• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመለስ ዜናዊ ራእይ

March 6, 2016 07:09 am by Editor 2 Comments

መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያ የጠላት ጠላት ደመኛ ጠላት ነው። ከአባቱ፣ ከእናቱና ከአያቶቹ የወረሰው በኢትዮጵያና በሕዝቧ ላይ የፈጸመው ግፍ፤ የሃገር ማፍረስ ድርጊት በታሪክ የማይረሳ ነው። እሱ ብቻ ሳይሆን የህወሓት አመራርንም ይጨምራል። የስም ዝርዝራቸውን በተለያዩት ጽሁፎቼና ከዚህ በላይም ስላካተትኳቸው እንሱን መመልከትና ማመሳከር ይቻላል።

የመለስ ዜናዊ ራእይ በኢትዮጵያ ልማት፣ እድገት፣ ዲሞክራሲ ማለትስ ምን ማለት ነው? በእርሱ አመራር ለ21 ዓመታት ኢትዮጵያ በልማትና በዲሞክራሲ አብባለች የሚሉት የህወሓት ደጋፊዎችና አጋር ድርጅት ተብለው የሚጠሩት ጸረ-ሕዝብና ጸረ-ኢትዮጵያ ስብስብ ብቻ ናቸው። ብዙ ለሆዳቸው ያደሩም አሉባቸው። ነገሩ የተጋላቢጦሽ ነው። መለስ ዜናዊ የሚመራው ህወሓትና አመራሩ በተፈጥሮው ጸረ-ሕዝብና ጸረ-ዲሞክራሲ ነው። ህወሓት አፈጣጠሩ አምባገነን እና ፋሽስት፣ እንዲሁም ጸረ-ዲሞክራሲ ሆኖ ያደገ ከመቅጽበት የልማት፣ እድገትና ዲሞክራሲ አራማጅ ሊሆን አይችልም። ጎባጣና ጠማማ ሆኖ ያደገ ባህር ዛፍ ተቃንቶ ለኤሌክትሪክ ምሰሶ ወይም ለቤት መስሪያ ማገር ልታደርገው አትችለም። በምሳር ቆራርጦ ማገዶ ከማድረግ ውጪ። ህወሓትን በዚህ አይነት ልንመለከተው ይገባል። ስለሆነም የመለስ ዜናዊ ራእይ ጸረ-ሕዝብ፣ ጸረ-ልማት፣ ጸረ-እድገት፣ ጸረ-ዲሞክራሲ ነው። መለስና ግብረአበሮቹ በዘር ማጥፋት ወንጀል የተሰማሩ፣ በሙስና የሕዝብና የሃገር ሃብት የዘረፉ፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ በፋሽስት መዋቅራቸው ያሰቃዩና የገደሉ ናቸው። እንደዚህ ያለ ጨቋኝና ፋሽስት መንግስት ልማታዊ ሊሆን አይችልም።

መለስ ዜናዊና ህወሓት ለኢትዮጵያና ሕዝቧ ምን ናቸው? በመለስ ዜናዊና በስብሃት ነጋ የሚመራው ፋሽስት ፓርቲ፣ ኢትዮጵያን ከግንቦት ወር 1983 ጀምሮ ከተቆጣጠሩ ወዲህ ኢትዮጵያና ሕዝቧ በወያኔ ሀውሓት ቅኝ አገዛዝ የወደቀችበት ወቅት ሆኖ፣ እነሆ ቅኝ ገዢው ህወሓት በሃገራችን አረመኔያዊ ድርጊት እየፈጸመ ይገኛል። በመለስ ዜናዊ የአገዛዝ ዘመን የኢትዮጵያ ሉአላዊንት ፈርሷል። ጥንታዊና ታሪካዊ የቀይ ባሕር ወደቦቿን አጥታለች። ሕዝብ በዘሩ እየታየ የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሟል። ስለዚህ መለስ ዜናዊና ህወሓት እንዲሁም አመራሩ የኢትዮጵያ ደመኛ ጠላት ናቸው።

መለስ ዜናዊ የወታደራዊ ሳይንስና ስትራተጂ ባለ ራእይ ይባላል። ይህ አነጋገር ደረቅ ውሸት ነው። መለስ ዜናዊን የሚያውቁና አብረውት በትግሉ የነበሩ ታጋዮች የማይቀበሉት ጉዳይ ነው። የህወሓት መንጋ በምን ዓይነት የውሸት አዘቅት ውስጥ እንደሰመጠ በግልጽ የሚያሳይ ነው። መለስ ዜናዊ ከትግሉ መጀመሪያ አንስቶ ለብዙ ዓመታት አብረን ተጉዘናል። በጣም የሚተማመንብን ጓደኞቹ ተክሉ ሃዋዝና እኔ ገ/መድህን አርአያ ነበርን። በሚገባ ስለምናውቀው የወታደራዊ ስታርቴጂስት አልነበረም። እውቀቱም ችሎታውም ፈጽሞ አልነበረውም። ሃቁ ይህ ነው።

“ጅብ በማያውቁት ሃገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ” እንዳለው ዓይነት ነው። መለስ ዜናዊ ከፈሪነቱ የተነሳ በተለያዩ ጦርነቶች ፈርቶ የሸሸ፣ በህወሓት ታሪክ ውስጥ በፈሪነቱ ቀዳሚውን ስፍራ የያዘ ግለሰብ ነው። ከሸሸባቸው ጦርነቶች ለአብነት፤

  1. በ1969 ከአድዋ ኦፐሬሽን ጦርነቱ እንደተጀመረ ፈርቶ የሸሸ፣
  2. በ1970 ከአዲ ደእሮ ፈርቶ የሸሸ፣
  3. በ1971 መጀመሪያ ላይ ከማይቅነጠል ውጊያ ፈርቶ የሸሸ፣
  4. በ1971 ህዳር ወር ከፈረስ ማይ ጦርነት ፈርቶ የሸሸ፣
  5. ሰኔ ወር 1971 ከሃገረ-ሰላም ውጊያ ታመምኩ ብሎ መሬት ላይ ሲንከባለል በበቅሎ ተጭኖ እንዲምለስ የተደረገው  ናቸው። በምስክርነት የሰራዊቱ የጦር አዛዥ አረጋዊ በርሄ የሚያውቀው ጉዳይ ነው።

በህወሓት ውስጥ ማንም ታጋይና አመራር የሚያውቀው ሃቅ አለ። ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጂ የነደፈው ጥናት እያደረገ ወታደረአዊ ስትራተጂ ወታደራዊ ታክቲክ የአሸዋ ገባታ ለረጅም አመታት ጥናት በማካሄድ የጻፈና ያዘጋጀ ብቸኛው አረጋዊ በርሄ ነው። ለሁሉም ወታደራዊ አመራር ስየ አብርሃ፣ ሃየሎም አርአያ ወዘተ. አስተምሮ ያሳደጋቸው አረጋዊ በርሄ ነው። ስየ አብርሃ ይሁን ሌላው የሚኩራሩበት ውሸት ነው። ወያኔ ህወሓት እስከ አሁን የሚጠቀሙበት ወታደራዊ ጉዞ በአረጋዊ በርሄ የተዘጋጀ እንጂ መለስ ዜናዊ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ ወታደራዊ ሳይንስ ይሁን ስትራተጂ የጤፍ ቅንጣት የምታክል እውቀት አልነበረውም። ሁሉም የሚዋሸው ለሆዱ፣ ለጥቅሙና የሙስና ዘርፊያውን በስፋት ለመቀጠል ስለሚፈልግ የሚመታው የውሸት ነጋሪት ነው።

ግደይ ዘርአጽዮን ከህወሓት ወጥቶ ወደ ስደት ሲሄድ በህቡር ገብረኪዳን መሪነት ተክለወይን አሰፋ፣ ተሻለ ደብረጽዮንን ጨምሮ ተፈትሾ የያዘውን ሰነዶች ሁሉ፣ ብጣሽ ወረቀት ሳትቀር፣ ጠራርገው በመውሰድ ባዶ እጁን ሱዳን ገባ።

አረጋዊ በርሄ፣ ህቡር ገ/ኪዳን፣ ስብሃት ነጋ፣ አርከበ እቁባይ ሁነው ለብዙ ዓመታት ሲያካሂዱት የነበረውን ወታደራዊ ጥናትና ስትራተጂ የአሸዋ ገበታ፤ በትልልቅ ወረቀቶች ላይ በሰእል መልክ የተዘጋጁ ጠቅላላ ወታደራዊ መጻሕፍት ብጣሽ ወረቀት ሳትቀር በሁለት የማዳበሪያ ከረጢት ሞልተው የወረሱትን በታጋዮች አሸክመው ለመለስ ዜናዊ አስረከቡት። ‘በሰው ደንደስ በርበሬ ተወደሰ’ እንደተባለው፣ መለስ ዜናዊ ባልሰራውና በማያውቀው ወታደራዊ ስትራተጂ የአሸዋ ገበታ ንድፈ ሃሳብና አረጋዊ በርሄ ደክሞ ያዘጋጀው ነው። አሁን ወያኔ የሚጠቀምበት ወታደራዊ አካሄድ የአረጋዊ በርሄ ሥራና ጥናት ነው። ባልሰራኸው፣ በማታውቀው ጥበብ የራስህ አስመስለህ መጠቀም ያስንቃል፣ ያዋርዳል። ስለዚህ መለስና የህወሓት መንጋ ውሸታምና በምን ዓይነት ድቅድቅ የውሸት ጨለማ እንደተዘፈቁና ማንነታቸውን እንዲያውቁ ይህንን የጽሑፍ ሰነድ እዚህ ላይ ያንብቡ። (ፎቶ: መለስ ዜናዊ ጥይት ማይበሳው ብርጭቆ ቤት ውስጥ በመስቀል አደባባይ ንግግር ሲያደርጉ – REUTERS/Thomas Mukoya)

ገብረመድህን አርአያ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    March 8, 2016 05:15 pm at 5:15 pm

    Ayt minim bitinterara zihon athonim
    Mele is a giant

    Reply
  2. Dana Tolosa says

    March 21, 2016 10:55 am at 10:55 am

    This is written out of hate including honorable exit primer minister MZ and his families. Anyone can understand this read it again

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule