• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘረኝነት ፈጣሪዋን ልታጠፋ ነው

December 13, 2017 12:34 am by Editor Leave a Comment

አባቶች “ሥራ ለሠሪው እሾህ ለአጣሪው” እንዲሉ ኢትዮጵያውያንን ከፋፍሎ ለመግዛት ዘረኝነትን ፖሊሲው ያደረገው ህወሃት ለሃያሰባት ዓመት ኮትኩቶና ውሃ እያጠታ ያሳደገው ዘረኝነት ወይም የጎሰኝነት ገመድ አንገቱ ላይ ተጠምጥሞ መተንፈሻ እያሳጣው ነው። ሰው በሰውነቱ ከዚያም ዝቅ ሲል በዜግነቱ ወይም በኢትዮጵያዊነቱ መከበር ሲኖርበት፣ ህዝቡን በጎጥ አጥር ከትቶ እርስ በርሱ እንዲጋደል ወያኔ ሌት ተቀን ሠርቷል። ለዘመናት የቆየው ኢትዮጵያዊ ትስስርና ባህሉ ህዝቡን በአንድነት ቢያቆየውም  ብዙ ዜጎች በማንነታቸው ተገድለዋል፣ ታስረዋል፣ ተዘርፈዋል፣ ተሰደዋል፣ ተንገላትተዋል። ጊዜ ይውሰድ እንጂ ኢትዮጵያውያን የወያኔ ተንኮል ከመረዳት አልፈው በቃህ በሚል ፍጻሜውን ለማቅረብ እየተንቀሳቀሱ ነው።

ዓለምን ያስደነገጠው የሩዋንዳ እልቂት ተመሳሳይ ቋንቋ፣ ባህልና እምነት ያላቸውን ሩዋንዳውያን ቅኝ ግዥዎቹ  በፊት ገጽታ፣ በፍንጫ ቅርፅ ልዩነት ብቻ ከፊሉን ቱትሲ ቀሪውን ሁቱ ብለው በመከፋፈል መታወቂያ ካወጡላቸው በሁዋላ አንድ እንዳይሆኑ ያስፋፉት የልዩነት ቅስቀሳ ነበር የሚሊዮኖችን እልቂት ያስከተለው። ጎረቤት ሶማልያ ህዝብዋ አንድ ቋንቋ፣ አንድ ሃይማኖት፣ አንድ ባህል እያለው ሰላሳ ዓመት የተጠጋ ብጥብጥ፣ መጋደል፣ መሰደድና እንደሃገር ያለመኖር ጦስ ውስጥ የገባው የጎሳ ልዩንትን እንደወያኔ ያሉ የስልጣን ጥመኞች ስለአጦዙት ነው። የዘር ፖለቲካ አጥፊ ለመሆኑ ብዙ የዓለም አገራትን ምሳሌ ማቅረብ የሚያስፈልገን አይደለም። ከየቀየው የተፈናቀሉ፣ ገደል የተጣሉና የተዘረፋ አማሮች፣ ኦሮሞዎች፣ ሲዳማዎች፣ በቅርቡ የተፈናቀሉ ግማሽ ሚሊዮን የሚሆኑ ኦሮሞዎች፣ ዛሬ በየዩኒቨርስቲው የሚገደሉ ኦሮሞ፣ አማራና ትግሬ ወጣቶች ምስክር ወይንም ትምህርት አይሆነንም ወይ? በዚህ ግድያ፣ በዚህ ስደት፣ በዚህ መፈናቀል ማን ነው የሚደሰትው? ዘረኝነትን ከሚያቀነቅነው ከይሲ ወያኔ በቀር!

ወያኔዎች ኢትዮጵያውያንን በመታወቂያቸው ላይ እያስገደዱ ብሄራቸውን ሲያስሞሉ ህዝቡ እንደሩዋንዳ እየተነጣጠለ እንዲጫረስ ነበር። የኦሮምያ አስተዳደር መታወቂያ ላይ የሚሰፍረው ብሄር የሚለው እንዲቀር በማድረጉ ሊመሰገን ይገባል።

የትምህርት ምኩራብ በሆኑ ዩኒቨርስቲዎች ለጋ ወጣቶች ከተለያዩ የአገራቸው ልጆች ጋር እንዳይገናኙ በዘር ሸንሽነው ያደራጁት ይህንን ልዩነት ይዘው እንዲያድጉና በጥላቻ ተለያይትው ለመገዛት እንዲመቹ ነበር። የወጣቶችን ትኩስ መንፈስና ስሜት ተጠቅመው የዘሩት ዘር ሙሉ በሙሉ ባያፈራም የሚያሳዝኑ ጉዳቶች ማድረሳቸው አልቀረም።በነዚህ ዩኒቨርስቲዎች የሽማግሌው የስብሃት ነጋና የዘመዶቹ ልጆች፣ የአባይ ፀሃዬ፣ የስዩም መስፍን፣ የአርከበ እቁባይ፣ የጌታቸው አሰፋና የሌሎችም ዘራፊ ወያኔ ልጆች የሉም። እነሱማ አባቶቻቸውን ተክተው ልጆቻችንን ሊገዙ በቻይናና በምዕራቡ ዓለም ትልልቅ ትምህርት ቤቶች በተዘረፈ የህዝብ ሃብት ይማራሉ። ከፊሎችም በሀሺሽ ናውዘዋል።

በየዩኒቨርስቲና ልዩ ልዩ ተቋማት ያላችሁ ወጣት ኢትዮጵያውያን ሆይ እንደ እናንተ ባሉ ምስኪን ኢትዮጵያውያን ላይ እጃችሁን አታንሱ! ጥላቻን የዘራው፣ ተስፋችሁን ያጨለመው የወያኔ ዘረኛ ስርዓት ነው። ይህ እንዲያበቃ የምታደርጉትን ትግል አቅጣጫው እንዲቀይር በተዘጋጀ ወጥምድ ውስጥ አትግቡ።

ህወሃቶች ኢትዮጵያውያን በየጎጣቸውና ጠባብ መንደራቸው ግርግም እንደገባ ክብት በአካባቢያቸው ተወስነው፣ የየክልሉ የወያኔ አሽከሮች ተሹመውባቸው፣ እንዳይንቀሳቀሱ ሲያግዱ ወያኔዎችና ቤተሰቦቻቸው መላ ኢትዮጵያን የመዝረፍ መብት ተጎናፅፈዋል። ለኦሮሞው አጥንቱን ከስክሶ ያስጠበቃት ኦጋዴን እንዳይኖርባት ሲገደልና በግማሽ ሚሊዮን የሚቆጠረው ሲፈናቀልባት ለህወሃት መኳንንትና ከሲአድባሬ ተባብረው ለወጉን ባለስልጣናት የግላቸው ናት። አማራው ከጠላት እየተዋደቀ እስከ ኦሜድላ ላስጠበቀው አገሩ ለጉቫ፣ ለዳንጉር፣ ለፓዊ ባዕድ ሆኖ የባንዳ የሹምባሽ ልጅ መሬቱንና ማዕድኑን ከአድዋ መጥቶ ይዘርፋል፤ አሶሳ ለኦሮሞው ውጭ አገር ሆና ይፈናቀልባታል፤ ጋምቤላን አኝዋኩ ጠብቆ መቆየቱ ሃጢያት ሆኖበት በመቶዎች ተገድሎ የተረፈው ተባርሮ የህወሃት ባለስልታናትና ዘመዶቻቸው በብቸኝነት (እንዳጋጣኢ ሆኖ ብለዋል) ኢንቭስተር ሆነውበታል። የምክር ቤት አባልም ናቸው። ጉራጌ ሠርቶ ያሳደጋት አዲስ አበባ ባዕዱ ሆና ከመርካቶ ተባርሮ እነሃጎስ ሱቆቹን የነጠቁት መሆኑን መናገር ሀቅ አንጂ ዘረኝነት አይደለም።

ለአንድ ኦሮሞ እንኳን ኦሮምያ ኢትዮጵያ ትጠብበዋለች። ልክ ለወያኔና ለቤትሰቦቻቸው እንደጠበበቻቸው። ለአማራው፣ ለጉራጌው፣ ለሲዳማው፣ ለወላይታው …ለሁሉም እንኳን አባቶቻቸው ተዋድቀው ያቆዩአት ኢትዮጵያ ይቅርና አፍሪካም፣ ዓለምም ይጠብባቸዋል። ቻይናና ወያኔ ከነዘመዶቹ የሚፏልልባት ኢትዮጵያ እንዴት ለዜጎቿ አትሆንም? ሁሉም በጠባብ የዘር አጥር ውስጥ ታስሮ ወያኔና አገልጋዮቹ መላ አገሩቱን ሲዘርፉ ለምን ይፈቀዳል?

የኦሮሞ ቄሮዎች፣ የአማራ ፋኖዎች የጠየቁት “እናንተ ማን ናችሁና ነው ሌሎችን አስራችሁ አገር የምትዘርፉት?” እያሉ ነው። በዚህም ሳያበቃ ለሶስት ዓመት በተካሄደው ህዝባዊ ትግል የተደናገጡትና የጌቶቻቸው አልጠረቃ ባይነት ያሳሰባቸው፣ አገልጋይነታችውም የሰለቻቸው የኢህአዴግ አባላት የህዝባቸውን ሮሮ ከመስማት አልፈው ወያኔን እየተገዳደሩ ነው። ለህወሃት ወፍራም ድመቶች በኦሮምያ፣ በአማራ፣ በጋምቤላ ወዘተ እንደወትሮው መዝረፍ ይቅርና መንቀሳቀስም ይክብዳቸዋል። በዚህም አያበቃም፤ የወያኔን አገዛዝ ህዝቡ በቃህ ስለአለው ፍፃሜው ቅርብ ነው።

አርባ ኪሎሜትር ድንበር አልፎ የገባን ሱዳን ተመለስ ማለት የፈራው ወያኔ እስክርቢቶ ብቻ የያዙትን የዩኒቨርስቲ ልጆች በመግደልና በመቀጥቀጥ የሰራዊቱን ሃያልነት ለማስመስከር ይታትራል። “በሸንጎ ቢረታ ሚስቱን ገብቶ መታ” እንዲሉ። ህወህት የዘራው የዘረኝነት መርዝ እንዲጋተው ይገደዳል። የኢትዮጵያ ህዝብ ለረጅም ጊዜ በቆየ የአብሮነት ባህሉ ዘረኝነትን አርክሶታልና። ወያኔ በሰፈረው ቁና ይሰፈርበታል።

ከአንተነህ መርዕድ (amerid2000@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: eprdf, Ethiopia, ethnic politics, Right Column - Primary Sidebar, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule