫ ሰዓት አናገኝም፤ ያኔ ሁኔታውን አንገዛውምና!

ይህ ወራሪ ቡድን፤ የመጨረሻ እስትንፋሱን የሚያወጣው በቃሬዛ ነው።ሕዝቡ አቸናፊ ሆኖ እንደሚወጣ ምንም ዓይነት ብዥታ ባይኖረንም፤ የሚከተለው ምን ይሆን?የሚለው ስጋትሀቅ ነው። ያንን ሳጋት የበለጠ ለማክፋት ይህ የትግሬዎች ቡድን ሲጥር፤ ታጋዩ ክፍል የሚሠጠው መልስ ወሳኝ ነው። ህዝቡ ማቸነፍ የሚችለው፤ ከዚህ ቡድን በልጦ ሲገኝ ነው። ጎልብቶ ሲገኝ ነው። ጎብዞ ሲገኝ ነው። ይህ ቡድን ምን እያቀደ ነው? ብሎ ቀድሞ ሲዘጋጅ ነው። ምን ሊያደርግ ይችላል? የሚለውን ወስዶ አደናቃፊ ዝግጅቶችን ሲያሰላ ነው። አስኪ ይህ ቡድን ሊያደርጋቸው የሚችሉትን እንመልከት፤

  • እንዳየነውና እንደሰማነው፤ አልቃይዳ ወይንም አልሸባብ ወይንም አይሲስ ብሎ ታጋዩን ያልሆነ ቀለም በመቀባት፤ የውጪ ሀገሮችን ድጋፍ ለማግኘት ይጥራል። አይሆንም ማለት ሞኝነት ነው። ዛሬም ድረስ በሺር አል አሳድ ሶሪያን የሚገዛው፤ አሜሪካና አውሮፓ በከፍተኛ ድጋፍ ተቃዋሚዎቹን ቢረዱም፤ በሶቪየቶችና ቻይናዎች ድጋፍ ነው። እኒህም ሆኑ ሌሎች ሀገራት፤ ስሌታቸውን የሚያተኩሩት፤ ለኔ ሀገር ሁኔታው ምን ያስገኝልኛል? ብለው ነው።
  • ከዚህ አያይዞ፤ የውጭ ቅጥረኞች በማለት ታጋዮችን በሀገር ቤት ለማስጠላት ይሞከራል። እያደረገውም ነው። ይህ፤ ጊዜ ለመገብያ የሚጠቀምበት ዘዴ ነው። ወረሩኝ ብሎም ጦርነት በጎረቤት ሀገሮች ሊከፍት ይችላል። ይህ ሁሉ፤ የሕዝቡንና የታጋዩን እንቅስቃሴ ለማለዘብ ነው። ጊዜው አልፏል።
  • ዋናው የዚህ የትግሬዎች ቡድን አስከፊ ተግባር፥ ጉልበቱን መጠቀም ነው። ይህ እብሪተኛ ቡድን መቼም ቢሆን የሚተማመነው፤ “ጉልበቴ ከሁሉም ይበልጣል!” ብሎ ነው።አሁንም ሁሉን ነገር “በጉልበቴ እወጣዋለሁ!” ብሎ፤ አረመኔያዊ ተግባሩን ቀጥሎበታል። ነገሮችን አጢኖ መመልከት ድክመት ይመስለዋል። በሰላም ባዶ እጁን አቤቱታ ሊያሰማ የወጣውን ሕዝብ፤ እስካፍንጫው የታጠቀ አጋዚ አሰልፎ በቀጥታ በሰልፉ ላይ በመተኮስ አሁን በመቶዎች የሚቆጠሩትን እየገደለ ነው። ነገ ደግሞ በሺዎች የሚቆጠሩትን ይረሽናል። እስኪሞት ድረስ ሌላ ዕውቀት የለውም። ካልገደለ ውሎ የሚያድር አይመስለውም። ሕዝብ ቆርጦ ከተነሳ፤ መመለሻ የሌለው መሆኑን ሊረዳው አይችልም። የዚህ ቡድን መነጽር፤ የተቃወመኝን ገድዬ፤ ጉዳዩን አጠፋለሁ ነው።
  • ታጋዩን ከሕዝቡ ለመነጠል ይጥራል። ደደብ ሆኖ ነው እንጂ፤ ታጋዩ እኮ ሕዝቡ ነው! ሊገባው አይችልም። ታጋዩን ሊከፋፋል ይሞክራል። ታጋዩን እኮ፤ ከዚህ ቡድን ሕልውናና ጥፋት የበለጠ የሚያንገበግበው የለም። ለነገሩ ይህ አዲስ አይደለም። እስከዛሬ ያቆየው፤ የሕዝቡ በአንድ አለመነሳት ነበር። በዘር፣ በሃይማኖትና በጥቅም መከፋፈሉን ተክኖበታል። አሁን ግን ሕዝቡ ይህን ሁሉ ጥሶ እንዲወጣ የዚህ ቡድን ለከት የለሽ በደል አስገድዶታል።
  • “አሸባሪዎች ናቸው!” ብሎ ማላዘን የዕለት ተግባሩ ነው። ነገ ደግሞ የየሰዓት ጸሎቱ ይሆናል። ለዚህም የሃይማኖት አባቶችን አሰልፎ ያስወግዛል፣ ይማጠናል፣ ያባብላል። የቤተክህነትና የመስጊድ መሪዎችን አቅርቦ ሊናዝዝ ይቻላል። አብሮም ሆዳም የመንግሥት ሠራተኞችንና የጦር መሪዎችን አሰልፎ ሊያስወግዝ ይቻላል።
  • መላ የፌዴራልና የክልል አስተዳደራዊ መዋቅሮችን የስለላ ድርጅት ያደርጋቸዋል። እያንዳንዱን ትግሬና የስመ ኢሕአዴግ አባል ተራ ሰላይ ያደርጋል። ከታጋዩ ከድተው ወደኔ ገቡ ብሎ የውሸት ታጋዮችን በቴሌቪዥን ሊያቀርብ ይችላል።ተዘረፈ ብሎ የመንግሥትን ካዝና ወደ መቀሌ ሊያሻግረው ይችላል። ይህ ቡድን ሌብነት ኒሻኑ ነው።
  • ለመታያ የተቀነባበረ የሱ ደጋፊ ሰላማዊ ሰልፎችና ትዕይንቶች ሊያዥጎደጉድ ይችላል። በማስፈራራት፣ በመደለልና በማስገደድ ሰልፍ እንዲወጡ ሊያደርግ ይችላል። ይህን ማንም አይስተውም። ሆኖም ግን የራሱን የመንፈስ ጭንቀት እንኳን አይበርድለትም። አምባገነን መንግሥታት ሙያቸው ነው። ትናንት መንግሥቱ ኃይለማርያም አድርጎታል።
  • ሲያስበረግገው የሚያድረው የሕዝቡ ቁጣ፤ በፓልቶክ፣ በፌስቡክ፣ በሬዲዮና በድረገጾች ላይ ዘመቻውን እንዲያበዛ ያደርገዋል። መስሎት ነው። ኢንተርኔቱን ይዝጋው፤ ሕዝቡ በኢንተርኔት ሳይሆን በሚኖርበት ሀቅ ተገፋፍቶ ነው የተነሳው። ፓልቶክ ደግሞ ሕዝቡን ወደ አንድ አመጣና በትክክለኛው ጠላቱ ላይ እንዲያተኩር ረዳው እንጂ፤ ችግሩ ያስተዳደር በደል ነው። የዜና ልውውጡን ሊያግት ቢሞከርም፤ በየቦታው ያለው የሱ ግፍ ያነሳሳው ነው።
  • በማታለልና በማውገርገር የተካነው ይህ የትግሬዎች ቡድን፤ እደራደራለሁ፣ ለውጥ አደርጋለሁ፣ ሽምግልና እገባለሁ ሊል ይቻላል። ይህን እያለ ግን፤ በጎን በከፋ ሁኔታ ያው መግደሉን ይቀጥልበታል። ይህን የሚለው ጊዜ ለመግዣ ብቻ ነው። ተገዶም ቢሆን ለድርድር ቢቀርብ፤ ሥልጣኑን ማጋራት ወይንም የሰረቀውን ሀብት መመለስ አይፈልግም። ሥልጣኑን የሚያስረክበው ወድሞ ነው።

ይህ ሁሉ ተግባሩ፣ አንድ ቀና አንድ ሌሊት ሊገዛለት ቢችልም፤ በአንጻሩ ግን፤ ትግሉን በትግሬዎችና በኢትዮጵያዊያን መካከል በማድረግ፤ የትግራይን ሕዝብ ለነገ ዕልቂት ያዘጋጀዋል። ይህ እየመጣ ያለ ሀቅ ነው። በርግጥ አሁን ሊለወጥ የሚችልበት ሰዓት ነው። ይህን ደግሞ እንደሚከተለው አቀርበዋለሁ።

ምንም አንኳ ይህን ፈጻሚው የትግሬዎች ቡድን ቢሆንም፤ በዚያው አኳያ፤ የታጋዩ ክፍል ጥረት፤ ሊያስተካክለው ወይንም ሊያባብሰው ይችላል። በአሁኑ ወቅት ታጋዩ ያለበት ሁኔታ አመቺ አይደለም። በርግጥ ሕዝቡ ራሱ እየመራ ያለበት ይህ እንቅስቃሴ፤ ወደፊት እንዲሄድና ለስኬት እንዲበቃ፤ መልክ መያዝ አለበት። ማዕከል ሊኖረ ይገባል። ይህ ማለት፤ አሁን ካሉት ድርጅቶች አንዱ ወይንም ሌላው ይምራው ማለት አይደለም። አሁንም መሪው በቦታው ሕይወቱን እየከፈለ ያለው ሕዝቡ ራሱ ነው። ታዲያ በውጪም ሆነ በሀገር ውስጥ ያለን የታጋዩ ክፍል ነን የምንል ሰዎች፤ እገዛችን መሆን ያለበት፤ ይህን ሕዝባዊ አካል መርዳትና ማጠናከር ነው። ለዚህ አመራር ተገዥ መሆን ነው። በየቦታው በመደረግ ላይ ያለው ሰላማዊ ሰልፍ፤ እንዲያው ከየሰማዩ ዱብ ዱብ ያለ አይደለም። ሕዝባዊ ቅንጅት አለው። ወጣቶቹ ከፍተኛውን መስዋዕትነት እየከፈሉ ያዋቀሩት የደማቸው ሐረግ ነው። ይህን ማጎልበት አለብን። የኔን ድርጅት ወይንም የኔን ድርጅት እያልን፤ ድርጅቶቻችን በሕዝቡ ላይ ለመጫን ያጎበጎብነው፤ ልጓማችንን መያዝ አለብን።

ጎንደር የተሰለፉት ወጣቶች፤ የእስልምና ተከታይ ወኪሎችና የኦሮሞ ወጣቶች ጉዳይ ጉዳያችን ነው!አሉ። የኦሮሞ ወጣቶች ተከትለው፤ ጠላታችን አማራ አይደለም ጠላታችን ወያኔ ነው! አሉ። የትግሬዎችን ቡድን አከርካሪ ሰበሩት። ይህ በተግባር መያያዝ አለበት። ጊዜውና ምቾቱ ያለን እኛ በውጭ የምንገኝ ይሄን አንድነትን የመፈለግ ጥረት ማጎልበት እንችላለን። አለዚያ፤ እንደ ግብፁ ሙባረክ ሳይሆን እንደ ሶሪያው አሳድ የተጓተተና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ብዙ ታጋዮች የሚያልቁበት ሀቅ መልበሳችን ነው።ግንቦት ሰባት የራሱን ንጉስ ለማንገስ ሲሯሯጥ፣ ኢሕአፓ የራሱን ለማንገስ ሲጣደፍ፣ ሰላማዊ የራሱን፣ መድረክ የራሱን ሲያዘጋጅ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል፤ አንድነት አጥቶ፤ ይጓተታል። ሶሪያ ውስጥ የየውጪ ሀገሮች፤ ማለትም የቱርክ፣ የሊባነን፣ የኩዌት፣ የአሜሪካ ደጋፊ ታጋዮች ተለያይተው በየበኩላቸው ባንድ በኩል፤ ሶቪየት ኢራንና ቻይና ደግሞ የአሳድን ማዕከላዊ መንግሥት ደግፈው፤ የሶርያ ሕዝብ እያለቀ እንዳለበት ሀቅ፤ ተያይዘን እንዳንሰምጥ እሰጋለሁ።

አንድነት አለመሰለፋችን ትግሉን ጎድቶታል። አንድ ጠላት አለን ብቻ ሳይሆን፤ ሁሉም ድርጅቶች ሕዝቡ የበላይና ወሳኝ ነው ብለዋል። ታዲያ ይሄን ከተቀበሉ፤ ለምን የየራሳቸውን ጥንካሬ አጉነው፤ ሌሎችን እንደሌሉ በመቁጠር ይሯሯጣሉ? ለምን ሀገርን በማስቀደም የትግሉ አካል ለመሆን ፈቃደኛ አይሆኑም? ይህ ተጠያቂነታቸውን ያጎላዋል። ይህ ትግሉን በመጎተት ያስጠይቃቸዋል። የትግሬዎች ቡድን የሚያደገውን ጥፋትና የሚያደርሰውን በደል መዘርዘሩ በቂ አይደለም። ባሁኑ ሰዓት ደግሞ፤ ሕዝቡ ደሙን እያፈሰሰ ባለበት ወቅት፤ ስለ በደሉ መዘርዘር ትርጉም አጥቷል። አሁን ትግሉ ወደፊት መሄዱንና የድል ጎዳና መቀየሱን ነው ማብሰር ያለብን። አሁን፤ የሕዝቡን ድል መዘርዘር ላይ መሆን አለብን። ይህ ግን በምኞት አይመጣም። ተጨባጭ ሥራዎችን መሥራት አለብን። ይህ ደግሞ የሚጀምረው፤ ትግሉን በአንድነት ለማድረግ ወደ አንድ በመሰባሰብ ነው። ምንም እንኳ ይህ የአንድነት ጥሪ ለፍቶ ለፍቶ የሟሸሸ ቢሆንም፤ አሁን ክፍተት ተፈጥሮ ማዕከሉ ባዶ ሲሆን፤ እንደ ትግሬዎች ቡድን ዘሎ ለሚገባ የታጠቀ ቡድን በሩን በርግደን እንዳንተው እፈራለሁ። ሕዝባዊ ድል የሚገኘው፤ ሕዝቡ ሲመራና ሲታገል ብቻ ነው። ድርጅቶች የሚታገሉት ለድርጅታቸው ነው። የሕዝብ ድርጅት ደግሞ የለንም።

ከታላቅ አክብሮታ ጋር

አክባሪያችሁ  አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ

ሐሙስነሐሴ፲፪ ቀን ፳፻፰ ዓመተ ምህረት( 08/18/2016 )

eske.meche@yahoo.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule