• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የሳሙኤል ግድያ ለታጋዮችም ለገዳዮችም ትልቅ ትምህርት ነው!”

July 5, 2015 11:54 pm by Editor Leave a Comment

ስለ ሳሙኤል ግድያ ብዙ ነገር ተብሏል፡፡ ብዙዎች ቁጭታቸውን ገልፀዋል፡፡ ለእኔ ከሳሙኤል አወቀ ግድያ ምን እንማራለን? የሚለው ነው ትልቁ ቁም ነገር፡፡ ሳሙኤል በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ንግግር ተናግረው የተገደሉ ሰዎች ጋር የሚመደብ ሰው ነው፡፡ የሳሙኤል ትውልድ አካል በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል፡፡ እንደገሚገሉት እያወቀ፣ ነገር ግን ያ ሞቱ ከንቱ እንዳይሆን አስፈላጊውን መረጃ አስቀምጦልናል፡፡ አቡነ ጴጥሮስ መንፈሳዊ አባት ማለት ምን ማለት እንደሆነ አስተምረው ህዝቡ ለጣሊያን እንዳይገዛ ሰብከው ተገድለዋል፡፡ ለዚህም ሀውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ይህ መታሰቢያ ለኢትዮጵያዊነት የመንፈስ ልዕልና እና የአልበገሬነት ምልክት ሆኖ ለዘላለም ይኖራል፡፡

የአቡነ ጴጥሮስን ታሪክ ተማሪዎችም ይማሩበታል፡፡ የሳሙኤልን ንግግርም ወደፊት እድሜ ከሰጠን እኛ እናየዋለን፡፡ እኛ ባንደርስበት እንኳ መጪው ትውልድ ሳሙኤል ለሀገሩ ሲል ዋጋ እንደከፈለ መታወሱ የማይቀር ነው፡፡ ምክንያቱም ይህን አይነት ታሪክ የሰሩ ሰዎች በህዝቡ ውስጥ ትንሽና የተመረጡ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ በመሆኑም ሳሙኤል ከመካከላችን የተገኘ ልዩና ዕንቁ የኢትዮጵያ ልጅ ነው፡፡ ሳሙኤል እኔ በምመራው ፓርቲ፣ በእኔ ትውልድ ውስጥ እንዲህ አይነት ታሪክ መስራቱ ትልቅ የመንፈስ ጥንካሬ ሰጥቶኛል፡፡ ህይወት ምን እንደሆነም አስተምሮኛል፡፡

በህይወት መቆየትን እንደ ትልቅ ነገር ቆጥረውት ከትግል እንድንወጣ የሚመክሩን በርካቶች ናቸው፡፡ እነሱ የሚሉን ህዝብ ሲጨቆን ዝም በሉ ነው፡፡ ሳሙኤል ደግሞ እንዲህ አይነቱን ነገር መስራት እንደሌለብን በደሙና በአንድ በማትተካ ህይወቱ አሳይቶናል፡፡ እንደዚህ የሚሉንን ሰዎች ለመናቅ ሳሙኤልን ማሰብ ብቻ በቂ ነው፡፡ ገንዘብ ሲቸግረኝ ሳሙኤል ህይወቱን ማጣቱን ማስታወስ ይገባኛል፡፡ ለህይወት ትኩረት ስሰጥ፣ መኖር ስመኝ፣ መንፈሴ ሲላላ በእኔ ትውልድ ዘላለማዊ ሆኖ ያለፈውን ሳሙኤልን ማስታወስ አለብኝ፡፡ የሳሙኤል ግድያ ለታጋዮችም ለገዳዮችም ትልቅ ትምህርት ይሰጣል፡፡ በእኔ እምነት ሳሙኤልን የገደሉት በግል ስለሚጠሉት አይመስለኝም፡፡ ሳሙኤል የብሩህ አእምሮ ባለቤት ነው፡፡

የመረጃና የአቋም ሰው ነው፡፡ በጣም ጠንካራ ልጅ ነው፡፡ ይህን አስተሳሰቡንና እምነቱን ነው የጠሉት፡፡ ይህ ሲጠፋ ለሌሎቹም መቀጣጫ መሆኑ ነው፡፡ ዛሬ ግን በሳሙኤል ደም እኛ ተሰባስበናል፡፡ መፍራትና ወደኋላ ማለት እንደሌለብንም አስተምሮናል፡፡ ከዚህ ባለፈ በዚህ ትግል ውስጥ ለነገ የሚባል ነገር እንደማይሰራ የሳሙኤል ግድያ አሳይቶናል፡፡.የሰው ልጅ በባህሪው ሞኝ ነው፡፡ ዛሬን ብቻ አይደለም ዘላለምንም የምንኖር ነው የሚመስለን፡፡ ለሳሙኤል ግድያ ግን ህይወት ምን ማለት እንደሆነች አሳይቶናል፡፡ ዛሬውኑ ልትጠፋ የምትችል ከንቱ እንደሆነች አስተምሮናል፡፡ በመሆኑም የሳሙኤል ሞት ትርጉም ያለውን ነገር ዛሬ አድርጌ እንዳልፍ እንጅ ለነገ እንዳልል ትልቅ ትምህርት ሆኖኛል፡፡ ዕቅድ አንድ ነገር ነው፡፡ ሆኖም ሞት አብሮን ያለ መሆኑን ተረድተን ለሀገራችን የሚጠቅመውንና ዛሬ ማድረግ ያለብንን ነገር ዛሬውኑ መስራት እንዳለብን ነው፡፡ እንደ ሳሙኤል በዚህ አለም የማያልፍ ነገርን ሰርተን ማለፍ አለብን፡፡ በነፃነት ትግል ውስጥ ሳሙኤል ስም ሲነሳ ይኖራል፡፡ እንደ ሳሙኤል በህይወት ትርጉም ያለው ነገር መስራት ለህይወትም ትልቅ ትርጉም ይሰጣል፡፡ በኢትዮጵያ ከሉሲ ጀምሮ በሚሊዮን የሚቆጠር ሰው ሞቷል፡፡ ዋናው ነገር ግን 80ና 90 ቆይቶ መሞት አይደለም፡፡ እንደ ሳሙኤል በአጭር እድሜው ያመነበትን ሰርቶ መሞት ትልቅ ትርጉም አለው፡፡

እኛም 90ና 80 አመትን መጠበቅ ሳይሆን በ27 አመትም መቀጨት እንዳለ አውቀን አሁን መስራት ያለብንን በፍጥነት ማከናወን አለብን፡፡ በዚህ ግለኝነት፣ አግበስባሽነት በነገሰበት ሀገር ላይ ህይወትን ያህል ነገር ከፍሎ በደሙ ለእኛው ትውልድ አስተምሮ ሄዷል፡፡ ለሀገር፣ ለህዝብና ለእውነት መቆም የተከበረ ስራ መሆኑን ያውም ህይወቱን እንደሚያጣ አውቆት ለዓላማው በፍላጎቱ ሲሞት ከዚህ በላይ አስተማሪ አያስፈልግም፡፡ በወቅቱ ‹‹ይህ ትውልድ አይረባም፣ ሀገሩን አይወድም፣ ከዝሙትና ከመጠጥ ያለፈ ነገር አያውቅም፣ አይችልም›› የሚባለውን ሳሙኤል የሚባል ብርቱ ልጅ ከመካከላችን ወጥቶ እውነት እንዳልሆነ በተግባር አሳይቶናል፡፡ በዚህ ዘመን ደግሞ የጠፋው ከሳሙኤል አይደለም፤ ለራሳችን የቃል ኪዳን ሰው መሆን ነው፡፡ የሳሙኤልን ቃል የራስ አድርጎ መውሰድ፡፡ ክብር፣ ሞገስ፣ እውነትና ቃል ኪዳን ለራስ ነው፡፡ እሱ አከበርንለትም አላከበርንለትም የሚያምንበትንና የድርሻውን ሰርቶ ሄዷል፡፡ ለራሳችን ለእውነት፣ ለህዝብ፣ ለሀገር መቆም የሚያስከብር መሆኑን አስተምሮን አልፎአል፡፡

ይህንን ሳሙኤል እያወቀው ሞቶ የሰጠንን ክብር፣ ቃልና መስዋዕትነት ሳናጓድል አደራ የማንበላ ሰዎች እንዳንሆን፡፡ እኔ የምታገለው ለማንም አይደለም፡፡ ይች እግዚያብሄር የሰጠኝ እድሜ ትርጉም ያላት ሆና እንድታልቅ ስለምፈልግ ነው፡፡ ሳሙኤል በልጅነት እድሜው ቤተሰቦቹን አሳዝኖ ለእኛ ዋጋ ከፍሎልናል፡፡ ይህን ቃል ኪዳን ድርጅታችን እንደ ሰማያዊ፣ እያንዳንዳችን እንደ ግለሰብም፣ እንደማህበረስብና እንደትውልድም እንዳንበላ ብርታቱን ይስጠን እላለሁ፡፡

(ነገረ ኢትዮጵያ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule