• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የሳሙኤል ግድያ ለታጋዮችም ለገዳዮችም ትልቅ ትምህርት ነው!”

July 5, 2015 11:54 pm by Editor Leave a Comment

ስለ ሳሙኤል ግድያ ብዙ ነገር ተብሏል፡፡ ብዙዎች ቁጭታቸውን ገልፀዋል፡፡ ለእኔ ከሳሙኤል አወቀ ግድያ ምን እንማራለን? የሚለው ነው ትልቁ ቁም ነገር፡፡ ሳሙኤል በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ንግግር ተናግረው የተገደሉ ሰዎች ጋር የሚመደብ ሰው ነው፡፡ የሳሙኤል ትውልድ አካል በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል፡፡ እንደገሚገሉት እያወቀ፣ ነገር ግን ያ ሞቱ ከንቱ እንዳይሆን አስፈላጊውን መረጃ አስቀምጦልናል፡፡ አቡነ ጴጥሮስ መንፈሳዊ አባት ማለት ምን ማለት እንደሆነ አስተምረው ህዝቡ ለጣሊያን እንዳይገዛ ሰብከው ተገድለዋል፡፡ ለዚህም ሀውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ይህ መታሰቢያ ለኢትዮጵያዊነት የመንፈስ ልዕልና እና የአልበገሬነት ምልክት ሆኖ ለዘላለም ይኖራል፡፡

የአቡነ ጴጥሮስን ታሪክ ተማሪዎችም ይማሩበታል፡፡ የሳሙኤልን ንግግርም ወደፊት እድሜ ከሰጠን እኛ እናየዋለን፡፡ እኛ ባንደርስበት እንኳ መጪው ትውልድ ሳሙኤል ለሀገሩ ሲል ዋጋ እንደከፈለ መታወሱ የማይቀር ነው፡፡ ምክንያቱም ይህን አይነት ታሪክ የሰሩ ሰዎች በህዝቡ ውስጥ ትንሽና የተመረጡ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ በመሆኑም ሳሙኤል ከመካከላችን የተገኘ ልዩና ዕንቁ የኢትዮጵያ ልጅ ነው፡፡ ሳሙኤል እኔ በምመራው ፓርቲ፣ በእኔ ትውልድ ውስጥ እንዲህ አይነት ታሪክ መስራቱ ትልቅ የመንፈስ ጥንካሬ ሰጥቶኛል፡፡ ህይወት ምን እንደሆነም አስተምሮኛል፡፡

በህይወት መቆየትን እንደ ትልቅ ነገር ቆጥረውት ከትግል እንድንወጣ የሚመክሩን በርካቶች ናቸው፡፡ እነሱ የሚሉን ህዝብ ሲጨቆን ዝም በሉ ነው፡፡ ሳሙኤል ደግሞ እንዲህ አይነቱን ነገር መስራት እንደሌለብን በደሙና በአንድ በማትተካ ህይወቱ አሳይቶናል፡፡ እንደዚህ የሚሉንን ሰዎች ለመናቅ ሳሙኤልን ማሰብ ብቻ በቂ ነው፡፡ ገንዘብ ሲቸግረኝ ሳሙኤል ህይወቱን ማጣቱን ማስታወስ ይገባኛል፡፡ ለህይወት ትኩረት ስሰጥ፣ መኖር ስመኝ፣ መንፈሴ ሲላላ በእኔ ትውልድ ዘላለማዊ ሆኖ ያለፈውን ሳሙኤልን ማስታወስ አለብኝ፡፡ የሳሙኤል ግድያ ለታጋዮችም ለገዳዮችም ትልቅ ትምህርት ይሰጣል፡፡ በእኔ እምነት ሳሙኤልን የገደሉት በግል ስለሚጠሉት አይመስለኝም፡፡ ሳሙኤል የብሩህ አእምሮ ባለቤት ነው፡፡

የመረጃና የአቋም ሰው ነው፡፡ በጣም ጠንካራ ልጅ ነው፡፡ ይህን አስተሳሰቡንና እምነቱን ነው የጠሉት፡፡ ይህ ሲጠፋ ለሌሎቹም መቀጣጫ መሆኑ ነው፡፡ ዛሬ ግን በሳሙኤል ደም እኛ ተሰባስበናል፡፡ መፍራትና ወደኋላ ማለት እንደሌለብንም አስተምሮናል፡፡ ከዚህ ባለፈ በዚህ ትግል ውስጥ ለነገ የሚባል ነገር እንደማይሰራ የሳሙኤል ግድያ አሳይቶናል፡፡.የሰው ልጅ በባህሪው ሞኝ ነው፡፡ ዛሬን ብቻ አይደለም ዘላለምንም የምንኖር ነው የሚመስለን፡፡ ለሳሙኤል ግድያ ግን ህይወት ምን ማለት እንደሆነች አሳይቶናል፡፡ ዛሬውኑ ልትጠፋ የምትችል ከንቱ እንደሆነች አስተምሮናል፡፡ በመሆኑም የሳሙኤል ሞት ትርጉም ያለውን ነገር ዛሬ አድርጌ እንዳልፍ እንጅ ለነገ እንዳልል ትልቅ ትምህርት ሆኖኛል፡፡ ዕቅድ አንድ ነገር ነው፡፡ ሆኖም ሞት አብሮን ያለ መሆኑን ተረድተን ለሀገራችን የሚጠቅመውንና ዛሬ ማድረግ ያለብንን ነገር ዛሬውኑ መስራት እንዳለብን ነው፡፡ እንደ ሳሙኤል በዚህ አለም የማያልፍ ነገርን ሰርተን ማለፍ አለብን፡፡ በነፃነት ትግል ውስጥ ሳሙኤል ስም ሲነሳ ይኖራል፡፡ እንደ ሳሙኤል በህይወት ትርጉም ያለው ነገር መስራት ለህይወትም ትልቅ ትርጉም ይሰጣል፡፡ በኢትዮጵያ ከሉሲ ጀምሮ በሚሊዮን የሚቆጠር ሰው ሞቷል፡፡ ዋናው ነገር ግን 80ና 90 ቆይቶ መሞት አይደለም፡፡ እንደ ሳሙኤል በአጭር እድሜው ያመነበትን ሰርቶ መሞት ትልቅ ትርጉም አለው፡፡

እኛም 90ና 80 አመትን መጠበቅ ሳይሆን በ27 አመትም መቀጨት እንዳለ አውቀን አሁን መስራት ያለብንን በፍጥነት ማከናወን አለብን፡፡ በዚህ ግለኝነት፣ አግበስባሽነት በነገሰበት ሀገር ላይ ህይወትን ያህል ነገር ከፍሎ በደሙ ለእኛው ትውልድ አስተምሮ ሄዷል፡፡ ለሀገር፣ ለህዝብና ለእውነት መቆም የተከበረ ስራ መሆኑን ያውም ህይወቱን እንደሚያጣ አውቆት ለዓላማው በፍላጎቱ ሲሞት ከዚህ በላይ አስተማሪ አያስፈልግም፡፡ በወቅቱ ‹‹ይህ ትውልድ አይረባም፣ ሀገሩን አይወድም፣ ከዝሙትና ከመጠጥ ያለፈ ነገር አያውቅም፣ አይችልም›› የሚባለውን ሳሙኤል የሚባል ብርቱ ልጅ ከመካከላችን ወጥቶ እውነት እንዳልሆነ በተግባር አሳይቶናል፡፡ በዚህ ዘመን ደግሞ የጠፋው ከሳሙኤል አይደለም፤ ለራሳችን የቃል ኪዳን ሰው መሆን ነው፡፡ የሳሙኤልን ቃል የራስ አድርጎ መውሰድ፡፡ ክብር፣ ሞገስ፣ እውነትና ቃል ኪዳን ለራስ ነው፡፡ እሱ አከበርንለትም አላከበርንለትም የሚያምንበትንና የድርሻውን ሰርቶ ሄዷል፡፡ ለራሳችን ለእውነት፣ ለህዝብ፣ ለሀገር መቆም የሚያስከብር መሆኑን አስተምሮን አልፎአል፡፡

ይህንን ሳሙኤል እያወቀው ሞቶ የሰጠንን ክብር፣ ቃልና መስዋዕትነት ሳናጓድል አደራ የማንበላ ሰዎች እንዳንሆን፡፡ እኔ የምታገለው ለማንም አይደለም፡፡ ይች እግዚያብሄር የሰጠኝ እድሜ ትርጉም ያላት ሆና እንድታልቅ ስለምፈልግ ነው፡፡ ሳሙኤል በልጅነት እድሜው ቤተሰቦቹን አሳዝኖ ለእኛ ዋጋ ከፍሎልናል፡፡ ይህን ቃል ኪዳን ድርጅታችን እንደ ሰማያዊ፣ እያንዳንዳችን እንደ ግለሰብም፣ እንደማህበረስብና እንደትውልድም እንዳንበላ ብርታቱን ይስጠን እላለሁ፡፡

(ነገረ ኢትዮጵያ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule